Ethio A+
255 subscribers
211 photos
10 videos
203 files
98 links
A+ is Possible!
Feel free to ask and give any suggestion!
@EthioAplus_admin

https://youtube.com/@ethioa_plus?si=DekKjJasKzd5Oaq-
Download Telegram
FOR MORE FULLY FUNDED SCHOLARSHIPS JOIN US👇

📌Telegram:- https://t.me/ethioaplus

🎓 If this isn’t for you, 📣 share it with others! 🌟
      አንድ ቀን እንዎት ነገሮቜን ታግሰህ ፣ ተቋቁመህና አሾንፈህ እንደወጣህ አስደማሚ ታሪክህን ታጋራለህ እሱም ለብዙዎቜ አበርቺ ይሆናል.... ታገስ!ጜና!!
🀞 መልካም ቀን!!👋

@ethioaplus
ለእስልምና እምነት ተኚታይ ዚቻናላቜን ቀተሰቊቜ

🌙 እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው ዚዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደሚሳቜሁ!

ዒድ ሙባሚክ!

© ethioaplus
....ጥቁሮቜን አብዝቶ ዹሚጠላ አንድ ነጭ አሜሪካዊ ወጣት፣ ለመዝናናት ኒዉዬርክ ዉስጥ ካሉ ሆ቎ሎቜ መሃል ወደ አንዱ ይገባል።

በሆቮሉ ዉስጥ ጥግ ይዞ ኹተቀመጠዉ አንድ ጥቁር ሰዉ በስተቀር በሆቮሉ ውስጥ ይዝናኑ ዚነበሩት በሙሉ ነጮቜ ነበሩ።

ይህ ወጣት ብቻዉን ዹተቀመጠዉን ጥቁር ሰዉ በጥላቻ áŠ¥á‹šá‰°áˆ˜áˆˆáŠšá‰° አስተናጋጇን በመጥራት ድምፁን ኹፍ አድርጎ...

"ኚዚያ ጥቁር ሰዉ በስተቀር!!እዚህ ሆቮል ዉስጥ ላሉት ሰዎቜ ዚሚፈልጉትን ምግብ ይመገቡ ሂሳቡን እኔ ነኝ ዹምኹፈለዉ!!" በማለት ኚኪሱ ብዙ ዶላሮቜን አዉጥቶ ለአስተናጋጇ ይሰጣል።

አስተናጋጇም በሰጣት ብር፣ ኚጥቁሩ ሰዉዬ ዉጭ፣ ሆቮሉ ዉስጥ ላሉት በሙሉ ዚሚፈልጉትን አይነት ምግብ አቀሚበቜላ቞ዉ።

ጥቁሩም ሰዉ ኚመናደድ ይልቅ አሜሪካዊውን ወጣት አዹተመለኹተ "አመሰግናለሁ!!" ይላል።

ወጣቱ እንደጠበቀዉ ጥቁሩ ሰዉ ምንም እንዳልተበሳጚ ሲመለኚት ፣ ድጋሜ አስተናጋጇን ይጠራና ድምፁን ኹፍ አድርጎ.. "አሁንም ኚዚያ ጥቁር ሰዉዬ ዉጭ ሆቮሉ ዉስጥ ላሉት በሙሉ ወይንና ሌላ ዚሚፈልጉት ነገር ይጠቀሙ እኔ ነኝ ዹምኹፍለዉ!!"በማለት  ጥቁሩን ሰዉ በጥላቻና ቁጣ አዹተመለኹተ ብዙ ዶላሮቜን ኚኪሱ አዉጥቶ ለአስተናጋጇ ይሰጣል።

አስተናጋጇም እንደታዘዘቜዉ ለሁሉም እንደዚፍላጎቱ አቀሚበቜላ቞ዉ።

ጥቁሩ ሰዉዬም እንደቀድሞዉ ሁሉ ፈገግ በማለት ወጣቱን "አመሰግናለሁ" ይለዋል።

ዚጥቁሩ ሰዉ ፈገግታ አሜሪካዊዉን በጣም ያናድደዉና አስተናጋጇን ጠርቶ..."ይኌ ጥቁር ሰዉ ግን ያመዋል እንዎ? ኚእሱ ዉጭ ሌላዉን ሰዉ ሁሉ ስጋብዝ መናደድ ሲገባዉ እዚሳቀ አመሰግናለሁ ይለኛል። ጀነኛማ አይመስለኝም!!"ሲል አስተናጋጇን ይጠይቃታል።

