የኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ክልላዊ ውክልና 👇🏿 https://bit.ly/3Md2s7q
#ምርጫ2018'ን የሚመለከቱ ወቅታዊ እና የተረጋገጡ መረጃዎችን ለመከታተል ይህንን ገጽ ( @ethioelections ) ይከታተሉ።
#ምርጫ2018'ን የሚመለከቱ ወቅታዊ እና የተረጋገጡ መረጃዎችን ለመከታተል ይህንን ገጽ ( @ethioelections ) ይከታተሉ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ቪዲዮ፦ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለው የጸጥታ ሁኔታ በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሚኖረውን ተጽዕኖ በተመለከተ የተለያዩ ባለድርሻዎች የተሳተፉበት ውይይት ዛሬ ሰኞ ጥር 25፤ 2018 በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀው በዚህ ውይይት ላይ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ርዕሰ መስተዳድሮችና ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የጸጥታ አካላት ተገኝተዋል።
ውይይቱ በተለያዩ ስፍራዎች ያለው የጸጥታ ሁኔታ ለቀጣዩ ምርጫ “አስቻይ” መሆን ወይም አለመሆኑ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልጸዋል።
ከቦርዱ ሰብሳቢ የመክፈቻ ንግግር በኋላ ባለው ውይይት ላይ የመገናኛ ብዙሃን እንዲታደሙ አልተፈቀደም።
በዛሬው ውይይት ላይ የ11 ክልሎች እንዲሁም የድሬዳዋ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሮች የጸጥታ ሁኔታን የሚመለከት ሪፖርት እንደሚቀርብ በቦርዱ የተዘጋጀው መርሃ-ግብር ያመለክታል። ሪፖርቱ በትግራይ ክልል ያለውን የጸጥታ ሁኔታ አላካተተም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaElections / @EthiopiaInsiderNews
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀው በዚህ ውይይት ላይ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ርዕሰ መስተዳድሮችና ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የጸጥታ አካላት ተገኝተዋል።
ውይይቱ በተለያዩ ስፍራዎች ያለው የጸጥታ ሁኔታ ለቀጣዩ ምርጫ “አስቻይ” መሆን ወይም አለመሆኑ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልጸዋል።
ከቦርዱ ሰብሳቢ የመክፈቻ ንግግር በኋላ ባለው ውይይት ላይ የመገናኛ ብዙሃን እንዲታደሙ አልተፈቀደም።
በዛሬው ውይይት ላይ የ11 ክልሎች እንዲሁም የድሬዳዋ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሮች የጸጥታ ሁኔታን የሚመለከት ሪፖርት እንደሚቀርብ በቦርዱ የተዘጋጀው መርሃ-ግብር ያመለክታል። ሪፖርቱ በትግራይ ክልል ያለውን የጸጥታ ሁኔታ አላካተተም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaElections / @EthiopiaInsiderNews
በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ ለሚደረገው ሀገር አቀፍ #ምርጫ ወደ 17 ሺህ በሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል መንገድ እንደሚካሔድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ቦርዱ ይሔን ያስታወቀው ዛሬ ሰኞ ጥር 25፤ 2018 ለቀጣዩ ምርጫ የጸጥታ ሁኔታን ለመገምገም ባዘጋጀው ውይይት ላይ ነው።
በዚሁ ውይይት መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ፤ የመራጮች ምዝገባ በሶስት አይነት መንገድ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
የመጀመሪያው የተለመደው "የማኑዋል" ምዝገባ ሲሆን ሌሎቹ አሁን ቦርዱ በሚያስጀምረው አዲሱ የዲጂታል ምዝገባ የሚከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
የዲጂታል ምዘገባው "ምርጫዬ" በተሰኘ መተግበሪያ የሚከናወን እና በራስ የሚካሄደውን (self-registration) እና በምርጫ አካላት ድጋፍ የሚካሄደውን (assisted-voter registration) የሚያጠቃልል መሆኑን የቦርድ ሰብሳቢዋ ገልጸዋል፡፡
“የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚናከናወን በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሁሉም የምርጫ ክልል መተግበር አይቻልም” ብለዋል የቦርድ ሰብሳቢዋ።
“ከመሠረተ ልማት፣ በጀትና የሰው ኃይል አቅርቦት አንጻር በተለዩ ወደ 17 ሺህ የሚጠጉ የምርጫ ክልሎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገናል” ሲሉ ሜላትወርቅ ለስብሰባው ተሳታፊዎች ተናግረዋል።
ለዚህም እንዲያመች ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ (ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🟥 ይህን ጉዳይ በተመለከተ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ የሰጡትን ማብራሪያ ይህን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/lg9jfSJfH2E ተጭነው ይመልከቱ።
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
ቦርዱ ይሔን ያስታወቀው ዛሬ ሰኞ ጥር 25፤ 2018 ለቀጣዩ ምርጫ የጸጥታ ሁኔታን ለመገምገም ባዘጋጀው ውይይት ላይ ነው።
በዚሁ ውይይት መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ፤ የመራጮች ምዝገባ በሶስት አይነት መንገድ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
የመጀመሪያው የተለመደው "የማኑዋል" ምዝገባ ሲሆን ሌሎቹ አሁን ቦርዱ በሚያስጀምረው አዲሱ የዲጂታል ምዝገባ የሚከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
የዲጂታል ምዘገባው "ምርጫዬ" በተሰኘ መተግበሪያ የሚከናወን እና በራስ የሚካሄደውን (self-registration) እና በምርጫ አካላት ድጋፍ የሚካሄደውን (assisted-voter registration) የሚያጠቃልል መሆኑን የቦርድ ሰብሳቢዋ ገልጸዋል፡፡
“የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚናከናወን በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሁሉም የምርጫ ክልል መተግበር አይቻልም” ብለዋል የቦርድ ሰብሳቢዋ።
“ከመሠረተ ልማት፣ በጀትና የሰው ኃይል አቅርቦት አንጻር በተለዩ ወደ 17 ሺህ የሚጠጉ የምርጫ ክልሎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገናል” ሲሉ ሜላትወርቅ ለስብሰባው ተሳታፊዎች ተናግረዋል።
ለዚህም እንዲያመች ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ (ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🟥 ይህን ጉዳይ በተመለከተ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ የሰጡትን ማብራሪያ ይህን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/lg9jfSJfH2E ተጭነው ይመልከቱ።
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
የፌደራል መንግስት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸምን በተመለከተ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 26፤ 2018 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው የፓርላማ አባላትን ጥያቄዎችን አድምጠዋል።
ከእነዚህ የፓርላማ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ተመራጭ ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ መጪውን ምርጫ አስመልክቶ ተከታታይ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበዋል።
የፓርላማ አባሉ ጥያቄ እንደሚከተለው ቀርቧል፦
“የምርጫ ወቅት በንጽጽር ከቅድመ ምርጫ በተሻለ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚዲያ እድል የሚያገኙበት እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም በአሁኑ ወቅት ይህንን ሁኔታ በሚያሳጣ መልኩ የህዝብ መገናኛ ብዙኃን በዝምታ ውሰጥ ሆነው፤ የምርጫ ድባብ እንዳይኖር እና ሂደቱ በተቀዛቀዘ ሁኔታ የቀጠለበት ሁኔታ ስላለ ይህ የሆነበት ምክንያት ማብራሪያ ቢሰጥ?
በተጨማሪም መንግስት በግልጽ የፓርቲና የመንግስት ሥራ ልዩነትን ባለማስመሩ፤ እነዚህ ሚዲያዎች የገዢው ፓርቲ አገልጋይ ሆነዋል እስከሚባል ድረስ የገለልተኝነት ጥያቄ ይነሳባቸዋል። ስለዚህ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን የሚገልጹበት እኩል ሜዳ በሌለበት ሁኔታ የምርጫው ውድድር እንዴት ጤነኛ ሊሆን ይችላል?”
🟥 የፓርላማ አባሉን ሙሉ ጥያቄ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.facebook.com/ethioelections/posts/pfbid0du2ZLX5266ZDeDXeZ78WKjcrdX7nxnirTfWHQGiW6LBAGZ34fFfnHPhsM3Zq3X24l
[በ“ምርጫ 2018-ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተጠናቀረ]
@ethioelections/ @EthiopiaInsiderNews
ከእነዚህ የፓርላማ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ተመራጭ ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ መጪውን ምርጫ አስመልክቶ ተከታታይ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበዋል።
የፓርላማ አባሉ ጥያቄ እንደሚከተለው ቀርቧል፦
“የምርጫ ወቅት በንጽጽር ከቅድመ ምርጫ በተሻለ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚዲያ እድል የሚያገኙበት እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም በአሁኑ ወቅት ይህንን ሁኔታ በሚያሳጣ መልኩ የህዝብ መገናኛ ብዙኃን በዝምታ ውሰጥ ሆነው፤ የምርጫ ድባብ እንዳይኖር እና ሂደቱ በተቀዛቀዘ ሁኔታ የቀጠለበት ሁኔታ ስላለ ይህ የሆነበት ምክንያት ማብራሪያ ቢሰጥ?
በተጨማሪም መንግስት በግልጽ የፓርቲና የመንግስት ሥራ ልዩነትን ባለማስመሩ፤ እነዚህ ሚዲያዎች የገዢው ፓርቲ አገልጋይ ሆነዋል እስከሚባል ድረስ የገለልተኝነት ጥያቄ ይነሳባቸዋል። ስለዚህ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን የሚገልጹበት እኩል ሜዳ በሌለበት ሁኔታ የምርጫው ውድድር እንዴት ጤነኛ ሊሆን ይችላል?”
🟥 የፓርላማ አባሉን ሙሉ ጥያቄ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.facebook.com/ethioelections/posts/pfbid0du2ZLX5266ZDeDXeZ78WKjcrdX7nxnirTfWHQGiW6LBAGZ34fFfnHPhsM3Zq3X24l
[በ“ምርጫ 2018-ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተጠናቀረ]
@ethioelections/ @EthiopiaInsiderNews
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለፓርላማ አባልነት በድጋሚ እንደማይወዳደሩ አስታወቁ
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን በመወከል በባህር ዳር ከተማ ምርጫ ክልል ተመርጠው ላለፈው አራት ዓመት ተኩል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቆዩት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ በመጪው ምርጫ እንደማይወዳደሩ አስታወቁ። ዶ/ር ደሳለኝ ራሳቸውን ለምርጫ በዕጩነት ላለማቅረብ የወሰኑት ነጻ፣ ሰላማዊ እና ፍትሐዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል “ምቹ መደላድል ባለመኖሩ” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
የፓርላማ አባሉ ይህን የገለጹት፤ የመጪው ምርጫ ተሳትፏቸውን በተመለከተ በይፋዊ የፌስ ቡክ ገጻቸው ዛሬ አርብ ጥር 29፤ 2018 ባሰራጩት መግለጫ ነው። ዶ/ር ደሳለኝ ባለፉት ዓመታት የባህር ዳር ከተማ በመወከል፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህዝቡ “ሀቀኛ ድምጽ” በመሆን ማገልገላቸውን በመግለጫቸው ላይ ጠቅሰዋል።
በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ ለሚካሄደው ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ የተወዳዳሪዎች ምዝገባ እየተከናወነ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በዕጩነት መመዝገብ አለመመዝገባቸውን በተመለከተ “ተደጋጋሚ” ጥያቄዎች ሲቀርብላቸው እንደቆየ ዶ/ር ደሳለኝ በመግለጫቸው ላይ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፤ ጥር 1 የተጀመረው የዕጩዎች ምዝገባ ከነገ በስቲያ እሁድ ይጠናቀቃል።
ዶ/ር ደሳለኝ በመጪው ምርጫ ለመወዳደር በባህር ዳር አሊያም በአዲስ አበባ በዕጩነት እንዲቀርቡ ከ“አንዳንድ ፓርቲዎች” ዕድሉ ተሰጥቷቸው እንደነበር በዛሬው መግለጫቸው ላይ አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ከሚመሩት አመራሮች ጋር ቅራኔ ያላቸው የፓርላማ አባሉ፤ ዕድሉን የሰጧቸውን ፓርቲዎች በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። 🔴ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://bit.ly/4qFiyVP
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን በመወከል በባህር ዳር ከተማ ምርጫ ክልል ተመርጠው ላለፈው አራት ዓመት ተኩል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቆዩት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ በመጪው ምርጫ እንደማይወዳደሩ አስታወቁ። ዶ/ር ደሳለኝ ራሳቸውን ለምርጫ በዕጩነት ላለማቅረብ የወሰኑት ነጻ፣ ሰላማዊ እና ፍትሐዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል “ምቹ መደላድል ባለመኖሩ” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
የፓርላማ አባሉ ይህን የገለጹት፤ የመጪው ምርጫ ተሳትፏቸውን በተመለከተ በይፋዊ የፌስ ቡክ ገጻቸው ዛሬ አርብ ጥር 29፤ 2018 ባሰራጩት መግለጫ ነው። ዶ/ር ደሳለኝ ባለፉት ዓመታት የባህር ዳር ከተማ በመወከል፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህዝቡ “ሀቀኛ ድምጽ” በመሆን ማገልገላቸውን በመግለጫቸው ላይ ጠቅሰዋል።
በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ ለሚካሄደው ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ የተወዳዳሪዎች ምዝገባ እየተከናወነ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በዕጩነት መመዝገብ አለመመዝገባቸውን በተመለከተ “ተደጋጋሚ” ጥያቄዎች ሲቀርብላቸው እንደቆየ ዶ/ር ደሳለኝ በመግለጫቸው ላይ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፤ ጥር 1 የተጀመረው የዕጩዎች ምዝገባ ከነገ በስቲያ እሁድ ይጠናቀቃል።
ዶ/ር ደሳለኝ በመጪው ምርጫ ለመወዳደር በባህር ዳር አሊያም በአዲስ አበባ በዕጩነት እንዲቀርቡ ከ“አንዳንድ ፓርቲዎች” ዕድሉ ተሰጥቷቸው እንደነበር በዛሬው መግለጫቸው ላይ አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ከሚመሩት አመራሮች ጋር ቅራኔ ያላቸው የፓርላማ አባሉ፤ ዕድሉን የሰጧቸውን ፓርቲዎች በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። 🔴ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://bit.ly/4qFiyVP
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምዝገባ የሚያከናወኑበትን ጊዜ እስከ የካቲት 16፤ 2018 አራዘመ። ቦርዱ የምዝገባ ጊዜውን ያራዘመው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቋሙ ባዘጋጃቸው የተለያዩ መድረኮች ላይ እና በጽሁፍ ጭምር ባቀረቡት ጥያቄ መሆኑን አስታውቋል።
ምርጫ ቦርድ ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ይፋ ባደረገው የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ፤ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወነው ከጥር 1 እስከ የካቲት 1 ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነበር። በዚህ መሰረት ምዝገባው የሚጠናቀቀው ከነገ በስቲያ እሁድ ቢሆንም፤ ቦርዱ ዛሬ አርብ ጥር 29 ምሽት ባወጣው መግለጫ ለዕጩዎች የተሰጠው ጊዜ በሁለት ሳምንት መራዘሙን አመልክቷል።
ቦርዱ በዛሬው መግለጫው፤ ከዚህ ወር መጀመሪያ አንስቶ ሲካሄድ በቆየው የዕጩዎች ምዝገባ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል፤ 15 የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ በሁለት የተለያዩ ቅንጅቶች እና በአንድ ግንባር ስር ሆነው ተወዳዳሪዎችን ማስመዘገባቸውን ገልጿል። የግል ዕጩዎችም በተመሳሳይ መልኩ ምዝገባ እያከናወኑ መሆኑንም ጠቁሟል።
የዕጩዎቹ ምዝገባ ሲከናወን የቆየው፤ ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ባደረገው የዲጂታል ምዝገባ ስርዓት ነው። ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ ይፋ ይተደረገው ይህ ስርዓት “ለአካታችነት” እና “ተደራሽነት” ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ “የዕጩዎችን እና የመራጮችን ጊዜ እንደሚቆጥብ”፤ “አላስፈላጊ ምልልሶችን እንደሚያስቀር” እና “ወጪ ቆጣቢ” እንደሆነ ምርጫ ቦርዱ በወቅቱ አስታውቆ ነበር። #ምርጫ2018
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://bit.ly/46qcw3P
ምርጫ ቦርድ ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ይፋ ባደረገው የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ፤ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወነው ከጥር 1 እስከ የካቲት 1 ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነበር። በዚህ መሰረት ምዝገባው የሚጠናቀቀው ከነገ በስቲያ እሁድ ቢሆንም፤ ቦርዱ ዛሬ አርብ ጥር 29 ምሽት ባወጣው መግለጫ ለዕጩዎች የተሰጠው ጊዜ በሁለት ሳምንት መራዘሙን አመልክቷል።
ቦርዱ በዛሬው መግለጫው፤ ከዚህ ወር መጀመሪያ አንስቶ ሲካሄድ በቆየው የዕጩዎች ምዝገባ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል፤ 15 የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ በሁለት የተለያዩ ቅንጅቶች እና በአንድ ግንባር ስር ሆነው ተወዳዳሪዎችን ማስመዘገባቸውን ገልጿል። የግል ዕጩዎችም በተመሳሳይ መልኩ ምዝገባ እያከናወኑ መሆኑንም ጠቁሟል።
የዕጩዎቹ ምዝገባ ሲከናወን የቆየው፤ ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ባደረገው የዲጂታል ምዝገባ ስርዓት ነው። ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ ይፋ ይተደረገው ይህ ስርዓት “ለአካታችነት” እና “ተደራሽነት” ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ “የዕጩዎችን እና የመራጮችን ጊዜ እንደሚቆጥብ”፤ “አላስፈላጊ ምልልሶችን እንደሚያስቀር” እና “ወጪ ቆጣቢ” እንደሆነ ምርጫ ቦርዱ በወቅቱ አስታውቆ ነበር። #ምርጫ2018
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://bit.ly/46qcw3P
በሰኔ 2013 ዓ.ም በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን ወክለው የፓርላማ አባል የሆኑት ዶ/ር አበባው ደሳለው፤ በመጪው ምርጫ ኢሕአፓን ወክለው ሊወዳደሩ ነው።
የአብን የአዲስ አበባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት ዶ/ር ይህዓለም ታምሩም በተመሳሳይ መልኩ የፓርቲ ለውጥ አድርገው በመጪው ምርጫ እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ዛሬ ማክሰኞ ጥር 3፤ 2018 ማምሻውን በበይነ መረብ በሰጠው መግለጫ ሁለቱ ቀድሞ የአብን አባላት ፓርቲውን መቀላቀላቸውን ይፋ አድርጓል። በበይነ መረብ የተካሄደውን መግለጫ ከሁለቱ የምርጫ ተወዳዳሪዎች ጋር በመሆን የሰጡት፤ የኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ሚስጥረስላሴ ታምራት ናቸው።
ሁለቱ የቀድሞ የአብን አባላት ለዘንድሮው ምርጫ በእጩነት የተመዘገቡት፤ ኢሕአፓ አባል በሆነበት “ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት” በተሰኘው የፓርቲዎች ቅንጅት በኩል መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ባለፈው መስከረም ወር የተመሰረተው ይህ የፓርቲዎች ቅንጅት፤ ከኢሕአፓ በተጨማሪ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ አባል የሆኑበት ነው።
በቅንጅቱ ተካትቶ የነበረው እናት ፓርቲ፤ በዚህ የፓርቲዎች ስብስብ ውስጥ አባል መሆኑን በተመለከተ በፓርቲው ጉባኤው ከማስጸደቅ አንጻር ያላሟላው ሂደት በመኖሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እግድ ተጥሎበታል።
እናት ፓርቲ ሂደቱን ሲያሟላ የስብስቡ አምስተኛ አባል መሆን እንደሚችል ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል። #ምርጫ2018
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የአብን-የፓርላማ-አባሉ-ዶ-ር-አበባው-ደሳለ-2/
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
የአብን የአዲስ አበባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት ዶ/ር ይህዓለም ታምሩም በተመሳሳይ መልኩ የፓርቲ ለውጥ አድርገው በመጪው ምርጫ እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ዛሬ ማክሰኞ ጥር 3፤ 2018 ማምሻውን በበይነ መረብ በሰጠው መግለጫ ሁለቱ ቀድሞ የአብን አባላት ፓርቲውን መቀላቀላቸውን ይፋ አድርጓል። በበይነ መረብ የተካሄደውን መግለጫ ከሁለቱ የምርጫ ተወዳዳሪዎች ጋር በመሆን የሰጡት፤ የኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ሚስጥረስላሴ ታምራት ናቸው።
ሁለቱ የቀድሞ የአብን አባላት ለዘንድሮው ምርጫ በእጩነት የተመዘገቡት፤ ኢሕአፓ አባል በሆነበት “ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት” በተሰኘው የፓርቲዎች ቅንጅት በኩል መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ባለፈው መስከረም ወር የተመሰረተው ይህ የፓርቲዎች ቅንጅት፤ ከኢሕአፓ በተጨማሪ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ አባል የሆኑበት ነው።
በቅንጅቱ ተካትቶ የነበረው እናት ፓርቲ፤ በዚህ የፓርቲዎች ስብስብ ውስጥ አባል መሆኑን በተመለከተ በፓርቲው ጉባኤው ከማስጸደቅ አንጻር ያላሟላው ሂደት በመኖሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እግድ ተጥሎበታል።
እናት ፓርቲ ሂደቱን ሲያሟላ የስብስቡ አምስተኛ አባል መሆን እንደሚችል ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል። #ምርጫ2018
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የአብን-የፓርላማ-አባሉ-ዶ-ር-አበባው-ደሳለ-2/
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ለመጪው ምርጫ ያዘጋጀው ማኒፌስቶ በዋናነት ትኩረት ያደረገው፤ “በመግባባት፣ በመፍታት፣ በማስፋት እና በመገንባት” ላይ መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ። የምርጫ ማኒፌስቶዉ ዋነኛ እሳቤ “ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር መትጋት” እንደሆነም ገልጸዋል።
አቶ አደም ይህን የገለጹት፤ የሰባተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የማኒፌስቶ እና የምርጫ ምልክት ይፋ ባደረገበት መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 3፤ 2018 በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ ከፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዱ የሆኑት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተገኝተዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የፓርቲው የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን አመራሮች በታደሙበት በዚህ መድረክ፤ ገዢው ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ “የስንዴ ነዶ” መሆኑን ይፋ አድርጓል። ፓርቲው በባለፈው ምርጫ የተጠቀመበት ምልክት አምፖል እንደነበር ይታወሳል።
በስድስተኛው ዙር ምርጫ ወቅት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን የሚያቀርቡበት እና የሚያስወስኑበት ጊዜ በምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ተካትቶ ነበር። ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ይፋ የተደረገው የዘንድሮው ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ግን ይህ ተግባር አልተካተተም። #ምርጫ2018
🟥ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/ብልጽግና-ፓርቲ-በመጪው-ምርጫ-የሚጠቀምበ/
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
አቶ አደም ይህን የገለጹት፤ የሰባተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የማኒፌስቶ እና የምርጫ ምልክት ይፋ ባደረገበት መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 3፤ 2018 በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ ከፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዱ የሆኑት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተገኝተዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የፓርቲው የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን አመራሮች በታደሙበት በዚህ መድረክ፤ ገዢው ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ “የስንዴ ነዶ” መሆኑን ይፋ አድርጓል። ፓርቲው በባለፈው ምርጫ የተጠቀመበት ምልክት አምፖል እንደነበር ይታወሳል።
በስድስተኛው ዙር ምርጫ ወቅት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን የሚያቀርቡበት እና የሚያስወስኑበት ጊዜ በምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ተካትቶ ነበር። ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ይፋ የተደረገው የዘንድሮው ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ግን ይህ ተግባር አልተካተተም። #ምርጫ2018
🟥ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/ብልጽግና-ፓርቲ-በመጪው-ምርጫ-የሚጠቀምበ/
@ethioelections / @EthiopiaInsiderNews
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ለቀጣዩ ምርጫ በዕጩነት ካዘጋጃቸው ተወዳዳሪዎች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ ከአንድ ቀን እስር በኋላ ተፈቱ። አቶ የሺዋስ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 4፤ 2018 ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ ተፈትተው በስልክ እንዳነጋገሯቸው የኢሕአፓ ፕሬዝዳንት አቶ አብርሃም ሃይማኖት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በተለያዩ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ለረዥም ጊዜ የፖለቲካ ተሳትፎ ያላቸው አቶ የሺዋስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት፤ ትላንት ማክሰኞ ከቀኑ 8 ሰዓት ገደማ እንደነበር የኢሕአፓ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ይስሀቅ ወልዳይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ገልጸዋል። አቶ የሺዋስ የተያዙት ከመኖሪያ ቤታቸው ውጭ ባለ ስፍራ መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
ፖሊስ ፖለቲከኛውን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት ወደሚገኘው ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደወሰዳቸው ማረጋገጣቸውን ጉዳዩን ሲከታተሉ የቆዩት አቶ ይስሀቅ ተናግረዋል። ኢሕአፓ ዛሬ ረፋድ ላይ ባወጣው አጭር መግለጫ፤ በቅርቡ ፓርቲውን በተቀላቀሉት በአቶ የሺዋስ ላይ የተወሰደውን የእስር እርምጃ ተችቷል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://bit.ly/4aIPRCh
በተለያዩ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ለረዥም ጊዜ የፖለቲካ ተሳትፎ ያላቸው አቶ የሺዋስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት፤ ትላንት ማክሰኞ ከቀኑ 8 ሰዓት ገደማ እንደነበር የኢሕአፓ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ይስሀቅ ወልዳይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ገልጸዋል። አቶ የሺዋስ የተያዙት ከመኖሪያ ቤታቸው ውጭ ባለ ስፍራ መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
ፖሊስ ፖለቲከኛውን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት ወደሚገኘው ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደወሰዳቸው ማረጋገጣቸውን ጉዳዩን ሲከታተሉ የቆዩት አቶ ይስሀቅ ተናግረዋል። ኢሕአፓ ዛሬ ረፋድ ላይ ባወጣው አጭር መግለጫ፤ በቅርቡ ፓርቲውን በተቀላቀሉት በአቶ የሺዋስ ላይ የተወሰደውን የእስር እርምጃ ተችቷል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://bit.ly/4aIPRCh
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቁሳቁሶች እሸጋ መርሀ ግብርን ለመገናኛ ብዙኃን አባላት አስጎበኘ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫንና በተለይም የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ አስፈላጊ የሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን የእሸጋ መርሃ ግብር በመጪዉ እሁድ እንደሚያጠናቅቅ ገለጸ።
