ደግነትን ላስተማራችሁን።
በአድዋ ኪዳን ላስተሳሰራችሁን።
ባርነትን ሳይሆን ነፃነትን ላወረሳችሁን።
አንገታችንን ቀና አድርገን እንድሄድ ላስቻላችሁን።
የአሸናፊነት ስነ - ልቦና እንዲነግስብን ላደረጋችሁ።
ለጥቁር የሰው ዘር ነጭን ማሸነፍ እንደሚቻል በቃል'ም በተግባር'ም ላሳያችሁ ለእናንተ ውለታችሁን መክፈል ባንችል'ም ሁሌ በልባችን ዝንት ዓለም ነግሳችሁ ትኖራላችሁ!!! የዛሬዋ ቀን እምዬ ምኒልክ ፣ እቴጌ ጣይቱ ፣ ፊት አውራሪ ገበየሁ ለእኛ ገፀ በረከት ይሆኑ ዘንድ በኢትዮጵያ ምድር የተወለዱባት ልዮ ቀን ናት።
💚 @ethale 💚
💛 @ethale 💛
❤️ @ethale ❤️
በአድዋ ኪዳን ላስተሳሰራችሁን።
ባርነትን ሳይሆን ነፃነትን ላወረሳችሁን።
አንገታችንን ቀና አድርገን እንድሄድ ላስቻላችሁን።
የአሸናፊነት ስነ - ልቦና እንዲነግስብን ላደረጋችሁ።
ለጥቁር የሰው ዘር ነጭን ማሸነፍ እንደሚቻል በቃል'ም በተግባር'ም ላሳያችሁ ለእናንተ ውለታችሁን መክፈል ባንችል'ም ሁሌ በልባችን ዝንት ዓለም ነግሳችሁ ትኖራላችሁ!!! የዛሬዋ ቀን እምዬ ምኒልክ ፣ እቴጌ ጣይቱ ፣ ፊት አውራሪ ገበየሁ ለእኛ ገፀ በረከት ይሆኑ ዘንድ በኢትዮጵያ ምድር የተወለዱባት ልዮ ቀን ናት።
💚 @ethale 💚
💛 @ethale 💛
❤️ @ethale ❤️
🥰2
የምስራች!
ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ቋንቋ ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ክፍል የማስተማሪያ መጻሕፍት እየተመረቀ ይገኛል ! በሀገርም በቤተ ክርስቲያንም ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ቋንቋ ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚውል 10 የማስተማሪያ መጻሕፍት ታትሞ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ እየተመረቀ ይገኛል።
የመጽሐፍቱ ዝግጅት 15 ዓመታት እንደፈጀ የመጻሕፍቱ አዘጋጅ የሆነችው መምህርት ኑኃሚን ዋቅጅራ ለተ.ሚ.ማ በሰጠችው ቃለመጠይቅ ገልጻለች።እስከ 12ተኛው ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ የነበረው የግዕዝ ቋንቋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአደራ እናት ሆና ጠብቃ አቅፋ የያዘችው እና እየተገለገለችበትም ነው ያለችው መምህርቷ የግዕዝ ቋንቋ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ብቻ እና የአንድ ማኅበረሰብ ብቻ ተደርጎ የሚታሰበው ልክ አለመሆኑን ገልጻ ዛሬ ላይ ያጣነውን ማንነት ለማግኘት ወደ ትላንት መመለስ አለብን ስለዚህም ሁሉም ሰው እና ታዳጊ ህፃናት የግዕዝ ቋንቋን እንዲማሩ ታስቦ መጻሕፍቱ ታትመው መመረቃቸውን መምህርቷ ገልጻለች።
መምህርት ኑኃሚን አክላም "ሁሉም ሰው በመጻሕፍቱ እንዲማር እና የግዕዝ ቋንቋን እንዲያውቅ መልዕክት አስተላልፋለች።በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፤ መምህራነ ወንጌል እንዲሁም ዘማርያን ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እና በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።
መምህርት ኑኃሚን ዋቅጅራ በስፔሻል ኒድ የመጀመሪያ ዲግሪ ከዲላ ዩኒቨርስቲ ፣ በነገረ መለኮት የመጀመሪያ ዲግሪ ከቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በግዕዝ ሥነ ድርሳን በማስተርስ ዲግሪ ተመርቃለች።
@ethale
ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ቋንቋ ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ክፍል የማስተማሪያ መጻሕፍት እየተመረቀ ይገኛል ! በሀገርም በቤተ ክርስቲያንም ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ቋንቋ ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚውል 10 የማስተማሪያ መጻሕፍት ታትሞ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ እየተመረቀ ይገኛል።
