Ethio A+
255 subscribers
211 photos
10 videos
203 files
98 links
A+ is Possible!
Feel free to ask and give any suggestion!
@EthioAplus_admin

https://youtube.com/@ethioa_plus?si=DekKjJasKzd5Oaq-
Download Telegram
#GOOD FRIDAY!

Good Friday is an important religious holiday for Christians throughout the world. It commemorates the crucifixion and death of Jesus Christ and is the most solemn day of the Christian year. It is the day before Easter Sunday, which celebrates the resurrection of Jesus.

Happy Good Friday!

@ethioaplus
" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው  " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

via @ethioaplus
👍1
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በዓሉ የሰላም እና የደስታ ይሁንላችሁ ።

መልካም በአል🙏

@ethioaplus
🙏21
Order of adjective with rules
👍2
Punctuation marks
👍2
መሳሳትህን አትጥላው ፣መውደቅም መሸነፍ አይደለም፤ ግን አንድ ነገር አስታውስ የተሸነፍከው ያቆምክ እለት ነው!

ማርቲን ሉተርም በአስገራሚ ንግግሩ እንዲህ ብሏል "መሮጥ ቢያቅትህ ተራመድ መራመድ ቢያቅትህ ዳዴ በል ዳዴ ማለት ቢያቅትህ ተንፏቀቅ ግን በፍፁም #እንዳታቆም!"

@ethioaplus
👍3
😱Biology common Terms for Grade 12 Entrance Examinations 🥰

1. Cell: The basic unit of life; the smallest structure capable of performing all life processes.

2. DNA (Deoxyribonucleic Acid): A molecule that carries genetic information in living organisms and is responsible for heredity.

3. Gene: A segment of DNA that contains the instructions for building a specific protein or function.

4. Chromosome: A thread-like structure made of DNA and proteins that contains genetic information; humans typically have 46 chromosomes.

5. Mitosis: A type of cell division that results in two genetically identical daughter cells, used for growth and repair.

6. Meiosis: A specialized form of cell division that reduces the chromosome number by half, producing gametes (sperm and eggs).

7. Protein: A macromolecule made up of amino acids, essential for structure, function, and regulation of the body’s tissues and organs.

8. Enzyme: A protein that acts as a catalyst to speed up chemical reactions in biological processes.

9. Photosynthesis: The process by which green plants and some other organisms convert light energy into chemical energy (glucose) using carbon dioxide and water.

10. Respiration: The biochemical process in which cells convert glucose and oxygen into energy, carbon dioxide, and water.

11. Homeostasis: The maintenance of a stable internal environment within an organism despite external changes.

12. Ecosystem: A community of living organisms interacting with one another and their physical environment.

13. Biodiversity: The variety of life in a particular habitat or ecosystem, including the number of species and genetic diversity.

14. Natural Selection: The process by which organisms better adapted to their environment tend to survive and produce more offspring.

15. Mutation: A change in the DNA sequence that can lead to variations in traits and may affect an organism's ability to survive.

16. Allele: Different forms of a gene that can exist at a specific locus on a chromosome.

17. Phenotype: The observable physical or biochemical characteristics of an organism, determined by its genotype and environment.

18. Genotype: The genetic constitution of an organism, representing the alleles inherited from its parents.

19. Autotroph: An organism that produces its own food from inorganic substances, typically through photosynthesis or chemosynthesis.

20. Heterotroph: An organism that cannot produce its own food and must consume other organisms for energy.

21. Cell Membrane: A phospholipid bilayer that surrounds the cell, controlling the movement of substances in and out.

22. Nucleus: The membrane-bound organelle that contains the cell's genetic material (DNA) and controls cellular activities.

23. Cytoplasm: The gel-like substance within the cell membrane that contains organelles and is the site of many metabolic processes.

24. Organelle: Specialized structures within a cell that perform distinct functions (e.g., mitochondria, ribosomes).

25. Vesicle: A small membrane-bound sac within a cell that transports materials to different locations inside the cell.

26. Antibody: A protein produced by the immune system that recognizes and neutralizes foreign objects like bacteria and viruses.

27. Hormone: A chemical messenger produced by glands in the endocrine system that regulates physiological processes in the body.

28. Symbiosis: A close interaction between two different species, which can be mutualistic, commensalistic, or parasitic.

