መንበር ሚዲያ
560 subscribers
78 photos
3 videos
44 links
@መንበር ሚዲያ
Download Telegram
በዚችም ቀን የክብር ባለቤት የሆነው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ አለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ የአለም ፈጣሪ የሁሉ ህዢ ሁሉ በእጁ የሆነ አምላክ በቀራንዮ አደባባይ በዕፀ መስቀል ላይ እጆቹ ተዘርግተው ችንካር ላይ ዋሉ መከራ እንግልት ግርፋት ደረሰበት ፈጣሪዋ እጆቹ ተዘርግቶ በአየችው ሰዓት ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም  የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው  ነው እንዳለ ነፍሱ  ከመለኮት ሳትለይ  ከሥጋ ተለየች በዚያ ግዜ  ሥጋ ከመለኮት ሳትለይ በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑለ ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ  ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና  የክብር ክብር ገንዘቡ የሆነ ራሱን ስውቶ ያዳነን  የመንግሥቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ የከፈተልን ለእርሱ ስግደት አምልኮት ይገባዋል ለዘላለሙ የመስቀሉ በረከት በላያችን ላይ ይደር እያልኩ በዛሬው ዕለት ይኽን ታላቅ ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በመሐል ስድስት ኪሎ አንድነቱ እና ገዳማዊ ሕይወትን ጠብቆ ለዘመናት የቆየው ታላቁ ገዳማችን ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል ክፍል ትምህርተ ወንጌል ለሁሉም ይድረስ ዘንድ በማሰብ ለሁለት ቀን የተዘጋጀውን ጉባዔ የመዝግያ መርሐ ግብር ተከናውኗል በጉባዔውም መምህራን ወንጌል ስለ ይቅርታ ስለሰላም ስለፍቅር በደንብ አበክረው አስተምረዋል ዘማሪዎችም ወቅቱን የዋጀ ሕማም መስቀሉን መከራውን እንግልት ስቃዩን  የሚገልጹ መዝሙሮች ተዘምረው በገዳሙ አስተዳደር መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ እና በገዳሙ አበው መነኮሳት በጸሎት እና በምስጋና  የጉባኤው ፍጻሜ ነበር  በተለየየ የሥራ መደራረብ እና በቦታው ተገኝታችሁ ጉባኤውን መታደም ላልቻላችሁ መንበር ሚዲያ በዩቱዩብ ቻናል በቅርብ ቀን ስለሚለቀቅ like share subscrib በማድረግ ዕለታዊ እና ወቅታዊ ትምህርተ ወንጌልን ከአውደ ምህረቱ ሳይሸራረፍ በቀጥታ ያገኛሉ መንበር ሚዲያን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን