Ethio A+
255 subscribers
211 photos
10 videos
203 files
98 links
A+ is Possible!
Feel free to ask and give any suggestion!
@EthioAplus_admin

https://youtube.com/@ethioa_plus?si=DekKjJasKzd5Oaq-
Download Telegram
ይህንን ጥረት ከግብ ለማድረስም በቀጣይ ወር በሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ከዚህ ቀደም የተማራቸውን ትምህርቶች ወደ ኋላ መለስ  ብሎ በመከለስ ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል።

ሌላኛዋ የካምፓሱ ተማሪ ሰሎሜ ታደሰ በፈተናው ውጤታማ እንድንሆን መምህራኖቻችን ጥያቄዎችን እንድንሰራ በማድረግና በሌሎች በሚያስፈልጉን ነገሮች  እየደገፉን ይገኛሉ ብላለች።

ፈተናው እየተቃረበ በመምጣቱ በእውቀትም በስነ-ልቦናም ብቁ ለመሆን ጥረቷን እንደምታጎለብት ገልፃለች።

ተማሪ አማኑኤል በበኩሉ፥ተፈታኞች ራሳቸውን በሚገባው ልክ በማዘጋጀትና በመፈተሽ ለላቀ ውጤት ዝግጁ መሆን አለባቸው ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

የኮከበ ፅባህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደለለኝ አስማረ  በበኩላቸው፥ ትምህርት ቤቱ በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 632 የቀን 63 የማታ ተማሪዎችን ያስፈትናል ብለዋል።

ትምህርት ቤቱም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው በሚፈለገው ደረጃ እንዲዘጋጁ ለማድረግ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲወስዱ እና ተፈታኞች በግቢው እያደሩ ማጥናት የሚችሉበት ሁኔታ ማመቻቸቱን ተናግረዋል።

ተፈታኝ ተማሪዎቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚፈተኑ መሆናቸውን  በማንሳት በተለይም በበይነ መረብ ለሚፈተኑ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በኮምፕዩተር ልምምድ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ምክትል ርዕሰ መምህር አብርሃም ድሪባ፥ ካምፓሱ በሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ፈተና 80 ተማሪዎችን እንደሚያስፈትን አስታውቀዋል።

ተማሪዎቹም ለረጅም ዓመታት በትምህርት ዓለም ያደረጉት ጉዞ ፍሬያማ እንዲሆን የተለያዩ ሞዴል ፈተናዎችን እየወሰዱ እንደሚገኙ አንስተው፥ ይህም እስከ ፈተናው መዳረሻ ይቀጥላል ነው ያሉት።

@ethioaplus
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለመውሰድ መመዝገባቸው ተገለጸ!

በ2017 የትምህርት ዘመን ከ608 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ፡፡የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ መልቀቂያ ፈተና የፈተና ስርቆትና ኩረጃ በሚቀንስ መልኩ በወረቀት እና በበየነ መረብ ይሰጣል።

በወረቀት የሚፈተኑት መሰረተ ልማት ያልተሟላባቸው፤ ኮምፒውተር እና ኢንተርኔት ኮኔክሽን በበቂ ባላገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ተፈታኞች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ዋና ዳይሬክተሩ፤ በበየነ መረብ የሚሰጠው ፈተና እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ወደፊት ሙሉ በሙሉ ፈተናውን በበየነ መረብ ለመስጠት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የፈተና ዝግጅቱ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በመግለጽ፤ ፈታኞችን የመመልመል፤ የተመለመሉት ወደዬመፈተኛ ጣቢያው እንዲሰማሩ የማድረግ ዝግጅት እየተካሄደ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡በአማራ ክልል ባለው ግጭት ሳቢያ በርካታ ት/ቤቶች የዘንደሮውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደማያስፈትኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ እየሩስ መንግሥቱ በቅርቡ ገልጸዋል።

በክልሉ በአጠቃላይ 685 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙ የገለጹት ኃላፊዋ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የዘንድሮውን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የሚያስፈትኑ ትምህርት ቤቶች 470 ብቻ ናቸው ብለዋል።

