ለጁምኣችን
💚
የሀይማኖት መብት ሳይከበርላቸው በሀገራቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታዩ የሀይማኖት፣የኢኮኖሚ እና የመሳሰሉት ጥያቄ እያለባቸው....ስለ ሀገራቸው ክብር የንጉሱን ጥሪ ተከትለው ለዘመቱት የሙስሊም ገበሬዎችና የጦር አበጋዞች እንዲሁም ለሁሉም የአድዋ ዘማቾች ክብር ለነሱ!
ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የሀገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው።
#ሙስሊሞቹ የጦር አበጋዞች እና ዓድዋ
በተለያዩ ጠሀፊወች በተደጋጋሚ እንዳስተዋልነው በታላቁ የአድዋ ጦርነት ለድሉ ከፍተኛውን ድርሻ ያበረከተው በራስ ሚካኤል ዓሊ ሥር የዘመተው የፈረሰኛ ጦር ነበር፤ በሌላ ግንባር ሲዋጉ የተማረኩት የጠላት ወታደሮች ሳይቀር የሚወረወረውን የፈረሰኛው ጦር ሚና እጅጉን የላቀ መሆኑን ሳይዘነጉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። ይህ ጦር በዓድዋ ጦርነት ወቅት ከንጉሠ ነገሥቱ ምኒልክ በእስከ ቀኝ በኩል ተሰልፎ የጠላትን ጦር እንዳልነበር ያደረገ እና ውሽመጣቸውን የቆረጠ ነበር። በጦርነትም ጄነራል አልበርቶኒን ሊረዳ የመጣውን በጄነራል ዳቦርሜዳ የሚመራውን ሙሉ ብርጌድ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር የደመሰሰው ይኼ ፈረሰኛ ሰራዊት ነው። የጄነራል ዳቦርሜዳ ሬሳ እንኴን አልተገኘም፤ ምንም ምርኮኛም አልነበረም። እንደሚታውቀው ይኼ ጦር Proper Wollo ከሚባለው የዛሬው ደቡብ ወሎ ክፍል የተውጣጣ በአብዛኛው የእስልምና ተከታይ የነበረ የገበሬ ወታደር ሲሆን በሙስሊም የጦር አበጋዞችም ይመራ ነበር።
.
ከታዋቂወቹ ከእነዚህ ሙስሊም ጦር አበጋዞች ዋናዋናወቹ የእርቄው ገዢ የሞሀመድ ቃንቄ ልጅ ደጅ አዝማች ይመር ሞሀመድ፣ የዓሊ ቤት ገዥ ራስ በሽር፣ የኮሬብ ገዥ ደጅ አዝማች ሊበን በሽር በጉልህ ስማቸው የሚነሳ ነው። አንዳንድ የውጭ ሀገር የታሪክ ጠሀፊወች ሀገራችንን ከውጭ ሆነው ክርስትያን ነገሥታቱን ብቻ በማየት በርካታ ሙስሊም ማህበረሰብ መኖሩን በመዘንጋት በጣፏቸው ማስታወሻወች ይኼን የእስልምና ተከታይ የዓድዋ ዘመቻ እግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር በዓድዋ ላይ ያደረገውን ተጋድሎ ለክርስትያን አገር የተከፈለ መስዋትነት በማለት ድሉን ለማጥበብ ይሞክራሉ። ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የአገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው። ዓድዋ ከተካሄደ ከሁለት ዓመት በኋላ የትግራዩ ራስ መንገሻ ሲያምጥ ከራስ መኮነን ጦር ጋር ተቀናጅቶ በቀላሉ ራስ መንገሻን በቁጥጥር ሥር ያዋለው በእነ ራስ በሽር እና ፊታውራሪ ሥራህ ብዙ የሚመራው ይኼው ጦር ነበር።
.
ሸጋ ጁምኣ!💚
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
💚
የሀይማኖት መብት ሳይከበርላቸው በሀገራቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታዩ የሀይማኖት፣የኢኮኖሚ እና የመሳሰሉት ጥያቄ እያለባቸው....ስለ ሀገራቸው ክብር የንጉሱን ጥሪ ተከትለው ለዘመቱት የሙስሊም ገበሬዎችና የጦር አበጋዞች እንዲሁም ለሁሉም የአድዋ ዘማቾች ክብር ለነሱ!
ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የሀገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው።
#ሙስሊሞቹ የጦር አበጋዞች እና ዓድዋ
በተለያዩ ጠሀፊወች በተደጋጋሚ እንዳስተዋልነው በታላቁ የአድዋ ጦርነት ለድሉ ከፍተኛውን ድርሻ ያበረከተው በራስ ሚካኤል ዓሊ ሥር የዘመተው የፈረሰኛ ጦር ነበር፤ በሌላ ግንባር ሲዋጉ የተማረኩት የጠላት ወታደሮች ሳይቀር የሚወረወረውን የፈረሰኛው ጦር ሚና እጅጉን የላቀ መሆኑን ሳይዘነጉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። ይህ ጦር በዓድዋ ጦርነት ወቅት ከንጉሠ ነገሥቱ ምኒልክ በእስከ ቀኝ በኩል ተሰልፎ የጠላትን ጦር እንዳልነበር ያደረገ እና ውሽመጣቸውን የቆረጠ ነበር። በጦርነትም ጄነራል አልበርቶኒን ሊረዳ የመጣውን በጄነራል ዳቦርሜዳ የሚመራውን ሙሉ ብርጌድ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር የደመሰሰው ይኼ ፈረሰኛ ሰራዊት ነው። የጄነራል ዳቦርሜዳ ሬሳ እንኴን አልተገኘም፤ ምንም ምርኮኛም አልነበረም። እንደሚታውቀው ይኼ ጦር Proper Wollo ከሚባለው የዛሬው ደቡብ ወሎ ክፍል የተውጣጣ በአብዛኛው የእስልምና ተከታይ የነበረ የገበሬ ወታደር ሲሆን በሙስሊም የጦር አበጋዞችም ይመራ ነበር።
.
ከታዋቂወቹ ከእነዚህ ሙስሊም ጦር አበጋዞች ዋናዋናወቹ የእርቄው ገዢ የሞሀመድ ቃንቄ ልጅ ደጅ አዝማች ይመር ሞሀመድ፣ የዓሊ ቤት ገዥ ራስ በሽር፣ የኮሬብ ገዥ ደጅ አዝማች ሊበን በሽር በጉልህ ስማቸው የሚነሳ ነው። አንዳንድ የውጭ ሀገር የታሪክ ጠሀፊወች ሀገራችንን ከውጭ ሆነው ክርስትያን ነገሥታቱን ብቻ በማየት በርካታ ሙስሊም ማህበረሰብ መኖሩን በመዘንጋት በጣፏቸው ማስታወሻወች ይኼን የእስልምና ተከታይ የዓድዋ ዘመቻ እግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር በዓድዋ ላይ ያደረገውን ተጋድሎ ለክርስትያን አገር የተከፈለ መስዋትነት በማለት ድሉን ለማጥበብ ይሞክራሉ። ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የአገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው። ዓድዋ ከተካሄደ ከሁለት ዓመት በኋላ የትግራዩ ራስ መንገሻ ሲያምጥ ከራስ መኮነን ጦር ጋር ተቀናጅቶ በቀላሉ ራስ መንገሻን በቁጥጥር ሥር ያዋለው በእነ ራስ በሽር እና ፊታውራሪ ሥራህ ብዙ የሚመራው ይኼው ጦር ነበር።
.
ሸጋ ጁምኣ!💚
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
✨ልብህ ያሰበውን ጥሩ ነገር ከመፈጸም አትቦዝን። ሃሳቡ በውስጥህ አርጅቶ እስኪሞት አትጠብቅ። ሰዎች ምን ይሉኝ ብለህ አትፍራ። ሰዎች ብትሠራም ባትሠራም የሆነ ነገር ማለታቸው አይቀርም። ብቻ መጠንቀቅ ያለብህ አንድ ነገር አለ። ያም ነገር ድርጊትህ በጎ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ላይ ነው። ድርጊትህ ጥሩ መሆኑን ካመንክበት ለመተግበር ተጣጣር።
🔱 ድርጊትህ ሙሉ በሙሉ ባይሳካ እንኳ በመሞከርህ ብቻ የህሊና እረፍት ታገኛለህ። በተከታታይ ከሠራህ ደግሞ እየሠራህ ማሻሻልህ አይቀርም።
🔆ጥሩ ነገር ለማድረግ ምቹ ጊዜ አትጠብቅ። ምቹው ጊዜ ሃሳቡ ወደ ጭንቅላትህ የመጣበት ጊዜ ነው።
🔱መማር ባለብህ ጊዜ ተማር፣ መሥራት ባለብህ ጊዜ ሥራ፣ መዝፈን ባለብህ ጊዜ ዝፈን፣ መዘመር ባለብህ ጊዜ ዘምር፣ መጻፍ ባለብህ ጊዜ ጻፍ፣ ማረፍ ባለብህ ጊዜ እረፍ።
✍Toughe G kebede
ውብ አሁን❤️
🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
🔱 ድርጊትህ ሙሉ በሙሉ ባይሳካ እንኳ በመሞከርህ ብቻ የህሊና እረፍት ታገኛለህ። በተከታታይ ከሠራህ ደግሞ እየሠራህ ማሻሻልህ አይቀርም።
🔆ጥሩ ነገር ለማድረግ ምቹ ጊዜ አትጠብቅ። ምቹው ጊዜ ሃሳቡ ወደ ጭንቅላትህ የመጣበት ጊዜ ነው።
🔱መማር ባለብህ ጊዜ ተማር፣ መሥራት ባለብህ ጊዜ ሥራ፣ መዝፈን ባለብህ ጊዜ ዝፈን፣ መዘመር ባለብህ ጊዜ ዘምር፣ መጻፍ ባለብህ ጊዜ ጻፍ፣ ማረፍ ባለብህ ጊዜ እረፍ።
✍Toughe G kebede
ውብ አሁን❤️
🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
#እምወድሽዋ!❤ቅዳሜዋ!❤ ሸጋዬ❤
፩ .
ሰዓዲ ይቀጥላሉ
"ከፀደይ ደመና አንዲት የዝናብ ጠብታ ወደ ምድር ወደቀች - ሰፊውን ባህር ስታይ በሀፍረት አቀረቀረች :: እንዲህም አለች :- " ባህሩ ሁሉ በሞላበት ፤ እኔ የት ነኝ ?በእርግጥም በህለውና የለሁም ልበል እንጂ ! "
በሀዘን ስታንጎራጉር በነበረበት ወቅት ነው አንድ የባህር ኦይስተር [Oyster] ወደ ሆዱ ውጦ ያስቀራት ፤ እጣ ክፍሏም ከትንሽ የዝናብ ጠብታ ወደ ክቡር ታላቅ የከበረ - ማዕድን ወደ ዕንቁነተ ቀየራት :: "
"ይሄው ነው" ይላሉ :- "አየህ ትሁት ነበረች ፥ ተከበረች ፤ ያለ መኖርን በር አንኳኳች ፥ ራሷን አሳነሰች ህልው የክቡራን ፅዋ - ተርታ ተቸራት :: "
፪.
አሁንም ሰዓዲ ይቀጥላሉ
ቀዘል አርሰላን ብርቱ የቤተ-መንግስት አጥር ነበረው - ቁመቱ ከ አልወንድ ተራራ የሚስተካከል [alofty mountain situated in Hamden , north-west of Isfahan] :: ከግንብ አጥሩ ውስጥ እንደ ሙሽራ ፀጉር በአፀደ - ፅጌያቱ ውስጥ እየተጠማዘዙ የሚዘልቁ ጎዳናውች ሞልተውታል ፤ በውስጧ ያሉ ኖሪዎቿ ሁሉ ያላንዳች ስጋት የተጠበቁ ነበሩ ::
ቀዘል በአንድ እለት - አንድ ጠቢብ መንገደኛ ያገኝና ይጠይቀዋል - ባንዳች የኩራት መንፈስ
" ከዚህ በፊት ይህን የመሰለ ብርቱ ግርማም የግንብ አጥር በተጏዝክበት ሁሉ አይተህ ታውቅ ይሆን ?"
" በእርግጥ ግሩም ነው !" ብሎ መለሰና :- " ነገር ግን አንዳች ብርታት እንደ ጎደለው አስባለሁ ፤ ካንተ በፊት የነብረው ንጉስ እጅ ላይ እንደ ነበር ሳስታውስ ፣ አሁንም ካንት በኇላ በሚነግሰው እጅ ላይ መውደቁን ሳስብ፣ ከዛም ደግሞ የነገሰው ንጉስ ከተስፋህ አፀድ ውስጥ ያሻውን ፍሬ ሲቢላ ይታየኝና - እውንትም አንዳች ጉልበት ፥ የሚመክትበት የተነሳው ነው እላለሁ :: "
In the estimation of the wise , the world is a false gem that passes each moment from one hand to another .
፫ .
አንድዎን የወሎ ሼኽ አንድ ያዲስ አበባ ሰው ሊኻድማቸው ወስዳቸው አሉ :: አሉ ነው መቼስ
ሁሉ ሁሉ ቀረበ ፣ ተበላም ተጠጣም :: ዱዓ ተያዘ ::
"ሼኾቹ እንግዲህ ያማረ ሀብት ፣ ያማረ መሬት ፣ ያማረ ቦታ ነው 'ምሻ በሉ ዱዓ ያርጉልኝ " አለ ከፊት ሆኖ እያያቸው
"እንግዲህ " አሉ :- " እንግዲህ አላህ ታንዱ ወስዶ ቲያበቃ ላንዱ ነው 'ሚሰጥና .. " እንዳሉ ሳያስጨርሳቸው
" ኧረ እነ ሸኽ እኔ የራሴን ነው 'ምፈልገው "
ቆጣ ብለው መለሱ :-
" ኧረግ ታያ ላንተ ተብሎ አዲስ መሬት አይዘረጋ !"
ምንጭ -Sa'adi collected works (Delphi classics)
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
፩ .
ሰዓዲ ይቀጥላሉ
"ከፀደይ ደመና አንዲት የዝናብ ጠብታ ወደ ምድር ወደቀች - ሰፊውን ባህር ስታይ በሀፍረት አቀረቀረች :: እንዲህም አለች :- " ባህሩ ሁሉ በሞላበት ፤ እኔ የት ነኝ ?በእርግጥም በህለውና የለሁም ልበል እንጂ ! "
በሀዘን ስታንጎራጉር በነበረበት ወቅት ነው አንድ የባህር ኦይስተር [Oyster] ወደ ሆዱ ውጦ ያስቀራት ፤ እጣ ክፍሏም ከትንሽ የዝናብ ጠብታ ወደ ክቡር ታላቅ የከበረ - ማዕድን ወደ ዕንቁነተ ቀየራት :: "
"ይሄው ነው" ይላሉ :- "አየህ ትሁት ነበረች ፥ ተከበረች ፤ ያለ መኖርን በር አንኳኳች ፥ ራሷን አሳነሰች ህልው የክቡራን ፅዋ - ተርታ ተቸራት :: "
፪.
አሁንም ሰዓዲ ይቀጥላሉ
ቀዘል አርሰላን ብርቱ የቤተ-መንግስት አጥር ነበረው - ቁመቱ ከ አልወንድ ተራራ የሚስተካከል [alofty mountain situated in Hamden , north-west of Isfahan] :: ከግንብ አጥሩ ውስጥ እንደ ሙሽራ ፀጉር በአፀደ - ፅጌያቱ ውስጥ እየተጠማዘዙ የሚዘልቁ ጎዳናውች ሞልተውታል ፤ በውስጧ ያሉ ኖሪዎቿ ሁሉ ያላንዳች ስጋት የተጠበቁ ነበሩ ::
ቀዘል በአንድ እለት - አንድ ጠቢብ መንገደኛ ያገኝና ይጠይቀዋል - ባንዳች የኩራት መንፈስ
" ከዚህ በፊት ይህን የመሰለ ብርቱ ግርማም የግንብ አጥር በተጏዝክበት ሁሉ አይተህ ታውቅ ይሆን ?"
" በእርግጥ ግሩም ነው !" ብሎ መለሰና :- " ነገር ግን አንዳች ብርታት እንደ ጎደለው አስባለሁ ፤ ካንተ በፊት የነብረው ንጉስ እጅ ላይ እንደ ነበር ሳስታውስ ፣ አሁንም ካንት በኇላ በሚነግሰው እጅ ላይ መውደቁን ሳስብ፣ ከዛም ደግሞ የነገሰው ንጉስ ከተስፋህ አፀድ ውስጥ ያሻውን ፍሬ ሲቢላ ይታየኝና - እውንትም አንዳች ጉልበት ፥ የሚመክትበት የተነሳው ነው እላለሁ :: "
In the estimation of the wise , the world is a false gem that passes each moment from one hand to another .
፫ .
አንድዎን የወሎ ሼኽ አንድ ያዲስ አበባ ሰው ሊኻድማቸው ወስዳቸው አሉ :: አሉ ነው መቼስ
ሁሉ ሁሉ ቀረበ ፣ ተበላም ተጠጣም :: ዱዓ ተያዘ ::
"ሼኾቹ እንግዲህ ያማረ ሀብት ፣ ያማረ መሬት ፣ ያማረ ቦታ ነው 'ምሻ በሉ ዱዓ ያርጉልኝ " አለ ከፊት ሆኖ እያያቸው
"እንግዲህ " አሉ :- " እንግዲህ አላህ ታንዱ ወስዶ ቲያበቃ ላንዱ ነው 'ሚሰጥና .. " እንዳሉ ሳያስጨርሳቸው
" ኧረ እነ ሸኽ እኔ የራሴን ነው 'ምፈልገው "
ቆጣ ብለው መለሱ :-
" ኧረግ ታያ ላንተ ተብሎ አዲስ መሬት አይዘረጋ !"