29. Population: A group of individuals of the same species living in a specific area at the same time.

30. Trophic Level: The position an organism occupies in a food chain, determined by its feeding relationships (e.g., producers, primary consumers).

https://t.me/ethioaplus
👍1
Physics 10 ጥያቄዎች ለ ማትሪክ ተፈታኞች ከነመልሶቻቸው

1.  What is the SI unit of capacitance?
A) Ohm
B) Farad
C) Coulomb
D) Volt

2. Which of the following factors does not affect the capacitance of a capacitor?
A) Area of the plates
B) Distance between the plates
C) Dielectric material between the plates
D) Charge on the plates

3. When a dielectric material is inserted between the plates of a capacitor, what happens to the capacitance?
A) Increases
B) Decreases
C) Remains the same
D) Fluctuates

4. In a parallel plate capacitor, the capacitance is directly proportional to:
A) Area of the plates
B) Distance between the plates
C) Both area and distance
D) Charge on the plates

5. If the potential difference across a capacitor is doubled, what happens to the stored energy in the capacitor?
A) Doubles
B) Halves
C) Quadruples
D) Remains the same

6. The energy stored in a capacitor is given by the formula:
A) 1/2CV^2
B) CV
C) Q/V
D) C/V

7. What happens to the capacitance of a capacitor if the distance between the plates is increased?
A) Increases
B) Decreases
C) Remains the same
D) Becomes zero

8. The total energy stored in a capacitor is directly proportional to:
A) Voltage across the capacitor
B) Square of the voltage across the capacitor
C) Inverse of the voltage across the capacitor
D) Charge on the plates

9. Which of the following materials is commonly used as a dielectric in capacitors?
A) Copper
B) Air
C) Glass
D) Silver

10. Capacitors are commonly used in electrical circuits for:
A) Storing charge
B) Regulating current
C) Increasing resistance
D) Decreasing voltage fluctuations


🔑Answers and explanation

➀. B) Farad
Explanation: The SI unit of capacitance is the Farad, symbol F.

⓶. D) Charge on the plates
Explanation: The capacitance of a capacitor is directly proportional to the area of the plates and the permittivity of the dielectric material, and inversely proportional to the distance between the plates.

⓷. A) Increases
Explanation: When a dielectric material is inserted between the plates of a capacitor, the capacitance increases due to the material's ability to store more charge.

⓸. A) Area of the plates
Explanation: In a parallel plate capacitor, the capacitance is directly proportional to the area of the plates.

⓹. C) Quadruples
Explanation: The energy stored in a capacitor is directly proportional to the square of the potential difference across it.

⓺. A) 1/2CV^2
Explanation: The energy stored in a capacitor is given by the formula 1/2CV^2, where C is the capacitance and V is the potential difference across the capacitor.

⓻. A) Increases
Explanation: The capacitance of a capacitor increases when the distance between the plates is increased.

⓼. B) Square of the voltage across the capacitor
Explanation: The total energy stored in a capacitor is directly proportional to the square of the voltage across the capacitor.

⓽. C
) Glass
Explanation: Glass is a common dielectric material used in capacitors due to its insulating properties.

⓾. A) Storing charge
Explanation: Capacitors are used in electrical circuits to store and release electrical energy in the form of charge.

https://t.me/ethioaplus
👍1
🔥 አታመንታ❗️

👉ቁጭ ብለህ እንዲህ ባደርግ እንዲህ ቢሆን አትበል! አድርገው! ወደ ተግባር ግባ! ወዳጄ ባህሩ ላይ ማፍጠጥ አያሻግርህም ተነስተህ ጀልባውን መቅዘፍ አለብህ።

👉ከአልጋህ ተነስ፣ መፅሀፉን አንብብ፣ አጠናለው ያልከውን ቀኑ ሳያልፍ ጨርሰው ፤ ወዳጄ የተግባር ሰው ካልሆንክ በሀሳብ መንሳፈፍ ነው ስራህ! ዳይ አሁን ጀምረው! ተነስ!

❤️የሚያምር🥰 ዕለት ተመኘንላችሁ🙏

https://t.me/ethioaplus
ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ የሚያደርግ ሕግ ሊተገብር መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ሕጉን ወደ መሬት ለማውረድ ትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች እና ከዘርፉ አመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ዕቅድ ይዟል፡፡

በሕጉ ዙሪያ ሸገር ኤፍኤም ያነጋገራቸው መምህራን ውሳኔው ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ሊታዩ የሚገባቸው ሌሎች ነገሮች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡

ተማሪዎች አሁን ላይ ክፍል ውስጥ ሞባይል ስልክ ይዘው ሲማሩ ‘’ትምህርታቸው ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ፣ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን መከታተል እንደሚያበዙ" ጠቅሰዋል፡፡