አስተናጋጇም ፈገግ በማለት "ኧሹ ጀነኛ ነዉ!! ዹሆቮሉ ባለቀት ስለሆነ ነዉ!!" በማለት ነበር ዚመለሰቜለት።

ጥላቻ ዚነበሚንን፣ ያለንን፣ ሊኖሹን ዚሚቜሉ ነገሮቜን በሙሉ ሊያጠፋ ዚሚቜልና ዚሰይጣንን ምግባር በሚገብሩ ጥቂት አወቅን ባይ አላዋቂዎቜ ዚሚፈበሚክ፣ አሰተሳሰብን ለማዛባት በሚስኪኑ ህዝብ ላይ ዹሚለቀቅ ዚጭንቅላት ቫይሚስ ነዉ።

ለዚህ አደገኛ ቫይሚስ ሁነኛ '𝓪𝓷𝓜𝓲 𝓿𝓲𝓻𝓟𝓌'ፍቅርና መዋደድ ብቻ ነዉ!!

ዚንባብ አለም 📗🌍

𝓢𝓱𝓪𝓻𝓮 𝓪𝓷𝓭 𝓳𝓞𝓲𝓷
@ethioaplus
ሮበርት ሙጋቀ ይህን ብለው ነበር👇

"ዚአፍሪካ ዚትምህርት ስርአት አስገራሚ ውጀቶቜ አሉት።

አንደኛ ደሹጃ ዹሚይዙ ቀለሜ ጎበዝ ተማሪዎቜ ጥሩ ውጀት አምጥተው ኢንጂነሪንግና ሜዲሰን እዲማሩ እድል ያገኛሉ።

ሁለተኛ ደሹጃ ዚሚይዙት ደግሞ ህግና
ማኔጅመንት ተምሹው አንደኛ ደሚጃዎቹን
ያስተዳድሯ቞ዋል።

ዝቅ ብለው በ ሶስተኛ ደሹጃ ዚሚገኙት
ተማሪዎቜ ደግሞ ፖለቲካ ውስጥ ይገቡና አንደኛም ሁለተኛም ደሹጃ ላይ ያሉትን ኹላይ ሆነው ይቆጣጠራሉ።

በትምህርት ወዳቂዎቜ ደግሞ ፖሊስና ወታደር ይሆናሉ እነዚህ ደግሞ ፖለቲኚኞቜን ይቆጣጠራሉ ደስ ያላላ቞ውን ፖለቲኚኛ እስኚ መግደል ድሚስ ።

ኹሁሉም ግን ምርጡ ጭራሜ ክላስም ሆነ ትምህርት ቀትም ገብቶ ዚማያውቀው ደግሞ ነብይና ጠንቋይ ይሆናል ይሄን ደግሞ ሁሉም ይኚተሉታል፡፡

𝓣𝓱𝓮 𝓵𝓮𝓰𝓮𝓷𝓭 🫡

@ethioaplus
👍2👎2💯1
እስኪ react ማድሚግ እጃቹ ይልመድ 🙁 እዚ ቀት ምንድን ነው ዝምታው 🫠 Subscribe, like, Share እያደሚግን ቻናላቜንን ተደራሜ እናድርጋት 👍🏜 ❀

https://t.me/ethioaplus
❀4
ሮበርት ሙጋቢ

... ሮበርት ሙጋቀ እንዲህ ብለው ነበር...ለነጫጭ መኪኖቜ ጥቁር ጎማ መጠቀም እስካልቆመ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

ኚሌሎቜ ቀለማት በፊት ነጫጭ ልብሶቜን አስቀድሞ ማጠብ እስካልቆመ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

ጥቁር ቀለምን ለመጥፎ ገድ፣ ነጭን ደግሞ ለሠላም ምልክት መጠቀም እስካልቆመ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

ጥቁር ቀለምን ለሐዘን፣ ነጭን ግን ለሠርግ መጠቀም እስካልቆመ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

ዕዳ቞ውን ያልኚፈሉ ሰዎቜን ኹነጭ መዝገብ ይልቅ ጥቁር መዝገብ ላይ መመዝገብ እስካልቆመ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

በፑል ጚዋታ ላይ ጥቁሩ ድንጋይ ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ነጩ ድንጋይ በሜዳው ውስጥ ብቻውን በድል መንኚባለሉ እስካልቀሚ ድሚስ ዘሚኝነት አይጠፋም