ምንጭ -Sa'adi collected works (Delphi classics)
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
❤️በሰላም ቤትህ ገብተህና ተኝነተህ በነጋታው ጠዋት በሰላም መነሳትህን በፍጹም አትልመደው (Never take it for granted)፤ ይህንን እድል ያላገኙ ብዙ ሰዎች አሉና!
🌗ይህንን ከፈጣሪ ብቻ ልታገኝ የምትችለውን የየቀን ተአምር እንዳልረሳኸው ለራስህ ለማስታወስ ከፈለክ ነገ ጠዋት በጥሩ አእምሮ ስትነቃ አንድን ነገር ለማድረግ አስበህ መተኛት ትችላለህ፡፡ ነገ የአንድን ሰው ችግር የሚያቃልል አንዲትን ተግባር ማከናወን ትችላለህ፡፡
❤️ዋጋ ከፍለህ ብታደርገው የአንተን ህልውና የማይነካ፣ ለሌላው ለጨነቀው ሰው ግን የህልውና ጉዳይ የሚሆን አቅም በእጅህ ካለ የፈቃደኝነት ጉዳይ ነው እንጂ ያንን ከማድረግ ምንም ነገር እንደማይከለክልህ አትዘንጋ፡፡ አንድ ቀን የተጨመረልን አንድን ነገር በሰዎች ሕይወት እንድንጨምር እንደሆነ አትዘንጋ፡፡
ውብ እንቅልፍ❤️
✍ ደ/ር እዮብ ማሞ
❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
🌗ይህንን ከፈጣሪ ብቻ ልታገኝ የምትችለውን የየቀን ተአምር እንዳልረሳኸው ለራስህ ለማስታወስ ከፈለክ ነገ ጠዋት በጥሩ አእምሮ ስትነቃ አንድን ነገር ለማድረግ አስበህ መተኛት ትችላለህ፡፡ ነገ የአንድን ሰው ችግር የሚያቃልል አንዲትን ተግባር ማከናወን ትችላለህ፡፡
❤️ዋጋ ከፍለህ ብታደርገው የአንተን ህልውና የማይነካ፣ ለሌላው ለጨነቀው ሰው ግን የህልውና ጉዳይ የሚሆን አቅም በእጅህ ካለ የፈቃደኝነት ጉዳይ ነው እንጂ ያንን ከማድረግ ምንም ነገር እንደማይከለክልህ አትዘንጋ፡፡ አንድ ቀን የተጨመረልን አንድን ነገር በሰዎች ሕይወት እንድንጨምር እንደሆነ አትዘንጋ፡፡
ውብ እንቅልፍ❤️
✍ ደ/ር እዮብ ማሞ
❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
ሰዓት እላፊ!
💚
# መፅሐፍ በዞረበት ከዞርኩኝ ሁለት ወር አልፎኝ ነበር (ለምንም ነገር ስሜት አጥታቹ ታውቃላቹ..?)እንደዛ ነገር! .....አስታወሳችሁት ከዚህ ቀደም ስለዚህ መፅሐፍ አውርቻቹ ነበር #በመሀል ለምን አልደግመውም በሚል መፅሐፉን ደገምኩት በቃ የተለየ ስሜት ነው የተሰማኝ በድጋሚም.......
#ተከተሉኝ
.
.
.
የጊዜ ዑደት የማይለውጠው ነገር አይኖረውም የማይችለው ነገር ቢኖር መሆን ያለብንን እና መሄዳችንን ብቻ ይመስለኛል ከዛ ውጭ ጊዜ ሁሉን እየወለወለ፣ እየከለሰ እያደሰም ሆነ እያፈረሰ እሳቤን፣ማንነትን ያሳየናል።ከጊዜ ጋር የማይበስል፣ በጊዜ እሳት ተጥዶም እንጭጭ የሚሆን አይጠፋም... ላውራላችሁ ያሰብኩት ስለ ጊዜ ሳይሆን ስለ አንድ መፅሀፍ ነው መቼቱን የወያኔ እንቅስቃሴ በተማሪዎች ላይ ሰርፆ በገባበት ወቅት ያረገው ይህ መፅሀፍ ከሀርቡ ተነስቶ በሀሳብ እና በፍልስፍና እየጎለበተ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴን ያስቃኘናል....ልጅ ሳለሁ የአንባቢ ጣሪያ የሰብለን እና የበዛብህን ታሪክ ፍቅር እስከ መቃብር ላይ አንቦ መጨረስ ይመስለኝ ነበር(ያኔ ይህ መፅሀፍ ሊነግረን የሚፈልገው ፍቅራቸውን ብቻ ይመስለኝ ነበር) በቃ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነበበ ካለ እሱ ለኔ የአንባቢ ጥግ ነበር....ለአሁኖቹ አንባቢያን ደግሞ አደፍርስ ይመስለኛል ገልጦ የጨረሰም አብጠርጥሮ የጨረሰም እኩል የምትወደው መፅሀፍ ሲባል አደፍርስ ይላል ይህን ሊል የሚችለው ግን ንባብን አዘውታሪ ከሆነ ብቻ ነው። ዛሬ ላይ ብዙ በገለጥን ቁጥር ብዙ እንደምናውቅ፤ ብዙ ባሰስን ቁጥር ብዙ እንደምናገኝ አውቃለሁ....አሁን ላወራላችሁ ያሰብኩት ስለ ሚክሎል ነው። ይህን መፅሀፍ ከገዛሁት ከወራቶች ቀደም ብሎም ያህል ቢሆነኝም ሁለቴ ገለጥኩት ሰሞኑን ነው ግን ውስጤን ሰቅዞ ስለያዘው እና ካተረፍኩት ደስታ ብትቃርሙ ብዬ ወደ እናንተ ያሳለፍኩት።
በፍቅር እስከ መቃብር ፣ በአደፍርስ እና አሁን ላወራላችሁ በፈለኩት ሚክሎል ውስጥ አንድ ከማህበረሰቡ በፍልስፍናቸው በእይታቸው እና በክዋኔያቸው አፈንጋጮች የተባሉ ግለሰቦች አሉ....ጉዱ ካሳ፣አደፍርስ እና ጉግሳ ነገር ግን ሁለቱ ከጉዱ ካሳ ጋር ሊያማስላቸው የሚችለው ነገር ማፈንገጣቸው ብቻ ሲሆን ሁለቱን ገፀ-ባህሪያት ግን አንዳንድ ተምሳሎት ስላላቸው ጥቂት ልበልላቸው። ሁለቱም ወጣት ናቸው የተገኙበትን ማህበረሰብ ማንቃት የሚሹ ፤ ሁለቱም ጥያቄ የሚጭሩ ሀሳቦችን የሚያነሱ ፤ ነገር ግን የሚክሎሉ ጉግሳ የማውቀው በቃኝ አይልም ሰው ይሰማል፣ የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ችላ አይላቸውም ይማርባቸዋል ፤ በሚያወራው አደፍርስ ሲያደንቁት ሲያሞካሹት ይወዳል ጉግሳ ግን ለሙገሳ ቦታም የለው ፤ አንዳንዴ የአደፍርስ ሀሳቦች ከማህበረሰቡ ሲወርድ(ሲቀል) ይታያል ፤ አደፍርስ መስጠትን እንጂ መቀበልን የህይወቱ ኡደት ውስጥ አልከተታቸውም ምን አልባት ሀሳቦችን ተቀባይ እንዲሆን በጉግሳ የህይወት እንቅስቃሴ ላይ የተሳሉት ይህን ባህሪ ስላደሉት ይሆናል መሬት ወርዶ ከመሀይሙ፣ ከእብዱ፤ ከሴተኛ አዳሪው ይስማማል ይማራል....የልጅነት ፍልስፍናውን በአባቱ ቅኝት ምንም የሚያቅትህ ነገር የለም፣ ሁሌም ቢሆን ከቀልብህ ምከር እያሉ የቃኙት ወጣት የዩንቨርስቲ ተማሪ በንባብ ያካበተውን ወደ ውስጥ ተመልካችነት ክህሎት አንድ እብድ ጋር ያደርሰው እና ያለምክንያት መኖር ክልክል ነው የሚል ፍልስፍና ይቸረዋል....ምርጥ ስነ-ፅሁፍ፣ ቆንጆ የሀሳብ ፍሰት እና የህይወት ፍልስፍና በአንድ ጥራዝ ታትመው ቀርበዋል!!!
አስቸኳይ የንባብ እርምጃ ይወሰድበት!!!!! እውነት አንብቡት ትወዱታላቹ!!
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta
💚
# መፅሐፍ በዞረበት ከዞርኩኝ ሁለት ወር አልፎኝ ነበር (ለምንም ነገር ስሜት አጥታቹ ታውቃላቹ..?)እንደዛ ነገር! .....አስታወሳችሁት ከዚህ ቀደም ስለዚህ መፅሐፍ አውርቻቹ ነበር #በመሀል ለምን አልደግመውም በሚል መፅሐፉን ደገምኩት በቃ የተለየ ስሜት ነው የተሰማኝ በድጋሚም.......
#ተከተሉኝ
.
.
.
የጊዜ ዑደት የማይለውጠው ነገር አይኖረውም የማይችለው ነገር ቢኖር መሆን ያለብንን እና መሄዳችንን ብቻ ይመስለኛል ከዛ ውጭ ጊዜ ሁሉን እየወለወለ፣ እየከለሰ እያደሰም ሆነ እያፈረሰ እሳቤን፣ማንነትን ያሳየናል።ከጊዜ ጋር የማይበስል፣ በጊዜ እሳት ተጥዶም እንጭጭ የሚሆን አይጠፋም... ላውራላችሁ ያሰብኩት ስለ ጊዜ ሳይሆን ስለ አንድ መፅሀፍ ነው መቼቱን የወያኔ እንቅስቃሴ በተማሪዎች ላይ ሰርፆ በገባበት ወቅት ያረገው ይህ መፅሀፍ ከሀርቡ ተነስቶ በሀሳብ እና በፍልስፍና እየጎለበተ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴን ያስቃኘናል....ልጅ ሳለሁ የአንባቢ ጣሪያ የሰብለን እና የበዛብህን ታሪክ ፍቅር እስከ መቃብር ላይ አንቦ መጨረስ ይመስለኝ ነበር(ያኔ ይህ መፅሀፍ ሊነግረን የሚፈልገው ፍቅራቸውን ብቻ ይመስለኝ ነበር) በቃ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነበበ ካለ እሱ ለኔ የአንባቢ ጥግ ነበር....ለአሁኖቹ አንባቢያን ደግሞ አደፍርስ ይመስለኛል ገልጦ የጨረሰም አብጠርጥሮ የጨረሰም እኩል የምትወደው መፅሀፍ ሲባል አደፍርስ ይላል ይህን ሊል የሚችለው ግን ንባብን አዘውታሪ ከሆነ ብቻ ነው። ዛሬ ላይ ብዙ በገለጥን ቁጥር ብዙ እንደምናውቅ፤ ብዙ ባሰስን ቁጥር ብዙ እንደምናገኝ አውቃለሁ....አሁን ላወራላችሁ ያሰብኩት ስለ ሚክሎል ነው። ይህን መፅሀፍ ከገዛሁት ከወራቶች ቀደም ብሎም ያህል ቢሆነኝም ሁለቴ ገለጥኩት ሰሞኑን ነው ግን ውስጤን ሰቅዞ ስለያዘው እና ካተረፍኩት ደስታ ብትቃርሙ ብዬ ወደ እናንተ ያሳለፍኩት።
በፍቅር እስከ መቃብር ፣ በአደፍርስ እና አሁን ላወራላችሁ በፈለኩት ሚክሎል ውስጥ አንድ ከማህበረሰቡ በፍልስፍናቸው በእይታቸው እና በክዋኔያቸው አፈንጋጮች የተባሉ ግለሰቦች አሉ....ጉዱ ካሳ፣አደፍርስ እና ጉግሳ ነገር ግን ሁለቱ ከጉዱ ካሳ ጋር ሊያማስላቸው የሚችለው ነገር ማፈንገጣቸው ብቻ ሲሆን ሁለቱን ገፀ-ባህሪያት ግን አንዳንድ ተምሳሎት ስላላቸው ጥቂት ልበልላቸው። ሁለቱም ወጣት ናቸው የተገኙበትን ማህበረሰብ ማንቃት የሚሹ ፤ ሁለቱም ጥያቄ የሚጭሩ ሀሳቦችን የሚያነሱ ፤ ነገር ግን የሚክሎሉ ጉግሳ የማውቀው በቃኝ አይልም ሰው ይሰማል፣ የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ችላ አይላቸውም ይማርባቸዋል ፤ በሚያወራው አደፍርስ ሲያደንቁት ሲያሞካሹት ይወዳል ጉግሳ ግን ለሙገሳ ቦታም የለው ፤ አንዳንዴ የአደፍርስ ሀሳቦች ከማህበረሰቡ ሲወርድ(ሲቀል) ይታያል ፤ አደፍርስ መስጠትን እንጂ መቀበልን የህይወቱ ኡደት ውስጥ አልከተታቸውም ምን አልባት ሀሳቦችን ተቀባይ እንዲሆን በጉግሳ የህይወት እንቅስቃሴ ላይ የተሳሉት ይህን ባህሪ ስላደሉት ይሆናል መሬት ወርዶ ከመሀይሙ፣ ከእብዱ፤ ከሴተኛ አዳሪው ይስማማል ይማራል....የልጅነት ፍልስፍናውን በአባቱ ቅኝት ምንም የሚያቅትህ ነገር የለም፣ ሁሌም ቢሆን ከቀልብህ ምከር እያሉ የቃኙት ወጣት የዩንቨርስቲ ተማሪ በንባብ ያካበተውን ወደ ውስጥ ተመልካችነት ክህሎት አንድ እብድ ጋር ያደርሰው እና ያለምክንያት መኖር ክልክል ነው የሚል ፍልስፍና ይቸረዋል....ምርጥ ስነ-ፅሁፍ፣ ቆንጆ የሀሳብ ፍሰት እና የህይወት ፍልስፍና በአንድ ጥራዝ ታትመው ቀርበዋል!!!
አስቸኳይ የንባብ እርምጃ ይወሰድበት!!!!! እውነት አንብቡት ትወዱታላቹ!!
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta
• ዛሬ ዕለተ ማግሰኞ የካቲት ፳፫-፳፻፲፫ ለዐዉዳችን እንዲስማማ ኾኖ የቀረ ተንቀሳቃሽ ምስል ነዉ። ቦታዉ ብሔራዊ ሙዚየም ዉስጥ ነዉ ፥ በወፍ በረር የዓድዋ ጦርነትን ለማዉሳት ሙዚየም ዉስጥ ባሉ ጥንታዊ ቅርሶች እና የኅብር የስነ ስዕል ልኺቃን ለሦስተኛ ያበጃጁትን አዉደ-ርዕይ ዋቢ አድርጎ የተቃኘ ነዉ። በነገራችኹ ላይ ይኽ የስነ-ስዕል አዉደ ርዕይ ከየካቲት ፲፱ እስከ መጋቢት ፲፱|፳፻፲፫ ድረስ እነደሚሠነብት ከደጋሾቹ ተነግሮኛል። •
ከ@Mykeyonthestreet የተሰረቀ
ከ@Mykeyonthestreet የተሰረቀ
🗣🗣ጉዞ ወደ ሀሳብ..........
በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል
"
አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው
ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ? ኢትዮጵያ በተለየ የሚያይ አምላክ አለ..? ካለስ የአምላክነቱ ባህሪ (ፍትሃዊነት) ጥያቄ ውስጥ አይገባም ወይ...?
በሚኒሊክ ግዜ በፈረስ መጥቶ
የጣሊያኖችን አንገት የቀላልን ጊዮርጊስ በሃይለስላሴ ግዜ ለምን አልመጣም..?
ጣሊያኖች ተመልሰው መጥተው በመርዝ ጋዝ እንደ በረሮ ሲረፈርፉን ያ አድዋ ላይ የዘመተው መልአክ የት ሄደ? በ'3 ቀን 33 ሺ ኢትዮጵያዊያን በአካፋ በዶማ በድንጋይ ተወግረው እንደ ዶሮ አንገታቸው ተበጥሶ በየ መንገዱ ሲጣሉ አዲሳባ የደም ባህር ስቶን አድዋ ላይ የጣሊያኖችን አንገት የቀነጠሰው ጊዮርጊስ ምነው ለአዲስ
አበባ ግዜ ሲሆን ፀጥ አለ? ..
#አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?
በእነዚህ ሀሳቦች ላይ የምታምኑበትን በጨዋ ደንብ ሀሳባቹን ወርውሩልን🙏🙏🙏
@balmbaras
በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል
"
አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው
ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ? ኢትዮጵያ በተለየ የሚያይ አምላክ አለ..? ካለስ የአምላክነቱ ባህሪ (ፍትሃዊነት) ጥያቄ ውስጥ አይገባም ወይ...?
በሚኒሊክ ግዜ በፈረስ መጥቶ
የጣሊያኖችን አንገት የቀላልን ጊዮርጊስ በሃይለስላሴ ግዜ ለምን አልመጣም..?
