TIKVAH-ETHIO
702 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ለምንድነው የረሃብ አድማ እያደረጉ የሚገኙት ?
የጤናቸው በሁኔታ ላይ ይገኛል ?
የተካሄዱት ሰልፎች ጉዳይ ?

* ዘግየት ብሎ ከ Oromo Prisoners Defense Team ባገኘነው ሪፖርት ላለፉት 12 ቀናት በረሃብ አድማ ላይ ከሚገኙት መካከል አቶ ሸምሰዲን ጠሃ በአድማው በመዳከሙ ምክንያት ከምሽቱ 3:00 ላይ ከቃሊቲ እስር ቤት ወደ ሆስፒታል በአንቡላንስ ተወስዷል። በአጠቃላይ አድማውን እያደረጉ ያሉት 20 ሲሆኑ ሌሎችም ያሉበት ሁኔታ እጅግ በጣም አሳሳቢ መሆኑ ተገልጿል።

https://telegra.ph/TikvahFamily-02-08-2

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
"4 የታጠቁ ሰዎች መኪናችንን ዘረፉን" - የቲክቫህ አባላት

መነሻውን ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ያደረገ የታርጋ ቁጥር 22984 "ሀይሮፍ መኪና" በ4 መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች እንደተዘረፈባቸው የመኪናው ባለቤቶች የሆኑ የቲክቫህ አባላት ጠቁመዋል።

አራቱ ሰዎች መኪናውን ኮንትራት ይዘው ይጓዙ የነበረ ሲሆን ወደ አዲስ አበባ ሊገባ ሲል ሹፌሩ እና ረዳቱን በመደብደብ መኪናውን ሰርቀው ጠፍተዋል።

መኪናው የተዘረፈባቸው አባላቶቻችን ጉዳዩን ለፖሊስ ያሳወቁ ሲሆን ከላይ በተገለፀው የታርጋ ቁጥር መኪና ያየ ካለ 0949908233 ወይም በአካባቢው ለሚገኙ የህግ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

#TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#Update

ምርጫ ቦርድ የሰማያዊ ሳጥን ተከፍቶ ውስጡ ያለው የድምጽ መስጫ ወረቀት ማሸጊያው ባለመከፈቱ ምክንያት የምርጫ ሂደቱ እንዲቀጥል የተወሰነባቸው የምርጫ ክልሎች ስለመኖራቸው አሳውቋል።

እነዚህም ፦

• ስንቄ 1 እና 2 የምርጫ ቁሳቁስ ሳጥኑ (ሰማያዊ ሳጥን) ወድቆ በመሰበሩ የተወዳዳሪ ፖርቲዎች ወኪል ባሉበት ቃለጉባኤ ተይዞ የድምፅ መስጫ ወረቀቱ የታሸገው ባለመከፈቱ ምርጫው እንዲካሄድ ተወስኗል።

ይህ ምርጫ ጣቢያ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የሚወዳደሩበት ነው።

• መተማ ላይ የምርጫ ቁሳቁስ መያዣ ሳጥኑ (ሰማያዊ ሳጥኑ) ቢነካካም የድምጽ መስጫ ወረቀቶቹ ማሸጊያ ባለመከፈቱ ምርጫው እንዲቀጥል ቦርዱ ወስኗል።

#SolianShimeles #TikvahEthiopia #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#ማስጠንቀቂያ

የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ታሽጎ የሚሄድበትን ሳጥን ፦
- መክፈት
- ማንቀሳቀስ
- መቁረጥ
- ውስጡን ማየት ከፍተኛ የሆነ #ወንጀል ነው።

ምርጫ ቦርድ ለሁሉም ምርጫ አስፈፃሚዎች፣ ወረዳ ላይ ያሉ ዝቅተኛ እርከን ላይ የሚሰሩ የመንግስት አካላት (ይከፈት እንየው የሚሉ) በሙሉ ከፍተኛ #ማስጠንቀቂያ ሠጥቷል።

በማንኛውም ሁኔታ በምርጫ ክልሎች ላይ ችግር ተፈጥሮ ከተገኘ ወደድጋሚ ምርጫ እንደሚሄድ መታወቅ አለበት ብሏል ቦርዱ ፤ አክሎም የድጋሚ ምርጫ ለሀገር ሃብት ጠቃሚ ስላልሆነ፣ ቦርዱም ብዙ ገንዘብ ስለሚያባክን ከድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ጋር በተገናኘ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopia #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
Audio
AudioLab
#መግለጫ

የእስካሁኑን የምርጫ ሂደት በተመለከተ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ የሰጡን መግለጫ።

#TikvahFamily #TikvahEthiopia

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#ETHIOPIA😷

ሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 ተጨማሪ 21 ዜጎችን በኮቪድ-19 ሳቢያ አጥታለች።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 21 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 4,743 የላብራቶሪ ምርመራ ደግሞ 248 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 601 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#ETHIOPIA😷

ሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 ተጨማሪ 20 ዜጎችን በኮቪድ-19 ሳቢያ አጥታለች።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 20 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 5810 የላብራቶሪ ምርመራ ደግሞ 386 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 555 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA

@ETHIO_TIKVHA