እኔ በበኩሌ ቜግር ዚለብኝምፀ ሜንት ቀት ገብ቞ ዹምጠርገው በነጭ ወሚቀት ( ሶፍት) እስኚሆነ ድሚስ ብዙ ቅር አይለኝም 😍

ሮበርት ሙጋቀ

@ethioaplus
@ethioaplus
Ethio A+
Photo
ዚዩኒቚርስቲ ተማሪዎቜ ኹመመሹቃቾው በፊት ለአንድ ዓመት áŠ¥áŠ•á‹²á‹«áˆµá‰°áˆáˆ© ሊገደዱ ነው።

ትምህርት ሚኒስ቎ር ዚዩኒቚርስቲ ተማሪዎቜ ኹመመሹቃቾው በፊት ማኅበሚሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ ዚሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድሚግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዹሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቮክኖሎጂ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎፣ ዹ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ዚተማሪዎቜ ውጀት ዝቅተኛ ዚሆነበትን መንስዔ በተመለኹተ በቀሹበ ጥናት ላይ  ውይይት ሲደሚግ፣ በዩኒቚርስቲ ተማሪዎቜ ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል።

ላለፉት ዓመታት(እሳ቞ው  በኃላፊነት ኚተሟሙ ጀምሮ)፣ ዹ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ዚተማሪዎቜ ውጀት በኹፍተኛ ደሹጃ ዝቅተኛ  እንዲሆን ካደሚጉ መንስዔዎቜ መካኚል፣ ዚመምህራን ብቃትና ዚተነሳሜነት ማነስ ተጠቃሜ መሆናቾው ጠቁመዋል።

ቜግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል ዚተለያዩ ተግበራት እዚተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጞዋል።

''ዚኢትዮጵያ ዩኒቚርስቲ ሰርቪስ'' ዹሚል መጠሪያ ዹተሰጠው አሠራር ኹ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደሚግ ዕቅድ ዚተያዘ መሆኑን ዚገለጹት ሚኒስትሩ፣ "በአራት ዓመት ዹሚመሹቅ ተማሪ፣ ዚሊስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማሚው ማኅበሚሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት ዚማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበሚሰቡን እንዲያገለግል ይደሹግና) እንዲመሚቅ ይደሹጋል"ሲሉ ተናግሚዋል። ይህም ሲሆን ዚተማሪዎቹ መሠሚታዊ ወጪ ዹሚሾፈን እንደሚሆንም አክለዋል።

ይህ አሰራር ለተማሪዎቜ ለራሳ቞ው ዚተግባር ትምህርት እንደሚሆንና ዹበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋ቞ውም ተናግሚዋል።

ተማሪዎቜ ዚመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እዚቀነሰ ዚመጣውን ወደ ሙያው ዚሚገባ ዚአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚሚዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደሹገ ግምገማ ፣ 100,000 ዚሚደርስ ዚመምህራን ዕጥሚት መኖሩ መታወቁን ዚተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በኹፍተኛ ደሹጃ ያለውን ዚመምህራን ዕጥሚት እንዲቀንስ ዚበኩልን እንደሚወጣ አስሚድተዋል።

ወደ መምህርነት ሙያ ዚሚገቡ ሰዎቜን ክፍተት ለማስተካኚል ኚተያዙ ዘርፈ ብዙ ዚማትጊያ ሥርዓቶቜ አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ ዚፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ ዚራሳ቞ው ድርሻ እንዲኖራ቞ውና ዚኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድሚግ፣ "ዚመምህራን ባንክ" ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል።

ባንኩ "በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ ዚኢትዮጵያ ዩኒቚርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

#Reporter

@ethioaplus
@ethioaplus
🔀Kind of paragraph 📒

🥇 Expository paragraph

The purposes of an expository paragraph are:

✅To instructor teach readers about something, and to change or add to the knowledge or attitude of the readers
✅To explain processes and give directions
✅To explain a new idea or a method of doing something

🥈 Narrative paragraph

The purpose of a narrative paragraph are:

✅ Telling a story
✅ A History text about historical events
✅ A letter you write to your friend about your journey

🥉 Descriptive paragraph

The purpose of this Descriptive paragraph is:

✅ To show the reader what someone or something looks like
✅To create pictures in the reader's mind