ጣሊያኖች ተመልሰው መጥተው በመርዝ ጋዝ እንደ በረሮ ሲረፈርፉን ያ አድዋ ላይ የዘመተው መልአክ የት ሄደ? በ'3 ቀን 33 ሺ ኢትዮጵያዊያን በአካፋ በዶማ በድንጋይ ተወግረው እንደ ዶሮ አንገታቸው ተበጥሶ በየ መንገዱ ሲጣሉ አዲሳባ የደም ባህር ስቶን አድዋ ላይ የጣሊያኖችን አንገት የቀነጠሰው ጊዮርጊስ ምነው ለአዲስ
አበባ ግዜ ሲሆን ፀጥ አለ? ..
#አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?
በእነዚህ ሀሳቦች ላይ የምታምኑበትን በጨዋ ደንብ ሀሳባቹን ወርውሩልን🙏🙏🙏
@balmbaras
👍1
🌊"If you don’t have peace within yourself, it is very difficult to work for peace. [During the Vietnam war] our thinking was, the other person is not our enemy. Our enemies are misunderstanding, discrimination, violence, hatred, and anger. With that kind of insight, we conducted the peace movement.
❄️If you are filled with anger, you create more suffering for yourself than for the other person. When you are inhabited by the energy of anger, you want to punish, you want to destroy. That is why those who are wise do not want to say anything or do anything while the anger is still in them.
🌊So you try to bring peace into yourself first. When you are calm, when you are lucid, you will see that the other person is a victim of confusion, of hate, of violence transmitted by society, by parents, by friends, by the environment. When you are able to see that, your anger is no longer there...”
~Thich Nhat Hanh~
❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
❄️If you are filled with anger, you create more suffering for yourself than for the other person. When you are inhabited by the energy of anger, you want to punish, you want to destroy. That is why those who are wise do not want to say anything or do anything while the anger is still in them.
🌊So you try to bring peace into yourself first. When you are calm, when you are lucid, you will see that the other person is a victim of confusion, of hate, of violence transmitted by society, by parents, by friends, by the environment. When you are able to see that, your anger is no longer there...”
~Thich Nhat Hanh~
❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ስብዕናችን #Humanity
🗣🗣ጉዞ ወደ ሀሳብ.......... በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል " አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም…
ለጠየቅነው ጥያቄ .....ከተሰጡን መልሶች መካከል......👇👇👇
Zenit Simeneh:👇👇
እነሱም ፩ አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው መልዕክ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣልያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላችሁ? በደንብ አምናለሁ ይሄ ሀሳብ እኛ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳንሆን የዛኔ የተዋጉት ጣልያኖች እንዴት ነበር ውጊያው ተብለው ሲጠየቁ የመለሱት መልስ ነው በዛን ጊዜ የነበረ ጋዜጣ አንብብ ቃልበቃል ታገኘዋለህ። የቤት ስራ ይሁን ሲቀጥል አንተ ስታስበው እውነት ዘመናዊ መሳሪያ እስከ አፍንጫው የታጠቀ እና ሙሉ ወታደራዊ ስልጠና ያለውን ሰራዊት እንዴት ነው በገጀራ እና በገበሬ ልናሸንፍ የምንችለው ይሄ እኮ ፊልም አይደለም እውነተኛ ታሪክ እንጂ ፊልም እንኳን ሲቀጣቀጡ እንኳን ተቀራራቢ የጦር መሳሪያ ይዘው ነው ይሄ የሚያሳየው ኢትዮጽያዊነት ሚስጥር፣ ሀይል መሆኑን እና የሚጠብቃት እንደማይተኛ ነው። ሲሰልስ ሚኒሊክ እምነቱ በጣም የሚያስደንቅ ነው ገጀራው ላይ ሳይቀር የሚኒሊክ ተስፋው እግዚአብሔር ነው ይላል። ሂድ እምነትህ አድኖሃል ተብሎ እንደተፃፈ በቅዱስ መፅሐፍ ተዋጊህ ወይም ሰልፉን የሚመራው እግዚአብሔር ነው ብለህ እሱን ስታምን ጉልበት የሱ መሆኑን ስታውቅ እና እሱን ስታስቀድም በተቃራኒው ደሞ በወታደር እና በታንክ ስትመካ ይለያያል።
🔑 ሌሎች ሀገሮች በጣልያን የተገዙት እምነት እና የኢትዮጵያዊያን አይነት ወኔ እና ስሜት ስሌላቸው ነው በርሊን ስምምነት ላይ እኮ እጣ ሲከፋፈሉ ሶስት ምርጫ አስቀምጠውልን ነው በፍላጎት,፣ በግድ እና በስምምነት አብዛኛው እምነት ስላልነበራቸው ሊገዙ ሆኗል እምነት ለምንም ነገር መሰረት ነው ጎልያድ በጠጠር የተሸነፈው በእምነት ነው።
እንደ ዕቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ፣ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ካልክ ለምንድን ነው አንድአንዶች በሞቀ ቤት እየተኙ፣እየበሉ እና እየጠጡ በቤታቸው ውሻን እና ድመትን አንደላቀው እየኖሩ ለምን የጎዳና ልጆች ለምን ይራባሉ፣ይጠማሉ፣ራሳቸውን ለማሞቅ ለምን ቤንዚን ይስባሉ አየህ እግዚአብሔር አለም ላይ አንዱን ሀብታም አንዱን ደሀ አንዱን አካለ ጎዶሎ አንዱን "ሙሉ አካል"አርጎ የሚፈጥረው እኔ እንደወደድኳችው እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ የሚለውን የራሱን ሀይለ ቃል እኛ እርስ በእርሳችን በመረዳዳት እንድንፈፅመው እና በኃላ በፍርድ ጊዜ ሲመጣ ብራብ ብጠማ አላበላችሁኝም አላጠጣችሁኝም እንደሚል ቃሉ እናም እኛ ምን ያህል እሱን እንደምንታዘዝ ለማወቅም ጭምር ነው ስለዚህ እግዚአብሔር ኢፍትሃዊነት አያሳይም።
በሚኒሊክ ጊዜ ያለውን ሁነት በሌላ ጊዜ አንብቤ እከሰታለው ለዚህ ብዬ ለዛሬ የሚሆነውን መልስ ለነገ ማስተላለፍ ስላልፈለኩ ነው።
፪ ማሳያ ኢትዮጵያ ላይ እንደተሴረው ሴራ የእውነት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ትኖር ነበር???
፫ ማሳያ ኮረናን ተመልከት እውነት ኢትዮጵያ ላይ ኮረና ያልሰለጠነው የተባሉትን መመርያዎች ተግብረን ነው ውሃ በሌለበት(በሶስት ቀን አንዴ ) በሚመጣበት ሀገር እጃችንን ታጥበን ነው? በጠባብ ቤት ውስጥ ፮ እና ፯ ሰው እየኖረ እርቀታችንን ጠብቀን ነው?
፬ የእውነት በበይነ መረብ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ምሁር ነን ባዮች በሚፅፉት፣በሚያፅፉት እና በሚከራከሩበት መጠን እውነት እነሱ ጋር ያለ አስተሳሰብ ህዝቡ ጋር ቢኖር የእውነት ኢትዮጵያ ውስጥ ወጣት ብሎም ሰላም የሚባል ነገር ይኖር ነበር?? ሌላ ብዙ ማሳያ መፃፍ ይቻላል ለዛሬ ግን እዚህ ላይ ላብቃ።ይሄ ሁሉ ችግር ስዘረዝር እንዳፈራ የሀገራችን አምላክ አይተኛም ሀገራችንን ይጠብቃታል!!!
አፍሪቃውያን የኢትዮጵያ አምላክ ቸርች እስከመገንባት ደርሰው ነበር
ክብር ከብረው ላስከበሩን ጀግኖች አያት አባቶቻችን!!!
ሞተው ላኖሩን ጀግኖች ማርያምን!!!!!
ተቆራርጦ ስለደረሰህ በጣም ይቅርታ ቢያልፍም መልካም መቶ ሀያኛ የአድዋ ድል ይሁንልን!!!!!