ክልሉ ቀደም ባሉት ዓመታት በየዓመቱ ከ150 ሺህ እስከ 180ሺህ ተማሪዎችን የማስፈተን አቅም እንደነበረው የገለጹት ኃላፊዋ ሰላም ባለባቸው አከባቢዎች በሚገኙ ት/ቤቶች የሚገኙ 99ሺህ 880 ተማሪዎች የዘንድሮን ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል ሲሉ ተናግረዋል።


@ethioaplus
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወሰዱ ተማሪዎች ለቅድመ ዝግጅት የሞዴል ፈተና እየተሠጠ መሆኑ ተገለጸ

ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወሰዱ ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲሰሩ እና ተማሪዎች 'ምን ያህል ተዘጋጅተዋል?'የሚለውን ለማወቅ፤ በክልል እና በሀገር ደረጃ የሞዴል ፈተና እየተሠጠ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።

በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወንድሜነህ ለአሐዱ እንደተናገሩት፤የሞዴል ፈተናው የሚሰጠው ተማሪዎች ከዋናው ፈተና በፊት የዝግጅት ደረጃቸውን እንዲገመግሙ ለመርዳት ነው።

"ፈተናው ተማሪዎች ጠንካራና ደካማ ጎናቸውን እንዲለዩ፣ ጊዜያቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲቆጣጠሩ እና ከፈተና ጋር የተያያዘ ጭንቀትን እንዲቀንስ ያስችላቸዋል" ሲሉም ተናግረዋል።

እንዲሁም ሊያጋጥሟቸው ስለሚችሉት ጥያቄዎች አወቃቀር እና አስቸጋሪነት እራሳቸውን እንዲያውቁ ጠቃሚ ዕድል ይሰጣቸዋል።

ሞዴል ፈተናው በክልልም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጥ ሲሆን፤ ይህም ተማሪዋቹ ምን ያህል ብቁ ናቸው የሚለውን ትክክለኛ ግምገማ እያስገኘ ነው ተብሏል።

እንዲህ ያለው ሁሉን አቀፍ የዝግጅት ስልት በሀገር አቀፍ ፈተና የተማሪዎችን አጠቃላይ ውጤት ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የ2017 ትምህርት ዘመን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ከሰኔ 23 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።

አገልግሎቱ በወረቀት የሚፈተኑ እና በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተፈታኞች እንደሚያካትት ተገልጿል።

የፈተናው ይዘት በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ እያንዳንዱ ተፈታኝ በትምህርት ቤቱ የተማረበትን የተማሪ መጽሐፍ መሠረት አድርጎ ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስተላልፏል።
የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች  ተጠናቀዋል - የትምህርት ፈተናና ምዘና  አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
****

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ተናገሩ።

አብዛኛውን ጊዜ ፈተና ሲነሳ የፈተና ስርቆትና ኩረጃ አብሮ የሚነሳ ሲሆን፤ ይህን ለማስቀረት መንግስት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተናን ተማሪዎች ከተማሩበት ት/ቤት ወደ  ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው እንዲፈተኑ አድርጓል።

ለፈተና ስረቆትና ኩረጃ የሚያግዙ  ድምፅን ምስልን የሚወስዱ ማንኛውንም  መሳሪያዎችን ተማሪዎች እንዳይጠቀሙና ይዘውም እንዳይገኙ  በመከልከል፤ ጥብቅ ፈተሻ  እንደሚደረገ የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ  ተይዘው ሲገኙም እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ተማሪዎች ፈተናን ለመስረቅና ለመኮረጅ የሚያባክኑትን ጊዜ ትምህርቱን በሚገባ ቢያጠኑበት መልካም ነው፤ ውጤታማም ብለዋል።

በብይነ-መረብና በወረቀት የሚሰጠው የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በተሳካ መንገድ ለመስጠት፤  የትምህርት ተቋማት የቁሳቁስና የተለያዩ ዝግጅቶችን አጠናቀው ተማሪዎችን በመጠበቅ ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

ፈተናውን በብይነ መረብ የሚፈተኑ ተማሪዎች በየትምህርተ ቤታቸው ልምምድ በማድረግ ላይ እንዳሉ የጠቆሙት ዶ/ር እሸቱ፤ ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎችም ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ እየተደረገም ይገኛል ነው ያሉት።

ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ለፈተናው የሚያስፈልጉ ግብአቶች ዝግጁ መሆናቸውን መፈተሸና ለሰው ሀይል ስልጠናዎችን መስጠት፤ እንዲሁም ከክልል ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ከዩኒቨርሲቲ የበላይ አመራሮች ጋር በቅርበት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
#FYI

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሞዴል ፈተና መሰጠት ጀምሯል፡፡

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ለሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ #ሞዴል ፈተና አዘጋጅቷል፡፡

ፈተናው ዛሬ መሰጠት የጀመረ ሲሆን፤ በጠዋት እና ከሰዓት መርሐግብር የሚከናወን ይሆናል፡፡

የትምህርት አመራርና መምህራን እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተሳካ የሞዴል ፈተና እንዲኖርና በሂደቱም ተፈታኞቻችን ከሲሰተሙና ከፈተና ማዕከላቱ ጋር በአግባቡ እንዲተዋወቁ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ  አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ዘንድሮ 150 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናውን በብይነ መረብ ይወስዳሉ።

@ethioaplus
✳️ በፈተና ጊዜ የሚፈጠርን ጭንቀት ወይም ቴንሽንን ልንቆጣጠር የምንችልባቸው ዘዴዎች! 😊

🔰 ፈተና የመፈተኛ ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው ። ይህም ጤናማ ፍርሀት ለፈተና እንድንተጋ ስለሚረዳን በተሻለ ለመዘጋጀት እንዲሁም ጥሩ ትኩረት ለመድረግ ያስችለናል።  ሆኖም ግን ይህ ጭንቀት ወይም ቴንሽን መጠነኛ ካልሆነ ወደ መደናገር እና ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ። በዚህም የተነሳ ፈተናችንን በጥሩ እንዳናስኬድ እና ተገቢውን ትኩረት እንዳንሰጥ ያረገናል ።  ከዚህም ሀሳብ ጋር በተያያዘ ለዚህ አይነቱ ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ እንድንገባ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ ምክንያቶች ውስጥ ጥቂቶቹ: 
📌 አሉታዊ ሀሳቦች ወደ አዕምሮ በመምጣት ሀሳባችን በሙሉ ስለ ፈተናው አስከፊነት እና ስለውጤት መበላሸት አብዝተን ስናስብ ።

📌 በቂ እና ምክንያታዊ ያልሆነ ግመታ እና ድምዳሜ አጠቃሎ ስለፈተናው ማሰብ ። 

📌 የውጫዊ ተፅእኖ እንደ ቤተሰብ ፣ መምህራን እና ጓደኛ የሚመጡ ጫናዎች አስተሳሰባችን ላይ ይህ መሆን አለበት ወይም መሆን የለበትም የሚል አቋም መያዝ ስህተትን እንዳንቀበል እና መሳሳትን እንድንፈራ ስለሚያረግ በፈተና መዳረሻ ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ።

📌• ሙሉ ሀሳብን ወደ ፈተናው ይዘት እና ሁኔታ ከማተኮር ይልቅ ወደ ውጤት እና ነጥብ ብቻ ላይ ማተኮር እና ማስላት።  እነዚህ ዋና ዋናዎቹ በፈተና ወቅት ውጥረትን እና ጭንቀትን የሚያስከትሉ ምክንያቶች ናቸው።  ስለዚህ ተፈታኞች የተወሰነ ዘዴን በመጠቀም ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት፤

🙌🏾 ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን ዜዴዎች፤

🎯• ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት። 

🎯• ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ ይህ ማለት ስለፈተናው ክብደት እና አስከፊነት ከማሰብ በተቃራኒው በአይነ ህሊና (visualization) ዘና ብለን ስንፈተን እና ፈተናውን በተገቢ መንገድ ስንፈተን በአእምሮችን መሳል ። ከዚህ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም በክፍል ውስጥ በብቃት የሰራናቸውን ፈተናዎች እና የገኘነውን ጥሩ ውጤቶች ማሰብ።  እናም ምን አይነት ፈተና ሊመጣ ይችላል ብለን አብዝተን አለመጨነቅ ይልቅ የሚመጣው ፈተና ከዚህ በፊት ከተማርነው የተለየ አለመሆኑን መረዳት እና መጪውም ፈተና በተመሳሳይ እንደምንሰራው ማሰብ።