4⃣ persuasive( argumentative) paragraph

The purpose of this study is:

✅ For Advertisement
✅To convince or persuade


🆒 Likeℹ Share 🛂

𝚓𝚘𝚒𝚗 𝚞𝚜 
@ethioaplus
👍1
"ዛፍ ለመቁሚጥ 6 ደቂቃ ብቻ ቢሰጠኝ🌎 አራቱን ደቂቃ መጥሚቢያውን እዚሳልኩ አጠፋዋለው"🧭 ብሎ ነበር አንድ ዚማኚብሚው ዹሀገር መሪ።😇

አንተም ጊዜ ማጥፋት ያለብህ ራስህን ለመቀዹር ነው እንጂ ትምህርት፣ ስራው፣ ገንዘቡ፣ ዹፍቅር ግንኙነቱን ማሳመር ቀላል ነው። ወዳጄ መጀመሪያ አንተ በአመለካኚትና በስብዕና ኹፍ በል እንጂ ሌላውን መቀዹር ማገዶ አይፈጅም!

መጋቢት 29/2017 ዓ.ም

መልካም ቀን///////////////

Ethio A+ The New Way Of Learning!📖

https://t.me/ethioaplus
በዩኒቚርሲቲዎቜ እዚተሰጠ ዹሚገኘው ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ2ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ እንዲሰጥ ተጠዚቀ፡፡

ዚፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት "በኢትዮጵያ መልቀቂያ ዚብሔራዊ ፈተና ውጀት ዚቅርብ ጊዜ ተለዋዋጭነት ግምገማ" በሚል ርዕስ ለአንድ ዓመት ዹቆዹ ጥናት ውጀት ይፋ አድርጓል።

ኢንስቲትዩቱ ካቀሚባ቞ው ዚፖሊሲ ምክሹ ሐሳቊቜ መካኚል፣ ኹ2014 ዓ.ም ጀምሮ በዩኒቚርሲቲዎቜ እዚተሰጠ ዹሚገኘው ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ2ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ ይሰጥ ዹሚለው ይገኝበታል፡፡

በኢንስቲትዩቱ ዚማኅበራዊ ልማትና አካታቜነት ማዕኹል ኃላፊና ኹፍተኛ ተመራማሪ ደሳለኝ አንጭሶ (ዶ/ር)፥ ዚተማሪዎቜ ውጀት እንዲቀንስ ካደሚጉ ቁልፍ ምክንያቶቜ መካኚል ዹፈተና አሰጣጥ ስርዓቱ መቀዹር በተለይ ኚኚተሞቜ ራቅ ካሉ አካባቢዎቜ ወደ ዩኒቚርሲቲ ዚሚመጡ ተማሪዎቜ ላይ ዹፈጠሹው ዚስነ-ልቩና ቜግር ተጠቃሜ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተፈጠሹው ዚስነ-ልቩና ቜግር ምክንያት ጥሩ ውጀት ማምጣት ዚነበሚባ቞ው ተማሪዎቜ ውጀት ሳያመጡ መቅሚታ቞ው ትኩሚት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡

"ተማሪዎቜ ዚባዮሜትሪክ መሚጃዎቜ እንዲሞሉ በማድሚግ እንዲሁም በ2ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ ዚደኅንነት ካሜራዎቜን በመግጠም ዚቁጥጥር ስራ በመስራት፣ ተማሪዎቜ ኚሚኖሩበት አካባቢ ሳይርቁ ፈተናውን እንዲፈተኑ ትምህርት ሚኒስ቎ር ዚሚዥም ጊዜ ዕቅድ ይዞ እንዲሠራ" ምክሹ ሐሳብ መቅሚቡን ገልፀዋል።

ዚትምህርት ቀቶቜን መሠሹተ ልማት ማሻሻል እና ኚታቜ ጀምሮ ጥራት ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ዚገለፁት ኃላፊውፀ ዚትምህርት ቀት አመራሮቜ ዕውቀትን መሠሚት ባደሚገ ሁኔታ ሊመደቡ እንደሚገባም ምክሹ ሐሳብ መቅሚቡን ተናግሚዋል።