👇👇👇👇
ስላም እንደት ነህ/ሽ
"አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?" የሚል ጥያቄ አንስተህ/ሽ እንድንወያይ ስለጋበዛችሁን አመሰግናለሁ።
እኔ አዎ በሚገባ ባይ ነኝ፡፡ ነገር ግን በእኔ አቅም ሊብራራ የማይችል ሲሆን የተቻለኝን ልሞክር
መጀመሪያ ፈጣሪ እንዲረዳን በእርሱ ማመን እና እርሱን የምንፈልገዉን መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ምሳሌ እኔ ከራበኝ ምግብ እንዲሰጡኝ ቤተሰቦቼን መጠየቅ አለብኝ፡፡ ስለዚህ ፈጣሪ እንዲረዳቸዉ ሌሎችም እንደ እምየ ምኒልክ አምነዉ መጠየቅ አለባቸዉ፡፡ ክርስቶስ ለኛ ነጻ ፈቃድ ነዉ የሰጠን፡፡ 38 ዓመት የአልጋ ቁራኛ የነበረዉን ወጣት ሲያድነዉ ዝም ብሎ ተነስ አልጋህን ተሸክመኅ ሒድ አላለዉም መጀመሪያ መዳን እንደሚፈልግ ከጠየቀ በኋላ አዳነዉ እንጅ፡፡ ስለዚህ እኛም እንዲረዳን መጠየቅ አለብን፡፡ የእምየ ምንሊክን የክተት አዋጅ ስናይ እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፋፍቶ አኖረኝ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ” በዚህ ዉስጥ ስንመለከት እስካሁንም እምየ ስልጣን ላይ የቆዩት በእርሳቸዉ ሀይል ብቻ ሳይሆን በፈጣሪም ቸርነት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ይቀጥሉ እና ”……….. ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብየ አልጠራጠርም” በዚህ ዉስጥ ደግሞ እምየ ፈጣሪን ይዘዉ ጦርነቱን እንደሚያሸንፉ ምንም ጥርጣሬ የላቸዉም፡፡ ይሄንንም እራሳቸዉ ጣሊያኖች ”አንድ ሰዉ በነጭ ፍረስ ሆኖ ፈጀን ከፊታቸዉ አላስደርሰን አለ” ብለዉ መጽሀፋቸዉ ላይ እንደጻፉ ይነገራል፡፡ በዚህ ዉስጥ ደሞ እምየ ምኒልክ የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ይዘዉ እንደዘመቱ ይታወቃል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረስ ደግሞ ነጭ ነዉ፡፡ ስለዚህ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ አብሮ አድዋ ላይ ተዋግትዋል፡፡ እንግዲህ እናንተ በጎደል ሙሉበት ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡
👇👇👇👇
አሁን ያነ ሳሀቸው ሀ ሳቦች እውነትም እንደጠየቅከው አይነት ጥያቄ ጭንቅላት ውስጥ ያጭራሉ....
ግን ምን አለ መሰለህ......
አዎ አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ አይን ያያታል
ለምን አልሽ ካልክ .... ያልኩበትን ሰበብ ልዘርዝር
1.ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደስጦታ ሲሰጣት(ያስራት ሀገርሽ ብሎ) "ሳያዩ የሚያምኑ ህዝቦች የሚኖሩባት ምድር ናት" ብሎ ራሱ መስክሮልናል
2. ትንቢተ አሞፅ ላይ "እናንት የእስራኤል ልጆች ሆይ ለኔ እንደኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን"ብሎ ምን ያህል እንደሚወደን መስክሯል
3.አምላክ ነጋ ጠባ የሚመሰገንባት አገር ናት... ሙስሊሙ ክርስትያኑ ፕሮቴስታንቱ ጆሆባው ሌላውም... ሳያመሰግን አይውልም አያድርም
ምሳሌ ልስጥህ... ሰንበት ሰንበት ይቀደሳል... አርብ አርብ ጁማ ነው... አለመግባባት ላይ "በህግ አምላክ!" ይባላል.... ስላምታ ላይ "እግዛብሔር ይመስገን" " አላህ ይመስገን" ይባላል... ሌላው የገዳማውያን ፀሎትም አይረሳም
4. "ኢትዮጵያ ታበፅዕ እደዊሀ ኀበ እግዚአብሔር" (እጇን ወደ እግዛብሔር ትዘረጋለች) ተብሎላታልም....
Zenit Simeneh:👇👇
እነሱም ፩ አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው መልዕክ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣልያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላችሁ? በደንብ አምናለሁ ይሄ ሀሳብ እኛ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳንሆን የዛኔ የተዋጉት ጣልያኖች እንዴት ነበር ውጊያው ተብለው ሲጠየቁ የመለሱት መልስ ነው በዛን ጊዜ የነበረ ጋዜጣ አንብብ ቃልበቃል ታገኘዋለህ። የቤት ስራ ይሁን ሲቀጥል አንተ ስታስበው እውነት ዘመናዊ መሳሪያ እስከ አፍንጫው የታጠቀ እና ሙሉ ወታደራዊ ስልጠና ያለውን ሰራዊት እንዴት ነው በገጀራ እና በገበሬ ልናሸንፍ የምንችለው ይሄ እኮ ፊልም አይደለም እውነተኛ ታሪክ እንጂ ፊልም እንኳን ሲቀጣቀጡ እንኳን ተቀራራቢ የጦር መሳሪያ ይዘው ነው ይሄ የሚያሳየው ኢትዮጽያዊነት ሚስጥር፣ ሀይል መሆኑን እና የሚጠብቃት እንደማይተኛ ነው። ሲሰልስ ሚኒሊክ እምነቱ በጣም የሚያስደንቅ ነው ገጀራው ላይ ሳይቀር የሚኒሊክ ተስፋው እግዚአብሔር ነው ይላል። ሂድ እምነትህ አድኖሃል ተብሎ እንደተፃፈ በቅዱስ መፅሐፍ ተዋጊህ ወይም ሰልፉን የሚመራው እግዚአብሔር ነው ብለህ እሱን ስታምን ጉልበት የሱ መሆኑን ስታውቅ እና እሱን ስታስቀድም በተቃራኒው ደሞ በወታደር እና በታንክ ስትመካ ይለያያል።
🔑 ሌሎች ሀገሮች በጣልያን የተገዙት እምነት እና የኢትዮጵያዊያን አይነት ወኔ እና ስሜት ስሌላቸው ነው በርሊን ስምምነት ላይ እኮ እጣ ሲከፋፈሉ ሶስት ምርጫ አስቀምጠውልን ነው በፍላጎት,፣ በግድ እና በስምምነት አብዛኛው እምነት ስላልነበራቸው ሊገዙ ሆኗል እምነት ለምንም ነገር መሰረት ነው ጎልያድ በጠጠር የተሸነፈው በእምነት ነው።
እንደ ዕቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ፣ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ካልክ ለምንድን ነው አንድአንዶች በሞቀ ቤት እየተኙ፣እየበሉ እና እየጠጡ በቤታቸው ውሻን እና ድመትን አንደላቀው እየኖሩ ለምን የጎዳና ልጆች ለምን ይራባሉ፣ይጠማሉ፣ራሳቸውን ለማሞቅ ለምን ቤንዚን ይስባሉ አየህ እግዚአብሔር አለም ላይ አንዱን ሀብታም አንዱን ደሀ አንዱን አካለ ጎዶሎ አንዱን "ሙሉ አካል"አርጎ የሚፈጥረው እኔ እንደወደድኳችው እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ የሚለውን የራሱን ሀይለ ቃል እኛ እርስ በእርሳችን በመረዳዳት እንድንፈፅመው እና በኃላ በፍርድ ጊዜ ሲመጣ ብራብ ብጠማ አላበላችሁኝም አላጠጣችሁኝም እንደሚል ቃሉ እናም እኛ ምን ያህል እሱን እንደምንታዘዝ ለማወቅም ጭምር ነው ስለዚህ እግዚአብሔር ኢፍትሃዊነት አያሳይም።
በሚኒሊክ ጊዜ ያለውን ሁነት በሌላ ጊዜ አንብቤ እከሰታለው ለዚህ ብዬ ለዛሬ የሚሆነውን መልስ ለነገ ማስተላለፍ ስላልፈለኩ ነው።
፪ ማሳያ ኢትዮጵያ ላይ እንደተሴረው ሴራ የእውነት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ትኖር ነበር???
፫ ማሳያ ኮረናን ተመልከት እውነት ኢትዮጵያ ላይ ኮረና ያልሰለጠነው የተባሉትን መመርያዎች ተግብረን ነው ውሃ በሌለበት(በሶስት ቀን አንዴ ) በሚመጣበት ሀገር እጃችንን ታጥበን ነው? በጠባብ ቤት ውስጥ ፮ እና ፯ ሰው እየኖረ እርቀታችንን ጠብቀን ነው?
፬ የእውነት በበይነ መረብ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ምሁር ነን ባዮች በሚፅፉት፣በሚያፅፉት እና በሚከራከሩበት መጠን እውነት እነሱ ጋር ያለ አስተሳሰብ ህዝቡ ጋር ቢኖር የእውነት ኢትዮጵያ ውስጥ ወጣት ብሎም ሰላም የሚባል ነገር ይኖር ነበር?? ሌላ ብዙ ማሳያ መፃፍ ይቻላል ለዛሬ ግን እዚህ ላይ ላብቃ።ይሄ ሁሉ ችግር ስዘረዝር እንዳፈራ የሀገራችን አምላክ አይተኛም ሀገራችንን ይጠብቃታል!!!
አፍሪቃውያን የኢትዮጵያ አምላክ ቸርች እስከመገንባት ደርሰው ነበር
ክብር ከብረው ላስከበሩን ጀግኖች አያት አባቶቻችን!!!
ሞተው ላኖሩን ጀግኖች ማርያምን!!!!!
ተቆራርጦ ስለደረሰህ በጣም ይቅርታ ቢያልፍም መልካም መቶ ሀያኛ የአድዋ ድል ይሁንልን!!!!!