ቦርዱ ዛሬ የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በየኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነትና የሎጂስቲክስ አገልገሎት ቅጥር ግቢ በሚገኘዉ መጋዘን የሚካሄደውን የምርጫ ቁሳቁሶች እሸጋ መርሀ ግብርን ለመገናኛ ብዙኃን አባላት አስጎብኝቷል፡፡ ዝርዝሩን ለማንበብ 👉 https://bit.ly/3Mku4b1
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫንና በተለይም የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ አስፈላጊ የሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን የእሸጋ መርሃ ግብር በመጪዉ እሁድ እንደሚያጠናቅቅ ገለጸ።
ቦርዱ ዛሬ የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በየኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነትና የሎጂስቲክስ አገልገሎት ቅጥር ግቢ በሚገኘዉ መጋዘን የሚካሄደውን የምርጫ ቁሳቁሶች እሸጋ መርሀ ግብርን ለመገናኛ ብዙኃን አባላት አስጎብኝቷል፡፡ ዝርዝሩን ለማንበብ 👉 https://bit.ly/3Mku4b1
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ ማድረጊያ ሥነ ስርዓት ላይ ዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብ ፈረሙ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክት ማስተዋወቂያና የዕጩዎች ሥነ ምግባር ደንብ መፈራረሚያ መርሐ ግብርን ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም አካሄደ።
በመርሐ ግብሩ የመክፈቻ ንግግራቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት የዕለቱ ትልቅ ሁነት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚወዳደሩባቸውን ምልክቶች ይፋ ማድረግና ለሕዝብ ማስተዋወቅ እንደሆነ ገልጸዋል። የምርጫ ምልክት ይፋ የማድረግያ መርሐ ግብሩ ዋና ዓላማ መራጩ ሕዝብ የሚመርጠውን ለይቶ ማወቅ እንዲችል ከምርጫ ምልክቱ ጀምሮ መረዳትና ማወቅ ስላለበት መሆኑንም ሜላትወርቅ ገልጸዋል። “በተለይም ሚዲያዎች የፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት አካታችና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታስተዋውቁና እንድታሳዩ ይጠበቅባቹሃል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በመርሐ ግብሩም ቦርዱ በ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የሚካፈሉና እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ 48 የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክትና ስያሜን በቅደም ተከተል በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም የዕጩዎች ሥነ ምግባር ደንብ መፈራረሚያ መርሐ ግብር ተያይዞ ተካሄዷል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሜላትወርቅ “የሠለጠነ ምርጫ ለማካሄድ ሥርዓትና ደንብ ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህ በምርጫው የሚወዳደሩ ዕጩዎችና ፓርቲዎች የሥነ ምግባር ደንቡን መፈረማቸው አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ👉 https://ethioelections.com/የፖለቲካ-ፓርቲዎች-የመወዳደሪያ-ምልክት/
በመርሐ ግብሩ የመክፈቻ ንግግራቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት የዕለቱ ትልቅ ሁነት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚወዳደሩባቸውን ምልክቶች ይፋ ማድረግና ለሕዝብ ማስተዋወቅ እንደሆነ ገልጸዋል። የምርጫ ምልክት ይፋ የማድረግያ መርሐ ግብሩ ዋና ዓላማ መራጩ ሕዝብ የሚመርጠውን ለይቶ ማወቅ እንዲችል ከምርጫ ምልክቱ ጀምሮ መረዳትና ማወቅ ስላለበት መሆኑንም ሜላትወርቅ ገልጸዋል። “በተለይም ሚዲያዎች የፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት አካታችና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታስተዋውቁና እንድታሳዩ ይጠበቅባቹሃል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በመርሐ ግብሩም ቦርዱ በ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የሚካፈሉና እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ 48 የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክትና ስያሜን በቅደም ተከተል በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም የዕጩዎች ሥነ ምግባር ደንብ መፈራረሚያ መርሐ ግብር ተያይዞ ተካሄዷል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሜላትወርቅ “የሠለጠነ ምርጫ ለማካሄድ ሥርዓትና ደንብ ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህ በምርጫው የሚወዳደሩ ዕጩዎችና ፓርቲዎች የሥነ ምግባር ደንቡን መፈረማቸው አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ👉 https://ethioelections.com/የፖለቲካ-ፓርቲዎች-የመወዳደሪያ-ምልክት/
የኢዜማው መሪ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወንበር መጋራት አለባቸው ሲሉ አሳሰቡ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ-ኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ሀገርን ለማሻገር መጪው 7ተኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች “ወንበር የሚጋሩበት እንጂ” እንደ በፊቱ ብልጽግና ፓርቲ “99 በመቶ አሸነፍኩ” የሚልበት መሆን እንደሌለበት አሳሰቡ።ኢዜማ ትላንት የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት የዘለቀ “ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታ እና ምርጫ” በሚል ርዕስ የበይነመረብ ውይይት አካሄዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የውይይት መነሻ አቅራቢ የነበሩት የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እንዳሉት ምርጫው በ5 ዓመት አንድ ጊዜ የሚደረግ የሐይማኖታዊ በዓል ክንውን ሳይሆን “ካለንበት የፖለቲካ ውጥንቅጥ የምንወጣበት” ብቸኛው መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም “በዚህ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወንበር ተጋርተው የሚሻገሩበት እንጂ እንደድሮው ብልፀግና ፓርቲ 99 በመቶ አሸነፍኩ ብሎ መቀጠል ሀገርን ወደ ሚፈለገው እድገት አያሻግርም” በማለት አሳስበዋል።
ኢዜማ ለህዝብ ክፍት ባደረገው የበይነመረብ (የዙም) ውይይት ከደጋፊዎቹና ከተሳታፊዎች ለተነሱት በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የድርጅቱ መሪና የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ👉https://ethioelections.com/የኢዜማው-መሪ-ፕ-ር-ብርሀኑ-ነጋ-በመጪው-ሀ/