በማኅበሚሰቡ ዘንድ "ትምህርት ምን ያደርጋል" ዹሚል ዕሳቀ መቀዹር ላይ አፅንኊት ሰጥቶ ዚለውጥ ሥራ መስራት ይገባል ዹሚለው በጥናቱ ዹተለዹ ምክሹ ሐሳብ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ጥናቱ በፀጥታ ቜግር ምክንያት ዚአማራ እና ኊሮሚያ ክልሎቜን እንዳላካተተ ተገልጿል። #Reporter

https://t.me/ethioaplus
በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዹ6ኛ ፣ ዹ8ኛና ዹ12ኛ ክፍል ምዮል ፈተና መስጫ ዹጊዜ ሎሌዳ

@ethioaplus
" ተማሪዎቜ ወደ ትምህርት ቀት ስልክ ይዘው እንዳይሄዱ ለማድሚግ እንቅስቃሎ ተጀምሯል " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

ተማሪዎቜ ወደ ትምህርት ቀት ስልክ ዚሚባል ነገር ይዘው እንዳይገቡ ለማድሚግ እንቅስቃሎ መጀመሩን ትምህርት ሚኒስ቎ር አሳወቀ።

ዚትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በሚመሩት ዚትምህርት ዘርፍ ላይ ስለአፈጻጻምና ስለታቀዱ እቅዶቜ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በሰጡት ማብራሪያም በሚቀጥለው ሳምንት ኚትምህርት ቢሮዎቜ ጋር ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።

በዚህም ወቅት ተማሪዎቜ ስልክ ትምህርት ቀት ይዘው እንዳይገቡ ለማድሚግ ስለሚደሚገው እንቅስቃሎ እንደሚመኚር ገልጞዋል።

" ዚጋራ ስምምነት ላይ ኚደሚስን ኚሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተማሪዎቜ ትምህርት ቀት ገብተው ትምህርት መኚታተል ነው እንጂ ኚስልክ ጋር ዚሚጫወቱበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ይደሹጋል " ብለዋል።


@ethioaplus
ለ150 ሺህ ተማሪዎቜ ዹ12ኛ ክፍል ፈተናን በበዹነ መሚብ ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል

ለ150ሺህ ተማሪዎቜ ዹ2017 ዓ.ም ዹ12ኛ ኹፍል ፈተናን በበዹነ መሚብ ለመስጠት ዝግጅት እዚተደሚገ መሆኑን ዚትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።በዘንድሮው ዓመት 150ሺህ ተማሪዎቜ በበዹነ መሚብ ለመፈተን ዝግጅት እዚተጠናቀቀ ነው ብለዋል።

በሀገር አቀፍ ደሹጃ 3 ሺህ 222 ትምህርት ቀቶቜ ዚማጠናኚሪያ ትምህርት እዚሰጡ ሲሆን ፈተናውን ለመውሰድ ኚተመዘገቡ 936 ሺህ 624 ተማሪዎቜ መካኚል 416 ሺህ 284 ተማሪዎቜ በ48 ሺህ 242 መምህራን ማጠናኚሪያ ትምህርት እዚተኚታተሉ እንደሚገኙ ተናግሚዋል።

በሌላ በኩል በ2016 ዓ.ም ምንም ተማሪ ኹለሰለፉ ትምህርት ቀቶቜ መካኚል 700 ትምህርት ቀቶቜ ተለይተው ዚአንድ ዓመት ሙሉ ድጋፍ በተለያዩ ዘርፎቜ እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል ብለዋል።

ኹሁሉም ክልሎቜና ኹተማ አስተዳደሮቜ በተመሚጡ 294 ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ 783 ርዕሰ መምህራን፣ 19ሺህ 566 መምህራንና 3ሺህ 628 ዚአስተዳደር ሰራተኞቜ በአጠቃላይ 23ሺህ 977 ዚትምህርት ማህበሚሰብ በተግባር ዹተደገፈ ስልጠና መሰጠቱን ገልፀዋል።

በ2016 ዓም በሀገር አቀፍ ደሹጃ ተግባራዊ ዹተደሹገውንና ውጀት ዚተገኘበትን ዚማጠናኚሪያ ትምህርት በስፋት ለመስጠት ዹንቅናቄ ሰነድ በማዘጋጀት በትኩሚት እዚተሰራ ስለመሆኑ አብራርተዋል።

በ2016 ዓም 674 ሺህ 814 ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ዚዩኒቚርስቲው መግቢያ ፈተና ወስደዋል። ኹዚህ 29ሺህ 727 ተፈታኞቜ በተመሚጡ ቊታዎቜ በበዹነ መሚብ መፈተናቾው ይታወሳል።

@ethioaplus