👇👇👇👇
ስላም እንደት ነህ/ሽ
"አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?" የሚል ጥያቄ አንስተህ/ሽ እንድንወያይ ስለጋበዛችሁን አመሰግናለሁ።
እኔ አዎ በሚገባ ባይ ነኝ፡፡ ነገር ግን በእኔ አቅም ሊብራራ የማይችል ሲሆን የተቻለኝን ልሞክር
መጀመሪያ ፈጣሪ እንዲረዳን በእርሱ ማመን እና እርሱን የምንፈልገዉን መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ምሳሌ እኔ ከራበኝ ምግብ እንዲሰጡኝ ቤተሰቦቼን መጠየቅ አለብኝ፡፡ ስለዚህ ፈጣሪ እንዲረዳቸዉ ሌሎችም እንደ እምየ ምኒልክ አምነዉ መጠየቅ አለባቸዉ፡፡ ክርስቶስ ለኛ ነጻ ፈቃድ ነዉ የሰጠን፡፡ 38 ዓመት የአልጋ ቁራኛ የነበረዉን ወጣት ሲያድነዉ ዝም ብሎ ተነስ አልጋህን ተሸክመኅ ሒድ አላለዉም መጀመሪያ መዳን እንደሚፈልግ ከጠየቀ በኋላ አዳነዉ እንጅ፡፡ ስለዚህ እኛም እንዲረዳን መጠየቅ አለብን፡፡ የእምየ ምንሊክን የክተት አዋጅ ስናይ እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፋፍቶ አኖረኝ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ” በዚህ ዉስጥ ስንመለከት እስካሁንም እምየ ስልጣን ላይ የቆዩት በእርሳቸዉ ሀይል ብቻ ሳይሆን በፈጣሪም ቸርነት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ይቀጥሉ እና ”……….. ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብየ አልጠራጠርም” በዚህ ዉስጥ ደግሞ እምየ ፈጣሪን ይዘዉ ጦርነቱን እንደሚያሸንፉ ምንም ጥርጣሬ የላቸዉም፡፡ ይሄንንም እራሳቸዉ ጣሊያኖች ”አንድ ሰዉ በነጭ ፍረስ ሆኖ ፈጀን ከፊታቸዉ አላስደርሰን አለ” ብለዉ መጽሀፋቸዉ ላይ እንደጻፉ ይነገራል፡፡ በዚህ ዉስጥ ደሞ እምየ ምኒልክ የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ይዘዉ እንደዘመቱ ይታወቃል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረስ ደግሞ ነጭ ነዉ፡፡ ስለዚህ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ አብሮ አድዋ ላይ ተዋግትዋል፡፡ እንግዲህ እናንተ በጎደል ሙሉበት ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡
👇👇👇👇
አሁን ያነ ሳሀቸው ሀ ሳቦች እውነትም እንደጠየቅከው አይነት ጥያቄ ጭንቅላት ውስጥ ያጭራሉ....
ግን ምን አለ መሰለህ......
አዎ አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ አይን ያያታል
ለምን አልሽ ካልክ .... ያልኩበትን ሰበብ ልዘርዝር
1.ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደስጦታ ሲሰጣት(ያስራት ሀገርሽ ብሎ) "ሳያዩ የሚያምኑ ህዝቦች የሚኖሩባት ምድር ናት" ብሎ ራሱ መስክሮልናል
2. ትንቢተ አሞፅ ላይ "እናንት የእስራኤል ልጆች ሆይ ለኔ እንደኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን"ብሎ ምን ያህል እንደሚወደን መስክሯል
3.አምላክ ነጋ ጠባ የሚመሰገንባት አገር ናት... ሙስሊሙ ክርስትያኑ ፕሮቴስታንቱ ጆሆባው ሌላውም... ሳያመሰግን አይውልም አያድርም
ምሳሌ ልስጥህ... ሰንበት ሰንበት ይቀደሳል... አርብ አርብ ጁማ ነው... አለመግባባት ላይ "በህግ አምላክ!" ይባላል.... ስላምታ ላይ "እግዛብሔር ይመስገን" " አላህ ይመስገን" ይባላል... ሌላው የገዳማውያን ፀሎትም አይረሳም
4. "ኢትዮጵያ ታበፅዕ እደዊሀ ኀበ እግዚአብሔር" (እጇን ወደ እግዛብሔር ትዘረጋለች) ተብሎላታልም....
ስብዕናችን #Humanity
🗣🗣ጉዞ ወደ ሀሳብ.......... በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል " አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም…
1ኛ ,3ኛ እና 4ኛ ማስረጃዎች (አንድ በል).... ......
አለም ሁሉ አምላክ የለም ወደ ማለት በደረሰበት በዚ ግዜ ሳይታጎል ሚመሰገንበትን ሕዝብናምድርን በተለየ አይን ማየቱ (ሁለተኛ) የአምላካዊ ባህሪውን ይሸረሽረል ብዬ አላምን...... ህጉን የጠበቀ ነውና በረከቱን የሚያገኘው
ሌላው ደግሞ ይኼን ክፉ ወረርሽኝ እንመልከት..... በውጭ ያሉ ወገኖች ሲረፈረፉ የኛ ወገን እንደተፈራው ያልተረፈረፈው በምን ይመስልሀል??? ...ተጠንቅቀን?... ነጭሽንኩርቱ??.. ወይስ... በምትሀት??? .... በአምላክ ልዩ ጥበቃ ነው
ሌላም ላምጣልህ.... እቺ ማነች... ሶርያ.... እና ሌሎችም ማላስታውሳቸው ሀገሮች አይፈርሱም የተባሉት ይኸው ብትንትናቸው ወጥቶ የለም እንዴ... እኛስ እስካሁን በቋፍ ቢሆንም ተ ሰብስበን ያለነው በምናችን ነው??? እጃችንን በምዘረጋለት በጠባቂያችን አይደለምን??
ሰው በሰው ላይ ...መንግስት በመንግስት ላይ... ወንድም በወንድም... ህዝብ በህዝብ...ላይ የመነሳቱ ጉዳይ.... ይህ የጊዜው ጉዳይ ነው.... በመፅሀፉም በግልፅ እንዳለው የግዜው መክፋት የፍፃሜው መቃርቢያ ምልክት ነው....
ደግሞ....
ኢትዮጵያውንያን ከማንም በላይ በማመን ይታወቃሉ! ያመነ ደግሞ ይሆንለታል! ይድናል! በ23 ብንዋጋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይረዳናል ብለው ስላመኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረዳቸው. ዳኑ! አበቃ!
ይህ የኔ ሀሳብ ነው! ብዙ እውቀት የለኝም ግን የተሰማኝን ከማውቀው አንፃር ገልጫለው... የተሳሳትኩት ካለ ልታረም ዝግጁ ነኝ...
👇👇👇👇
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን በርሱ አምነው እንደ ሃሳቡ ለሚጓዙ ሁሉ ሊራዳ ይመጣል። ይህን አሳብ በደንብ ለመረዳት የእስራኤልን ታሪክ (በብሉይ ኪዳን ያለውን) ማንበብ ይረዳል። በርሱ ስታምን እርሱም ይታመናል በኃይልህ እና በጉልበትህ ስትታመን ደግሞ ለኃይልህ እና ለጉልበትህ አሳልፎ ይሰጥሃል በጉልበትህ ልክ ትዋጋለህ። እስራኤልን በኤርትራ ባህር አሳልፎ ፈርኦንና ሰራዊቱን ሲያሰጥም ብቸኛው ልዩነት እምነታቸው ነው። እኒህ በርሱ ኃይል እነዚህ በሠራዊት ብዛት ። ከመንገዱ ፈቅ ባሉ ጊዜ ደግሞ ከነርሱ በሚያንስ ሠራዊት ሲረቱም አይተናል። the bottom line is እግዚአብሔር ይረዳል። ይህም ፍትሃዊነቱን አያዛባም። ተበዳይ እና በዳይ መካከል ያለውን ልዩነት እንኳን እሱ እኛ እንረዳለን።
ሌላው መልአክ በፈረስ መጣ የሚል ታሪክ የለንም። ይልቁንም ጊዮርጊስ የሚባል ሰማእት በምልጃው ተራዳን ነው የሚባለው። በነገርህ ላይ እርሱም ሮማዊ ነው። ለዘር ሳይሆን ግን ለእውነት እና ለእምነት አድልቷል። ደግሞ ሰይፍ ይዞ ተዋጋ ማለት ሳይሆን ለሚዋጉት ብርታት ሆናቸው ማለት ነው።
ለምን በሁለተኛው ጦርነት አልመጣም ላልከው ከላይ ያወራነው በደንብ የሚያስረዳ ይመስለኛል። በእምነታችን ልክ ይረዳናል። ትንሽነታቸውን አምነው እርሱን ተስፋ አድርገው ተኳሽ ወታደርና ቀዳሽ ካህን ይዘው በወጡ ጊዜ ጉልበት ሆናቸው። በተቃራኒው የአውሮፓ ኅብረትን አምነው እጃቸውን ወደነርሱ በዘረጉ ጊዜ ደግሞ ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጣቸው።
Anyways ይህን ሁሉ ለመርዳት አማኝ መሆን ሳያስገልግ አይቀርም።
የሌሎቻቹን መርጠን የምናቀርብ ይሆናል!