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ-ኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ሀገርን ለማሻገር መጪው 7ተኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች “ወንበር የሚጋሩበት እንጂ” እንደ በፊቱ ብልጽግና ፓርቲ “99 በመቶ አሸነፍኩ” የሚልበት መሆን እንደሌለበት አሳሰቡ።ኢዜማ ትላንት የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት የዘለቀ “ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታ እና ምርጫ” በሚል ርዕስ የበይነመረብ ውይይት አካሄዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የውይይት መነሻ አቅራቢ የነበሩት የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እንዳሉት ምርጫው በ5 ዓመት አንድ ጊዜ የሚደረግ የሐይማኖታዊ በዓል ክንውን ሳይሆን “ካለንበት የፖለቲካ ውጥንቅጥ የምንወጣበት” ብቸኛው መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም “በዚህ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወንበር ተጋርተው የሚሻገሩበት እንጂ እንደድሮው ብልፀግና ፓርቲ 99 በመቶ አሸነፍኩ ብሎ መቀጠል ሀገርን ወደ ሚፈለገው እድገት አያሻግርም” በማለት አሳስበዋል።
ኢዜማ ለህዝብ ክፍት ባደረገው የበይነመረብ (የዙም) ውይይት ከደጋፊዎቹና ከተሳታፊዎች ለተነሱት በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የድርጅቱ መሪና የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🟥ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ👉https://ethioelections.com/የኢዜማው-መሪ-ፕ-ር-ብርሀኑ-ነጋ-በመጪው-ሀ/
በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል “አከራካሪ ሆነው” የቆዩ የተባሉ አምስት የምርጫ ክልሎች፤ “የይገባኛል ጥያቄው እስከሚፈታ” ድረስ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው ለፓርላማ “በቀጥታ” ምርጫ እንዲደረግባቸው ውሳኔ ተላለፈ። ውሳኔ የተላለፈባቸው የምርጫ ክልሎች፤ ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኮረም ኦፍላ እና ራያ አላማጣ ናቸው።
እነዚህ ምርጫ ክልሎች ከሁለቱ ክልሎች ውጭ ሆነው ምርጫ እንዲካሄድባቸው ውሳኔ ያሳለፈው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው። ለምክር ቤቱ ውሳኔ መንስኤ የሆነው፤ ጥር 22፤ 2018 ይፋ የተደረገው የምርጫ ክልሎች እና ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
በዚህ ዝርዝር ላይ በሁመራ ምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎች፤ በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን፣ በሰቲት ሁመራ፣ ቃፍታ ሁመራ እና ወልቃይት ወረዳዎች የሚገኙ እንደሆነ ተጠቅሶ ነበር። በአዲ ረመጽ የምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ በትግራይ ክልል፣ ምዕራባዊ ዞን፣ በወልቃይት እና ፀገዴ ወረዳዎች ውስጥ ያሉ መሆናቸው በዝርዝሩ ላይ ሰፍሯል።
በዚሁ ክልል፣ በተመሳሳይ ዞን ውስጥ እንደሚገኝ በምርጫ ቦርድ ዝርዝር ተጠቅሶ የነበረው የፀለምቲ ምርጫ ክልል፣ በፀለምቲ ወረዳ የሚገኝ መሆኑ በሰነዱ ተመልክቷል። በትግራይ ክልል፣ ደቡብ ዞን ስር ያሉ የምርጫ ክልሎች ሆነው የተጠቀሱት ደግሞ ኦፍላ ኮረም እና አላማጣ ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/በትግራይ-ክልል-ስር-የነበሩ-አምስት-የምር/
እነዚህ ምርጫ ክልሎች ከሁለቱ ክልሎች ውጭ ሆነው ምርጫ እንዲካሄድባቸው ውሳኔ ያሳለፈው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው። ለምክር ቤቱ ውሳኔ መንስኤ የሆነው፤ ጥር 22፤ 2018 ይፋ የተደረገው የምርጫ ክልሎች እና ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
በዚህ ዝርዝር ላይ በሁመራ ምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎች፤ በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን፣ በሰቲት ሁመራ፣ ቃፍታ ሁመራ እና ወልቃይት ወረዳዎች የሚገኙ እንደሆነ ተጠቅሶ ነበር። በአዲ ረመጽ የምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ በትግራይ ክልል፣ ምዕራባዊ ዞን፣ በወልቃይት እና ፀገዴ ወረዳዎች ውስጥ ያሉ መሆናቸው በዝርዝሩ ላይ ሰፍሯል።
በዚሁ ክልል፣ በተመሳሳይ ዞን ውስጥ እንደሚገኝ በምርጫ ቦርድ ዝርዝር ተጠቅሶ የነበረው የፀለምቲ ምርጫ ክልል፣ በፀለምቲ ወረዳ የሚገኝ መሆኑ በሰነዱ ተመልክቷል። በትግራይ ክልል፣ ደቡብ ዞን ስር ያሉ የምርጫ ክልሎች ሆነው የተጠቀሱት ደግሞ ኦፍላ ኮረም እና አላማጣ ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/በትግራይ-ክልል-ስር-የነበሩ-አምስት-የምር/
እናት ፓርቲ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች ዕጩዎችን ባያቀርብም በ“ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት (ለኢትዮጵያ)” ስር ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀቱን አስታወቀ።
በመጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በአማራና ትግራይ ክልሎች ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት እጩዎቹን ማስመዝገብ ያልፈለገው እናት ፓርቲ፤ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" በተሰኘው አዲስ የፓርቲዎች ቅንጅት ውስጥ በመካተት ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን ግን እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ፓርቲው ይህን ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ያሳለፈው፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መከፋፈልን እና መብዛትን በመቀነስ፣ እንዲሁም የተበታተነውን የፖለቲካ ኃይል በማዋሃድ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለና አንድ ወጥ አማራጭ ለማቅረብ በማለም መሆኑን የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አቶ ጌትነት ወርቁ አብራርተዋል።
ከዚህ ጎን ለጎንም፣ እናት ፓርቲ ወደ አዲሱ ጥምረት ለመቀላቀል ባደረገው ሂደት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ተፈጥሮ የነበረውን የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ውክልና እና ስንብት አለመግባባት በውይይት መፍታት መቻሉ ተገልጿል። ቦርዱ ባስቀመጠው የቁጥጥር መስፈርት መሠረት ማስተካከያዎችን በማድረግና አስፈላጊውን ሂደት በማሟላት፣ ፓርቲው ከየካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ወደ ትብብሩ መመለሱ ተረጋግጧል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://ethioelections.com/እናት-ፓርቲ-በአማራ-እና-ትግራይ-ክልሎች-ዕ/
[ምርጫ 2018 - በኢትዮጵያ ኢንሳይደር]
#ምርጫ2018 #እናትፓርቲ #ኢትዮጵያ #ምርጫቦርድ #EthiopiaElection
በመጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በአማራና ትግራይ ክልሎች ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት እጩዎቹን ማስመዝገብ ያልፈለገው እናት ፓርቲ፤ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" በተሰኘው አዲስ የፓርቲዎች ቅንጅት ውስጥ በመካተት ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን ግን እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ፓርቲው ይህን ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ያሳለፈው፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መከፋፈልን እና መብዛትን በመቀነስ፣ እንዲሁም የተበታተነውን የፖለቲካ ኃይል በማዋሃድ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለና አንድ ወጥ አማራጭ ለማቅረብ በማለም መሆኑን የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አቶ ጌትነት ወርቁ አብራርተዋል።
ከዚህ ጎን ለጎንም፣ እናት ፓርቲ ወደ አዲሱ ጥምረት ለመቀላቀል ባደረገው ሂደት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ተፈጥሮ የነበረውን የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ውክልና እና ስንብት አለመግባባት በውይይት መፍታት መቻሉ ተገልጿል። ቦርዱ ባስቀመጠው የቁጥጥር መስፈርት መሠረት ማስተካከያዎችን በማድረግና አስፈላጊውን ሂደት በማሟላት፣ ፓርቲው ከየካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ወደ ትብብሩ መመለሱ ተረጋግጧል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://ethioelections.com/እናት-ፓርቲ-በአማራ-እና-ትግራይ-ክልሎች-ዕ/
[ምርጫ 2018 - በኢትዮጵያ ኢንሳይደር]
#ምርጫ2018 #እናትፓርቲ #ኢትዮጵያ #ምርጫቦርድ #EthiopiaElection
ኢዜማ ብልጽግና ፓርቲ በግዳጅ ከባለሀብቶች ገንዘብ እየሰበሰበ ነው ሲል ከሰሰ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የፓርቲው አባል ካልሆኑ ነጋዴዎችና ባለሃብቶች በአስገዳጅነት ገንዘብ እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ። ብልጽግና ፓርቲ የመንግሥትን መዋቅር በመጠቀም በየክፍለ ከተማውና በወረዳዎች በአካል በመሄድ እና በስልክ በማስፈራራት አባል ካልሆኑ ባለሀብቶች ገንዘብ እየሰበሰበ መሆኑ በኢዜማ መግለጫ ተገልጿል። ይህ ተግባር የምርጫ ህግን የሚጥስ እና ከሞራል ያፈነገጠ መሆኑን ኢዜማ አመልክቷል።
ኢዜማ ገዢው ፓርቲ ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ እና ከኢ-ዴሞክራሲያዊ አካሂዶች እንዲቆጠብ ጠይቋል። በተጨማሪም ኢዜማ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ህገወጥ ተግባር በትኩረት በመከታተል እንዲያስቆመው እና የመንግሥት ሀብት ለፓርቲ ዓላማ መዋልን በፅኑ እንዲያወግዝ አሳስቧል። ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሁሉም ፓርቲዎች በእኩልነት የሚጠቀሙበት የምርጫ ፈንድ እንዲቋቋምም ሀሳብ አቅርቧል።
[ምርጫ 2018 - በኢትዮጵያ ኢንሳይደር]
#ምርጫ2018 #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ብልጽግና_ፓርቲ #EthiopiaElection
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የፓርቲው አባል ካልሆኑ ነጋዴዎችና ባለሃብቶች በአስገዳጅነት ገንዘብ እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ። ብልጽግና ፓርቲ የመንግሥትን መዋቅር በመጠቀም በየክፍለ ከተማውና በወረዳዎች በአካል በመሄድ እና በስልክ በማስፈራራት አባል ካልሆኑ ባለሀብቶች ገንዘብ እየሰበሰበ መሆኑ በኢዜማ መግለጫ ተገልጿል። ይህ ተግባር የምርጫ ህግን የሚጥስ እና ከሞራል ያፈነገጠ መሆኑን ኢዜማ አመልክቷል።
ኢዜማ ገዢው ፓርቲ ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ እና ከኢ-ዴሞክራሲያዊ አካሂዶች እንዲቆጠብ ጠይቋል። በተጨማሪም ኢዜማ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ህገወጥ ተግባር በትኩረት በመከታተል እንዲያስቆመው እና የመንግሥት ሀብት ለፓርቲ ዓላማ መዋልን በፅኑ እንዲያወግዝ አሳስቧል። ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሁሉም ፓርቲዎች በእኩልነት የሚጠቀሙበት የምርጫ ፈንድ እንዲቋቋምም ሀሳብ አቅርቧል።
[ምርጫ 2018 - በኢትዮጵያ ኢንሳይደር]
#ምርጫ2018 #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ብልጽግና_ፓርቲ #EthiopiaElection
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ አምስት የምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልል ውጭ ሆነው በቀጥታ የፓርላማ ምርጫ እንዲካሄድባቸው በተላለፈው ውሳኔ ላይ ጊዜያዊ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ። ፍርድ ቤቱ እግዱን ያስተላለፈው ከዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ የቀረበውን የእግድ አቤቱታ ተከትሎ ነው።
ስምረት ፓርቲ አቤቱታውን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው በፕሬዝዳንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል ነው። ዛሬ ሐሙስ የካቲት 19፤ 2018 ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ለቀረበው አቤቱታ ተከሳሽ ወይም ተጠሪ የተደረገው ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑን አቶ ጌታቸው በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ያጋሩት የፍርድ ቤት ሰነድ አመልክቷል።
ምርጫ ቦርድ በፍርድ ቤት አቤቱታ የቀረበበት፤ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል “አከራካሪ ሆነው” የቆዩ የተባሉ አምስት የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ይፋ ባደረገው ውሳኔ ነው። እነዚህ የምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኮረም ኦፍላ እና ራያ አላማጣ ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የምርጫ-ቦርድ-ውሳኔ-በፍርድ-ቤት-ጊዜያዊ-እ/
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
ስምረት ፓርቲ አቤቱታውን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው በፕሬዝዳንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል ነው። ዛሬ ሐሙስ የካቲት 19፤ 2018 ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ለቀረበው አቤቱታ ተከሳሽ ወይም ተጠሪ የተደረገው ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑን አቶ ጌታቸው በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ያጋሩት የፍርድ ቤት ሰነድ አመልክቷል።