ስልክ መያዛቸው ከትምህርታቸው እንዲናጠቡ እያደረጋቸው መሆኑን ያነሱት መምህራኑ፤ መፅሐፍት እና ጥናት ላይ ከማተኮር ይልቅ ሌሎች ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎች ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ አድርጓል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ትምህርት ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንዳሉ ገልፀዋል፡፡ በቂ የመፅሐፍት አቅርቦት፣ የICT ላብ፣ የኮምፒውተር ግብዓቶች እንዲሁም የተለያዩ አጋዥ መፅሐፍት ሊሟሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡

@ethioaplus
👍4
የቆመው የናጋሳኪው ልጅ " ብዙዎቻችኹ የምታውቁት ታሪካዊ ፎቶ ነው።
በ 1933 ዓመተ ምሕረት የኛ ክረምት ወራት ውስጥ በጃፓኗ ናጋሳኪ ከተማ ከዘነበው የአተም ቦምብ በኋላ የተነሳ ፎቶ ነበር።
ዕድሜው 10 ያኽል ይኾናል የተባለ ልጅ የሞተውን ትንሽ ወንድሙን እንዳዘለ ቀጥ ብሎ  እሱም ሞቱን ሲጠብቅ ተገኝቶ የተነሳ ፎቶ ነው።

አንድ ወታደር ተጠግቶት እንዳይደክመው ያዘለውን ሙት ወንድሙን እንዲያወርደው ነገረው።

የዚያ ልጅ ምላሽ ግን " አይከብድም፤ ወንድሜ ነው፣" ኾነ።

ወታደሩም ገባው።

ከዝያን ጊዜ ጀምሮ ይህ ፎቶ የጃፓን አንድነት ምልክት ኾነ።

የኛም መሪ ቃል ቢኾን ምናለበት፦ "ከባድ አይደለም፤ ወንድሜ ነው፣"
ቢወድቅ፣ አንሳው። ቢደክምህም እንኳ፣ እርዳው።
የርሱ ድጋፍ ደካማ ቢኾን እንኳ፣ እናም ቢሳሳት እንኳ፣ ይቅር በለው፤ ምክንያቱም እሱ ከባድ ሳይኾን ወንድምህ ነው። ደግሞም ዓለም እሱን ብትተወውም አንተ በጀርባህ እዘለው።

ጓደኝነት እና ቤተሰብ ማለት ምንም ይኹን ምን እርስ በራስ ተዛዝሎ መኖር ነው።

መጋቢ ሰለሞን አበበ
🔥5👍1
በ2017 ዓ.ም የሚሰጠውን ሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪዎች የኦንላይን መለማመጃ ፈተና መስጠት ተጀምሯል፡፡

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን ቴክኖሎጅ ስራ አስፈጻሚ በተሰራው ሶፍትዌር አማካኝነት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና በኦንላይን ለሚፈተኑ ተማሪዎች የመለማመጃ ፈተና በመሰጠት ላይ ነው።

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን ቴክኖሎጅ ስራ አስፈፃሚ አዱኛው አለበል እንደገለጹት የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ኢንተርኔት ባለባቸው አካባቢዎች የሚማሩ ተማሪዎች በበይነ መረብ እንደሚሰጥ ከትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ለሚገኙ ሶስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1,670 ለሚሆኑ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የአይሲቲ ባለሙያዎች በተሰራው ሶፍትዌር የበየነ መረብ የመለመጃ ፈተና ከትናንት ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ስራ አስፈጻሚው አያይዘውም የመለማጃ ፈተናው አስፋላጊነት ተፈታኝ ተማሪዎች ቴክኖሎጅው ጋር አንዲግባቡና ለቀጣይ ለዋናው ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የመለማመጃ ፈተናው  ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 07/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ጠቅሰው በቀጣይ የአዊ ብሄረሰብ ትምህርት መምሪያ በሚያወጣው መርሀ ግብር መሰረት የበየነ መረብ (ኦንላይን) ሞዴል ፈተና እንደሚፈትኑም ገልፀዋል።

@ethioaplus
#EthiopianDefenceUniversity

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ምልመላ ማድረግ ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን መልምሎ ለማስተማር በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን በማካሔድ ላይ ይገኛል።

በዚህም ከመንግሥት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር እንቅስቃሴ ዙሪያ ውይይት አካሒዷል።

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ እና የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የተማሪ ቅበላና ምልመላ ዙሪያ ገለጻ ከተደረገላቸው ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ይጠቀሳሉ።

በወታደራዊ  ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በፈጠራ ክህሎት ልዩ አቅም ያላቸው ተማሪዎች በውድድር ዩኒቨርሲቲውን መቀላቀል እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በጤና፣ በኢንጅነሪግ እና ሌሎችም የሙያ ዘርፎች ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚካተት መገለፁ ይታወሳል።

©️tikvahuniversity

@ethioaplus