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
አለም ሁሉ አምላክ የለም ወደ ማለት በደረሰበት በዚ ግዜ ሳይታጎል ሚመሰገንበትን ሕዝብናምድርን በተለየ አይን ማየቱ (ሁለተኛ) የአምላካዊ ባህሪውን ይሸረሽረል ብዬ አላምን...... ህጉን የጠበቀ ነውና በረከቱን የሚያገኘው
ሌላው ደግሞ ይኼን ክፉ ወረርሽኝ እንመልከት..... በውጭ ያሉ ወገኖች ሲረፈረፉ የኛ ወገን እንደተፈራው ያልተረፈረፈው በምን ይመስልሀል??? ...ተጠንቅቀን?... ነጭሽንኩርቱ??.. ወይስ... በምትሀት??? .... በአምላክ ልዩ ጥበቃ ነው
ሌላም ላምጣልህ.... እቺ ማነች... ሶርያ.... እና ሌሎችም ማላስታውሳቸው ሀገሮች አይፈርሱም የተባሉት ይኸው ብትንትናቸው ወጥቶ የለም እንዴ... እኛስ እስካሁን በቋፍ ቢሆንም ተ ሰብስበን ያለነው በምናችን ነው??? እጃችንን በምዘረጋለት በጠባቂያችን አይደለምን??
ሰው በሰው ላይ ...መንግስት በመንግስት ላይ... ወንድም በወንድም... ህዝብ በህዝብ...ላይ የመነሳቱ ጉዳይ.... ይህ የጊዜው ጉዳይ ነው.... በመፅሀፉም በግልፅ እንዳለው የግዜው መክፋት የፍፃሜው መቃርቢያ ምልክት ነው....
ደግሞ....
ኢትዮጵያውንያን ከማንም በላይ በማመን ይታወቃሉ! ያመነ ደግሞ ይሆንለታል! ይድናል! በ23 ብንዋጋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይረዳናል ብለው ስላመኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረዳቸው. ዳኑ! አበቃ!
ይህ የኔ ሀሳብ ነው! ብዙ እውቀት የለኝም ግን የተሰማኝን ከማውቀው አንፃር ገልጫለው... የተሳሳትኩት ካለ ልታረም ዝግጁ ነኝ...
👇👇👇👇
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን በርሱ አምነው እንደ ሃሳቡ ለሚጓዙ ሁሉ ሊራዳ ይመጣል። ይህን አሳብ በደንብ ለመረዳት የእስራኤልን ታሪክ (በብሉይ ኪዳን ያለውን) ማንበብ ይረዳል። በርሱ ስታምን እርሱም ይታመናል በኃይልህ እና በጉልበትህ ስትታመን ደግሞ ለኃይልህ እና ለጉልበትህ አሳልፎ ይሰጥሃል በጉልበትህ ልክ ትዋጋለህ። እስራኤልን በኤርትራ ባህር አሳልፎ ፈርኦንና ሰራዊቱን ሲያሰጥም ብቸኛው ልዩነት እምነታቸው ነው። እኒህ በርሱ ኃይል እነዚህ በሠራዊት ብዛት ። ከመንገዱ ፈቅ ባሉ ጊዜ ደግሞ ከነርሱ በሚያንስ ሠራዊት ሲረቱም አይተናል። the bottom line is እግዚአብሔር ይረዳል። ይህም ፍትሃዊነቱን አያዛባም። ተበዳይ እና በዳይ መካከል ያለውን ልዩነት እንኳን እሱ እኛ እንረዳለን።
ሌላው መልአክ በፈረስ መጣ የሚል ታሪክ የለንም። ይልቁንም ጊዮርጊስ የሚባል ሰማእት በምልጃው ተራዳን ነው የሚባለው። በነገርህ ላይ እርሱም ሮማዊ ነው። ለዘር ሳይሆን ግን ለእውነት እና ለእምነት አድልቷል። ደግሞ ሰይፍ ይዞ ተዋጋ ማለት ሳይሆን ለሚዋጉት ብርታት ሆናቸው ማለት ነው።
ለምን በሁለተኛው ጦርነት አልመጣም ላልከው ከላይ ያወራነው በደንብ የሚያስረዳ ይመስለኛል። በእምነታችን ልክ ይረዳናል። ትንሽነታቸውን አምነው እርሱን ተስፋ አድርገው ተኳሽ ወታደርና ቀዳሽ ካህን ይዘው በወጡ ጊዜ ጉልበት ሆናቸው። በተቃራኒው የአውሮፓ ኅብረትን አምነው እጃቸውን ወደነርሱ በዘረጉ ጊዜ ደግሞ ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጣቸው።
Anyways ይህን ሁሉ ለመርዳት አማኝ መሆን ሳያስገልግ አይቀርም።
የሌሎቻቹን መርጠን የምናቀርብ ይሆናል!
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras
❤️የፍቅር ቦታው ልብ ነው። ልብ ደግሞ ንፁህ ወርቅ ነው። ፈጣሪ በመለኮታዊ ሃይሉ ያነጠፈው፤ ያብረቀረቀው ወርቅ ቢኖር ልብ ነው።
❤️የፍቅር ፀዳል ውበት የሚንፀባረቀው በልብ መስታወት ውስጥ ነው። ነፀብራቁ፣ ደግሞ፣ በፈጣሪ ፍቅር፣ ይገለፃል።
ውብ አዳር❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
❤️የፍቅር ፀዳል ውበት የሚንፀባረቀው በልብ መስታወት ውስጥ ነው። ነፀብራቁ፣ ደግሞ፣ በፈጣሪ ፍቅር፣ ይገለፃል።
ውብ አዳር❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ለጁምኣችን!
💚
ከዕውቀት አይነቶች በላጩ «ልክህን ማወቅ» ነው እራስን መሆን፤ እራስን መግዛት ፤እራስን ማክበር ፤ራስን ማሸነፍ ፤ እራስን ማወቅ የድሎች ሁሉ መጀመርያ ይመስለኛል።ራስን ማሸነፍ ባላንጣን ከማሸነፍ በላይ ጀግና ያስደርጋል።
ሌሎች ነገሮችን ከመርታት የራስን ፍላጎት ማሸነፍ እውነተኛው ጀግንነት ነው።" አቅም ሲኖርህ ከራስህ ትወዳደራለህ። ራስህን ትተቻለህ። ከትናንትህ መሻልህን ትመዝናለህ። ዋናው የምታስብበት ቦታ ፣ የምትመኘው ሆነ መድረስ የምትፈልግበት ቦታ አለመድረስህ
አያደለም ትልቁ ነጥብ ያለው # የነበርክበት ቦታ አለመገኘትህ ነው። ጉዞ የጀመረ ይደርሳል።ግን እንዳትረሳ "ልክህን ማወቅ ለመንገድህ ጠቃሚ ነው"
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta
💚
ከዕውቀት አይነቶች በላጩ «ልክህን ማወቅ» ነው እራስን መሆን፤ እራስን መግዛት ፤እራስን ማክበር ፤ራስን ማሸነፍ ፤ እራስን ማወቅ የድሎች ሁሉ መጀመርያ ይመስለኛል።ራስን ማሸነፍ ባላንጣን ከማሸነፍ በላይ ጀግና ያስደርጋል።
ሌሎች ነገሮችን ከመርታት የራስን ፍላጎት ማሸነፍ እውነተኛው ጀግንነት ነው።" አቅም ሲኖርህ ከራስህ ትወዳደራለህ። ራስህን ትተቻለህ። ከትናንትህ መሻልህን ትመዝናለህ። ዋናው የምታስብበት ቦታ ፣ የምትመኘው ሆነ መድረስ የምትፈልግበት ቦታ አለመድረስህ
አያደለም ትልቁ ነጥብ ያለው # የነበርክበት ቦታ አለመገኘትህ ነው። ጉዞ የጀመረ ይደርሳል።ግን እንዳትረሳ "ልክህን ማወቅ ለመንገድህ ጠቃሚ ነው"
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta
👍1
በዲግሪ የተመረቀ/ች
3 አመት የስራ ልምድ ያለው/ት
ብዛት 1
ላይሰንስ ያለው/ት
የስራ ቦታ እሪቼ ባቡር ፌርማታ መስከረም ማዞሪያ የድሮው መስከረም ሆቴል ፊት ለፊት
@Nagayta
3 አመት የስራ ልምድ ያለው/ት
ብዛት 1
ላይሰንስ ያለው/ት
የስራ ቦታ እሪቼ ባቡር ፌርማታ መስከረም ማዞሪያ የድሮው መስከረም ሆቴል ፊት ለፊት
@Nagayta