🎯 • ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ። ምክንያቱም ከላይ እንደ ምክንያት ለተቀመጡት ነጥቦች ከዚህ ሀሳብ በተያያዘ አንድ ተማሪ በፈተና ጥሩ ውጤት ባያገኝ እና ቢሳሳት ቀድሞውኑ ወደ ጭንቅላቱ የሚመጣው አለማወቁ ዋጋ እንደሚያስከፍለው እና ቤተሰቦቹም ሆነ መምህራን እንደ ሰነፍ እና ዋጋ እንደሌለው ስለሚገመት ስህተትን አስተካክሎ ለቀጣይ ለማሻሻል እና ለመማር መሰናክል ይፈጥራል።   ስለዚህ ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን። 

🎯• ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ። ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል። 

🎯• የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ  መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።

🔰 ፈተና ከጀመርን በኋላ መድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤

🍁 • ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።  

🍁• አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ። 

🍁• ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።

🍁 • በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ።
ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር፡፡ ለምሳሌ ;አሁን ደህና ነኝ ፥ ጥሩ ሆኛለሁ ወይም በምናምነው ሀይማኖት ጊዜ የማይወስድብንን አጭር ፀሎት በልባችን መፀለይ። ከዛም መልሰን በተረጋጋ መንፈስ ፈተናውን መጀመር። 

🍁• ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤

🍁  • በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።

🍁• ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ። 

🍁• በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ። ይልቅ በጣም ሳንንቀራፈፍ ተረጋግተን ፈተናውን  መስራት እና ፈተናውን ከጨረስን በኋላ ተመልሰን የሰራነውን ጥያቄ አጠቃላይ ማየት።


https://t.me/ethioaplus
😢1
የሚኮርጅ ሰው ያለእውቀት እና ክህሎት የሚጓዝ በመሆኑ አዲስ ነገር መፍጠር አይችልም፡-ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ተክለማርያም
****

የሚኮርጅ ሰው ያለእውቀት እና ክህሎት የሚጓዝ  በመሆኑ አዲስ ነገር መፍጠር እንደማይችል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና  ተማራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ተክለማርያም ተናገሩ።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጅትን በተመለከተ ከኤፍኤም አዲስ 97.1 ጋር ቆይታ ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፥ ለተማሪ ፈተና ማለት ከክፍል ወደ ክፍል ማለፊያ ወይም መውደቂያ ሳይሆን የተማሪዎችን ጠንካራ እና ደካማ ጎን ለመለየት፤ እንዲሁም ደካማ ጎኑን ለመሙላት እና ጠንካራውን ይበልጥ ለማሻሻል አጋዥ ተግባር ነው ብለዋል።

የፈተና ዓላማ እውቅትን እና ክህሎትን ለማጠናከር ነው ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ የተማሪዎች እውቀትን ከፍ ለማድረግ፣ የትምህርት ተገቢነትን ለማሳደግ እንዲሁም የልጆች ጥንካሬን ለማየትና ለመደገፍ የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በኢትዮጵያ  ከዚህ ቀደም ከውጭ ተኮርጆ ሲተገበር የነበረው የትምህርት ፖሊሲ፤ የሀገሪቱን ችግር ከመፍታት ይልቅ ራሱ ችግር ሆኖ በመቆየቱ በትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ማድረግ አስፈላጊ  እርምጃ መሆኑንም አንስተዋል።

አዲሱ የትምህርት ፖሊሲ መሰረት ከ2013 ወዲህ መሰጠት ከተጀመረ በኋላ፤ ፈተና አብዛኛው ተማሪ በራሱ ሰርቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት አለመቻሉ የትምህርት ፖሊሲውን ክፍተት በደንብ ያሳያልም ብለዋል ፕሮፌሰሩ።

@ethioaplus
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ ለሚፈተኑ ተፈታኞች የቴክኒካል ድጋፍ የሚሰጥ ቡድን ተቋቁሟል።

በበይነ መረብ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ማንኛውንም ድጋፍ በመጀመሪያ በትምህርት ቤታቸው ቀጥሎም በመፈተኛ ማዕከላት ካሉ የትምህርት አመራር እና ቴክኒክ ድጋፍ ሰጪዎች ማግኘት እንደሚችሉ ይታወቃል።