ምርጫ ቦርድ በፍርድ ቤት አቤቱታ የቀረበበት፤ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል “አከራካሪ ሆነው” የቆዩ የተባሉ አምስት የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ይፋ ባደረገው ውሳኔ ነው። እነዚህ የምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኮረም ኦፍላ እና ራያ አላማጣ ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የምርጫ-ቦርድ-ውሳኔ-በፍርድ-ቤት-ጊዜያዊ-እ/
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተስፋና ስጋት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመጪው 7ተኛ ሀገራዊ ምርጫ የዲጂታል መራጮች ምዝገባ ስርዓት ሊተገበር መሆኑን ማስታወቁን ተከትሎ፣ ይህ አዲስ አሰራር ከሚሰጠው ተስፋ ጎን ለጎን ስጋትንም ፈጥሯል። ቦርዱ ቴክኖሎጂው ሂደቱን ለማቀላጠፍ፣ ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚረዳ ይፋ ቢያደርግም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ግን በቅርቡ ባጠናቀቁት የዕጩዎች ዲጂታል ምዝገባ ላይ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በመጥቀስ ስጋት እንዳላቸው ይገልጻሉ።
ፓርቲዎቹ እንደሚሉት፣ የዕጩዎች ምዝገባ ላይ የነበረው የሲስተም እና የኢንተርኔት ተደራሽነት ችግር እንዲሁም የማጽደቅ ሂደቱ መዘግየት ከፍተኛ የጊዜና የሀብት ብክነት አስከትሏል። በመሆኑም በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮችን በዲጂታል ለመመዝገብ መታቀዱ ተመሳሳይ እንቅፋቶች እንዳይፈጠሩ ሰፊ ዝግጅትና የሙከራ ስራዎች መከናወን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በዓለም አቀፍ ተሞክሮ መሰረትም የዲጂታል ምዝገባ ማጭበርበርን ለመከላከል ቢረዳም፣ ከሳይበር እና የግል መረጃ ደህንነት ጋር የተያያዙ ስጋቶችን በአግባቡ ታሳቢ ማድረግ እንደሚገባ ጥናቶች ያሳስባሉ።
🔴ሙሉ ትንታኔውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የዲጂታል-የመራጮች-ምዝገባ-ተስፋና-ስጋት/
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection #digitalregistration
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመጪው 7ተኛ ሀገራዊ ምርጫ የዲጂታል መራጮች ምዝገባ ስርዓት ሊተገበር መሆኑን ማስታወቁን ተከትሎ፣ ይህ አዲስ አሰራር ከሚሰጠው ተስፋ ጎን ለጎን ስጋትንም ፈጥሯል። ቦርዱ ቴክኖሎጂው ሂደቱን ለማቀላጠፍ፣ ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚረዳ ይፋ ቢያደርግም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ግን በቅርቡ ባጠናቀቁት የዕጩዎች ዲጂታል ምዝገባ ላይ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በመጥቀስ ስጋት እንዳላቸው ይገልጻሉ።
ፓርቲዎቹ እንደሚሉት፣ የዕጩዎች ምዝገባ ላይ የነበረው የሲስተም እና የኢንተርኔት ተደራሽነት ችግር እንዲሁም የማጽደቅ ሂደቱ መዘግየት ከፍተኛ የጊዜና የሀብት ብክነት አስከትሏል። በመሆኑም በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮችን በዲጂታል ለመመዝገብ መታቀዱ ተመሳሳይ እንቅፋቶች እንዳይፈጠሩ ሰፊ ዝግጅትና የሙከራ ስራዎች መከናወን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በዓለም አቀፍ ተሞክሮ መሰረትም የዲጂታል ምዝገባ ማጭበርበርን ለመከላከል ቢረዳም፣ ከሳይበር እና የግል መረጃ ደህንነት ጋር የተያያዙ ስጋቶችን በአግባቡ ታሳቢ ማድረግ እንደሚገባ ጥናቶች ያሳስባሉ።
🔴ሙሉ ትንታኔውን ለማንበብ ➡️ https://ethioelections.com/የዲጂታል-የመራጮች-ምዝገባ-ተስፋና-ስጋት/
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection #digitalregistration
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በዋትስአፕ መተግበሪያ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የተቀናጁ የጠለፋ ጥቃቶች አሉ በማለት የጥንቃቄ መልዕክት አስተላለፈ
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተለይም 7ተኛውን ሀገራዊ የምርጫ ሂደትን ተገን በማድረግ፣ ዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን ኢላማ ያደረጉ ጠላፊዎች ሰፊ የሳይበር ጥቃት እየፈጸሙ እንደሚገኙ አስተዳደሩ በሚደርሱት መረጃዎችና የሳይበር ደህንነት ትንተናዎች ማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል፡፡
ይህ ጥቃት በተለይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ተማሪዎችን፣ በርቀት ሆነዉ በዲጂታል አማራጮች የሚማሩ ግለሰቦችን እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ፣ መላው የዋትሳፕ ተጠቃሚ ማህበረሰብ የጥቃት ስልቶችና የመከላከያ መንገዶች በማወቅ እንዲጠነቀቅ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የባለ 6-አሃዝ ኮድ ለዋትስአፕ ተጠቃሚዎች በመላክ የምርጫ ደጋፊ በመምሰል፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደጋፊ በሚመስል መልኩ የፓርቲዎችን አርማ (Logo) በመጠቀም፣ የምርጫ መረጃ አቅራቢ በመምሰል፣
▶️ "ለፓርቲያችን ድጋፍዎን እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን ይግለጹ" ፣
▶️"የምርጫ ቅስቀሳ ቡድናችንን ይቀላቀሉ" ፣
▶️ "የምርጫ ጣቢያዎትን ለማወቅ"፣
▶️ "የዕጩዎችን ዝርዝር ለማየት" ወይም
▶️ "የምርጫ ውጤቶችን በቅድሚያ ለማግኘት" የሚሉ አሳሳች ማስፈንጠሪያዎችን (Links) በመጠቀም የተጠቃሚዎችን የዋትስአፕ አካውንት በቁጥጥራቸው ስር እያዋሉ እንደሚገኙም አስተዳደሩ ገልጿል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተለይም 7ተኛውን ሀገራዊ የምርጫ ሂደትን ተገን በማድረግ፣ ዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን ኢላማ ያደረጉ ጠላፊዎች ሰፊ የሳይበር ጥቃት እየፈጸሙ እንደሚገኙ አስተዳደሩ በሚደርሱት መረጃዎችና የሳይበር ደህንነት ትንተናዎች ማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል፡፡
ይህ ጥቃት በተለይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ተማሪዎችን፣ በርቀት ሆነዉ በዲጂታል አማራጮች የሚማሩ ግለሰቦችን እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ፣ መላው የዋትሳፕ ተጠቃሚ ማህበረሰብ የጥቃት ስልቶችና የመከላከያ መንገዶች በማወቅ እንዲጠነቀቅ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የባለ 6-አሃዝ ኮድ ለዋትስአፕ ተጠቃሚዎች በመላክ የምርጫ ደጋፊ በመምሰል፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደጋፊ በሚመስል መልኩ የፓርቲዎችን አርማ (Logo) በመጠቀም፣ የምርጫ መረጃ አቅራቢ በመምሰል፣
▶️ "ለፓርቲያችን ድጋፍዎን እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን ይግለጹ" ፣
▶️"የምርጫ ቅስቀሳ ቡድናችንን ይቀላቀሉ" ፣
▶️ "የምርጫ ጣቢያዎትን ለማወቅ"፣
▶️ "የዕጩዎችን ዝርዝር ለማየት" ወይም
▶️ "የምርጫ ውጤቶችን በቅድሚያ ለማግኘት" የሚሉ አሳሳች ማስፈንጠሪያዎችን (Links) በመጠቀም የተጠቃሚዎችን የዋትስአፕ አካውንት በቁጥጥራቸው ስር እያዋሉ እንደሚገኙም አስተዳደሩ ገልጿል።
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection
😁1