ድልድይ
[ዮሐንስ ተመስገን]
ተንከተም ማለት ድልድይ ማለት ነው። ድልድይ ደግሞ አገልግሎቱ መሻገሪያ ነው። ድልድይ ካለ ማዕበል አይነካም፤ የሚናውጠውን አይነካም። ጎርፍም ይሁን ቆሻሻ ቁልቁል እየተመለከቱ ያለ ፍርሃት ይሻገሩበታል።
<ተንከተም> ሊቀሊቃውንት ስምዐኮነ የኒቂያ ጉባኤን ውሳኔ ጸሎተ ሃይማኖትን ያብራሩበት መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ በተለያዩ ዘመናት የተነሡና ወደ ፊትም የሚነሡ የንስጥሮስ፤ የአርዮስ፤ የመቅዶንዮስ ... የክህደት ማዕበል አነዋውጾ እንዳያስቀር ድልድይ ሁኖ ያሻግራል። በምስጢረ ሥጋዌና በምስጢረ ሥላሴ ላይ የሚነሡ የኑ*ፋ*ቄ ጎርፎችን ከአእምሮ በታች እያሳየ በትርጓሜ ድልድይነት ያመላልሳል።
ሊቁ በክፍል ሁለት በአንቀጽ አንድ (ገጽ 62) <ነአምን በአሐዱ አምላክ> ብለው ጀመረው ገጽ 494 ላይ በአንቀጽ 12 <ወሕይወተ ዘይመጽእ ለዓለመ ዓለም> በማለት ጸሎተ ሃይማኖትን በ12 አናቅጽ ከፍለው አብራርተውታል።
ተንከተም ማንበብ ከምስጢር ጋር መዋል ነው። ምስጢረ ሥላሴንና ምስጢረ ሥጋዌን ላይ ሃይማኖተ አበውን ከኢትዮጵያውያን አበው ማብራርያ ጽሑፎች ጋራ እያዋደደ በጸሎተ ሃይማኖት ዙሪያ የማያዳግም መጽሐፍ ሁኖ ወጥቱዋል። ጸሐፊውን የማሳስበው ሌሎች እንዲህ ማብራሪያ የሚፈልጉ መጻሕፍትን እያዘጋጁ እንዲያቀርቡልን ነው። ለአሁኑ የኑፋ*ቄ ማዕበሉን በተንከተም እንድትሻገሩ ለማለት እወዳለሁ።
[ዮሐንስ ተመስገን]
ተንከተም ማለት ድልድይ ማለት ነው። ድልድይ ደግሞ አገልግሎቱ መሻገሪያ ነው። ድልድይ ካለ ማዕበል አይነካም፤ የሚናውጠውን አይነካም። ጎርፍም ይሁን ቆሻሻ ቁልቁል እየተመለከቱ ያለ ፍርሃት ይሻገሩበታል።
<ተንከተም> ሊቀሊቃውንት ስምዐኮነ የኒቂያ ጉባኤን ውሳኔ ጸሎተ ሃይማኖትን ያብራሩበት መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ በተለያዩ ዘመናት የተነሡና ወደ ፊትም የሚነሡ የንስጥሮስ፤ የአርዮስ፤ የመቅዶንዮስ ... የክህደት ማዕበል አነዋውጾ እንዳያስቀር ድልድይ ሁኖ ያሻግራል። በምስጢረ ሥጋዌና በምስጢረ ሥላሴ ላይ የሚነሡ የኑ*ፋ*ቄ ጎርፎችን ከአእምሮ በታች እያሳየ በትርጓሜ ድልድይነት ያመላልሳል።
ሊቁ በክፍል ሁለት በአንቀጽ አንድ (ገጽ 62) <ነአምን በአሐዱ አምላክ> ብለው ጀመረው ገጽ 494 ላይ በአንቀጽ 12 <ወሕይወተ ዘይመጽእ ለዓለመ ዓለም> በማለት ጸሎተ ሃይማኖትን በ12 አናቅጽ ከፍለው አብራርተውታል።
ተንከተም ማንበብ ከምስጢር ጋር መዋል ነው። ምስጢረ ሥላሴንና ምስጢረ ሥጋዌን ላይ ሃይማኖተ አበውን ከኢትዮጵያውያን አበው ማብራርያ ጽሑፎች ጋራ እያዋደደ በጸሎተ ሃይማኖት ዙሪያ የማያዳግም መጽሐፍ ሁኖ ወጥቱዋል። ጸሐፊውን የማሳስበው ሌሎች እንዲህ ማብራሪያ የሚፈልጉ መጻሕፍትን እያዘጋጁ እንዲያቀርቡልን ነው። ለአሁኑ የኑፋ*ቄ ማዕበሉን በተንከተም እንድትሻገሩ ለማለት እወዳለሁ።
ይህ ቅጂ የሌላችሁ 15 ቅጂዎች ስላሉን በ0941555550 ደውለው መያዝ ይችላሉ።
በዚሁ አጋጣሚ በቀድሞው ከቅጽ 7 - 13 አንድ ላይ አጠቃልሎ የያዘው #ቅጽ_2 በቅርቡ ታትሞ ገበያ ላይ ይውላል።
በዚሁ አጋጣሚ በቀድሞው ከቅጽ 7 - 13 አንድ ላይ አጠቃልሎ የያዘው #ቅጽ_2 በቅርቡ ታትሞ ገበያ ላይ ይውላል።