ተጨማሪ ድጋፍ ለተፈታኝ ተማሪዎቹ የሚሰጥ ቴክኒካል ቡድን በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል።

ዘጠኝ አባላት በውስጡ የያዘው ቴክኒካል ቡድኑ፤ በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተከፋፍሎ የተደራጀ ነው።

(የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ቡድኑን ድጋፍ ለማግኘት ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።)


@ethioaplus
በኢትዮጵያ ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ፈቃድ እንጂ እውቅና ያላቸው ተቋማት የሉም ተባለ

በኢትዮጵያ ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ፈቃድ እንጂ እውቅና ያላቸው ተቋማት አለመኖራቸውን የኢፌዲሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ሁለቱን ከተማ አስተዳደሮች እና 14 ቱንም ክልሎች አጠቃሎ 375 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ሲሆን፤ እነዚህ ተቋማት ፈቃዳቸውን ከኢፌዲሪ የትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን የሚወስዱ እና የሚያድሱ እንደሆነም ነው የተገለጸው።

ታዲያ እነዚህ ተቋማት የሚሰጡት ከዲግሪ ጀምሮ ያለው የትምህርት ደረጃ፤ በዓለም አቀፍ እውቅና ያለው እና በተማሩበት የትምህርት ዘርፍ የትኛውም ሀገር ላይ ሄደው ድጋሚ የሄዱበትን ሀገር ትምህርት መማር ሳያስፈልጋቸው መስራት የሚያስችል አይደለም።

"ይህ ለምን ሆነ?፣ ተቋማቱን ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲኖራቸው እና በእነዚህ ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎችም በዓለማቀፍ ደረጃ ተስተካካይ እንኳን ባይሆን ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችል የትምህርት ደረጃ እንዲኖራቸው ማድረግ ለምን አልተቻልም?" ሲል አሐዱ ጠይቋል።

የኢፌዲሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን የተቋማት ቁጥጥር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ኤሮ በሰጡት ምላሽም፤ ይህን እውቅና ለመስጠት በመጀመሪያ ተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ሊያገኝ እንደሚገባው ገልጸው፤ እስካሁን ግን እውቅናውን አለማግኘቱን ተናግረዋል።

"በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉም የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፈቃድ እንጂ እውቅና ገና ያልተሰጣቸው ናቸው" ብለዋል።

ተቋሙም ከዓለም አቀፍ ደረጃ ሰጭ ተቋም ማለትም (አይሶ) ገና እውቅና እንዳልተሰጠውም ተናግረዋል። እሱን ለማድረግ እና እውቅና ያላቸው የትምህርት ተቋማትን ለማፍራት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል።
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን የሚሰጡ ከ28 ሺህ በላይ #ፈታኞች መመልመላቸው ተገለፀ፡፡

ፈታኞቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጠውን ፈተና በብቃት ለመስጠት ዝግጅት ያደረጉ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለኢቲቪ ተናግረዋል፡፡

ዘንድሮ መልቀቂያ ፈተናውን በበይነመረብ የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች አስፈላጊውን ልምምድ እያደረጉ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በፈተናው ወቅት የኢንተርኔት እና የመብራት መቆራረጥ እንዲሁም ሌሎች ችግሮች እንዳይፈጠሩ፤ ከ10 ተቋማት የተወጣጣ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እየሠራ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

@ethioaplus
በኢትዮጵያ ፈተና ሳያጠኑ ማለፍ እንደማይቻል ግልፅ እየሆነ ነው - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
****

በኢትዮጵያ እንደከዚህ ቀደሙ ፈተና ሳያጠኑ እና ሳይረዱ ማለፍ እንደማይቻል  ግልፅ እየሆነ በመምጣቱ አብዛኛው የትምህርት ማህበረሰብ  በትኩረት ልጆችን ለማብቃት ርብርብ ማድረግ መጀመሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ የ12ኛ ክፍል ፈተና ዝግጅትን በተመለከተ ለኢቲቪ 57 የዜና መሰናዶ በሰጡት ማብራሪያ፤ ሀገር አቀፍ ፈተናውን ያለምንም እክል ለመስጠት በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

እንደ ሀገር በወረቀትም ሆነ በበይነ መረብ ፈተናውን ያለምንም ችግር ለመስጠት፤ ከ28ሺህ በላይ ፈታኞች ተመልምለዋልም ነው ያሉት።

ባለፉት ጊዜያት ብዙ ተማሪዎችን ማሳለፍ ያልቻሉ ትምህርተ ቤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ፤  የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሩ በዘድሮው ፈተና ብዙ ተማሪዎችን የማሳለፍ እድል እንዳላቸውም ጠቁመዋል።

ሀገራዊ ፈተናውን በበይነመረብ የሚፈተኑ 150ሺህ ተፈታኞችም አስፈላጊውን ልምምድ እያደረጉ መሆናቸውንም አንስተዋል።

ያነበቡ ተማሪዎች እንዲሁም ተማሪዎቻቸውን በደንብ ያዘጋጁ ትምህርት ቤቶች ጥሩ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉም ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

በፈተናው ወቅት የኢንተርኔትና የመብራት መቆራረጥ እንዲሁም ሌሎች ችግሮች እንዳይፈጠሩ፤ ከ10 ተቋማት የተወጣጣ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

@ethioaplus
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ተኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !


ኢድ ሙባረክ 💜

Join us➔ @ethioaplus
3
ለ22 ሴት አይነስውራን ተማሪዎች ድጋፍ ተደረገ።

ጸሐይ ዘውዴ መታሰቢያ የስኮላርሺፕ ፈንድ ለ22 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ሴት አይነስውራን ተማሪዎች ድጋፍ አደረገ።

ፈንዱ የቀድሞዋ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  ተ/ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት  ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በዘንድሮው ዓመት ለሚመረቁ 22 ሴት አይነስውራን ተማሪዎች የስማርት ስልኮችን ድጋፍ አድርጓል።

ጸሐይ ዘውዴ መታሰቢያ የስኮላርሺፕ ፈንድ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 14 ዓመታት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አይነስራውን ተማሪዎች የመማሪያ ቴክኖሎጂ ግባአቶችን ጨምሮ የገንዘብና የተለያዩ ድጋፎችን እንዲሁም ስልጠናዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአካል ጉዳተኞችን  የትምህርት ስኬት ለማረጋገጥ የልዩ ድጋፍ ቢሮ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ በዚሁ ወቅት ተገልጿል፡፡

@ethioaplus
እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም” ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የመምህራን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

"እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው፣ መኪናቸውን በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤታቸው በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ለኔ ደስታ የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጥ ውስጡን እየተሠሩ ያሉት ሥራዎች ሲሳኩ የመምህራን ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል።

የመምህራን ጥያቄ በደመወዝ ጭማሪ ብቻ የማይመለስ መሆኑን አንስተው፣ የደመወዝ ጭማሪው ላይ ብቻ ትኩረት ከተደረገ ያለችው ተበልታ ታልቃለች ብሏል።

@Ethioaplus
ፈተናውን ከስርቆት በጸዳ መልኩ እንዲሰጥ በማድረግ ውጤታማና ተወዳዳሪ ትውልድ መፍጠር ይገባል – ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ ሂደትን በተመለከተ የጸጥታ ዕቅድና ኦሬንቴሽን መርሐ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ኃላፊዎች፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ተወካዮች እና የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የ12ኛ ክፍል ፈተና በአግባቡ እንዲሰጥ ትኩረት የተሰጠው የተሻለ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ገልጸው፤ ፈተናውን ከስርቆት በጸዳ መልኩ እንዲሰጥ በማድረግ ውጤታማና ተወዳዳሪ ትውልድ መፍጠር ይገባል ብለዋል።

ባለፉት ሦስት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ ችግሮችን በማረም ፈተናውን በተሻለ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤት የተገኘባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የጸጥታ አካላት ሚና ትልቅ መሆኑን ጠቁመው፤ 12ኛ ክፍል ፈተና ከነበረበት ችግሮች ተላቆ በተሻለ መልኩ እንዲሰጥ የጸጥታ ተቋማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

ዘንድሮ ፈተናው ለ150 ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ፈተና አሰጣጡ ወደ ዲጂታል እንዲሸጋገር እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ፖሊስ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም እንዲካሄድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቁመዋል።

@ethioaplus
2