የመጽሐፍቱ ዝግጅት 15 ዓመታት እንደፈጀ የመጻሕፍቱ አዘጋጅ የሆነችው መምህርት ኑኃሚን ዋቅጅራ ለተ.ሚ.ማ በሰጠችው ቃለመጠይቅ ገልጻለች።እስከ 12ተኛው ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ የነበረው የግዕዝ ቋንቋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአደራ እናት ሆና ጠብቃ አቅፋ የያዘችው እና እየተገለገለችበትም ነው ያለችው መምህርቷ የግዕዝ ቋንቋ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ብቻ እና የአንድ ማኅበረሰብ ብቻ ተደርጎ የሚታሰበው ልክ አለመሆኑን ገልጻ ዛሬ ላይ ያጣነውን ማንነት ለማግኘት ወደ ትላንት መመለስ አለብን ስለዚህም ሁሉም ሰው እና ታዳጊ ህፃናት የግዕዝ ቋንቋን እንዲማሩ ታስቦ መጻሕፍቱ ታትመው መመረቃቸውን መምህርቷ ገልጻለች።
መምህርት ኑኃሚን አክላም "ሁሉም ሰው በመጻሕፍቱ እንዲማር እና የግዕዝ ቋንቋን እንዲያውቅ መልዕክት አስተላልፋለች።በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፤ መምህራነ ወንጌል እንዲሁም ዘማርያን ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እና በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።
መምህርት ኑኃሚን ዋቅጅራ በስፔሻል ኒድ የመጀመሪያ ዲግሪ ከዲላ ዩኒቨርስቲ ፣ በነገረ መለኮት የመጀመሪያ ዲግሪ ከቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በግዕዝ ሥነ ድርሳን በማስተርስ ዲግሪ ተመርቃለች።
@ethale
አጼ ዘረ ያዕቆብ በወርቅ ቀለም ያስጻፏት የብራና መጻሕፍ።በጥንታዊት ኢትዮጵያ በወርቅ እንደ ምድር አሽዋ የነበረበት ደግ ዘመን።ስለ ግሸኗ ተዓምረ ማርያም ያልተነገሩ ምስጢሮች ....በእንባ መጻሕፍ ያስጻፉት ንጉስ...በወርቅ ቀለም የተሰሩ አብያተ ክክርቲተያኖችናሌሎች ያልተሰሙ ታሪኮች አዲስ በከፈትነው የዩቲዮብ ቻናል ይዘንላችሁ መጠናል ሀሳብ አስተያይታችሁን አጋሩን ።ሌሎች ዝግጅቶች እንዲደርስዎ subscribe ያድርጉ።
https://youtu.be/H8HPn8gIuSs
https://youtu.be/H8HPn8gIuSs
YouTube
በወርቅ ቀለም የተጻፉ የብራና መጻሕፍት
አጼ ዘረ ያቆብ በወርቅ ቀለም ያስጻፏት የብራና መጻሕፍ።በጥንታዊት ኢትዮጵያ በወርቅ እንደ ምድር አሽዋ የነበረበት ደግ ዘመን።ስለ ግሸኗ ተዓምረ ማርያም ያልተነገሩ ምስጢሮች።በወርቅ ቀለም የተሰሩ አብያተ ክርስትያኖች።
👍2
ቤተ ክርስቲያኔን ሳያት ኢትዮጵያን ዐያታለሁ!
ኢትዮጵያን ኦርቶዶክሳውያን የበለጠ የሚወድዷት በነገረ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአግባቡ ስለምትጠቀስ ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያኔን ሳያት ኢትዮጵያን ዐያታለሁ፡፡ እንኳን እና ኦርቶዶክሳውያን ቀርቶ ሌሎች መጽሐፍ
ቅዱስን የሚመለከቱ ሁሉ ኢትዮጵያን ያዩአት ዘንድ ይገደዳሉ፡፡
ኢትዮጵያ ጉልኅ ናት፣ ኢትዮጵያም ምስጢር ናት፡፡ ኢትዮጵያን አጉልታ የምታሳየኝ ቤተ ክርስቲያኔ እንደኾነች ሁሉ ምስጢርነቷንም የምትተረጉምልኝ ቤተ ክርስቲያኔ ናት፡፡ ኢትዮጵያዊነትን ኹለት ጊዜ ተቀብያለሁ፡፡ አንድ ጊዜ ከአባቴ አብራክ ከእናቴ ማኅፀን ስከፈል ሌላ ጊዜ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ስወለድ፡፡ እናም የሀገሬን ነገር ከቤተ ክርስቲያኔ ልነጥለው አልችልም፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ከብሉይ እስከ ሐዲስ ሳይታክት የሚያነሣሣትን የቅድስት ሀገር ነገር ትቼ መኖር አልፈልግም አልችልምም፡፡
የመጀመሪያው መጽሐፍ የመጽሐፈ ሔኖክ ሀልዎት ያለ ኢትዮጵያ ምሉዕ አይደለም፡፡ የአበ ብዙኀን አብርሃም ታሪክ ያለ ኢትዮጵያ ከዳር አይደርስም፡፡ የሊቀ ነቢያት መጻሕፍተ ኦሪት ዘፍጥረት፣ ዘጸአት እና ዘኁልቊ ያለ ኢትዮጵያ ይጎድላሉ፡፡ የቃል ኪዳኑ ታቦት ታሪክ ኢትዮጵያ ካልገባችበት ዝርው ይኾናል፡፡ የሊቀ ነቢያት ሙሴ ሕይወት ከኢትዮጵያ ጋር ካልተቆራኘ ይጎድላል፡፡ ገና እንደተወለደ እናቱ በሣጥን አድርጋ የዓባይ ወንዝ ላይ ስትጥለው የሚጀምረው ታሪኩ ኢትዮጵያዊቷን ሲጳራ የትዳር አጋሩ እስከማድረግ ይቀጥላል፡፡ በኢትዮጵያዊው ካህን ምርጥ ትምህርት አስተዳደሩን እንዳቀና ካላወቅን እንዴት የመጽሐፍ ቅዱስ ወዳጆች እንባል ዘንድ እንችላለን?
ቅዱስ ዳዊት በምጡቅ መዝሙሩ፣ ቅኔው እና ትንቢቱ ኢትዮጵያን ከፍ አድርጎ ይሞሽራታል፡፡ መጻሕፍተ ነገሥት ኢትዮጵያን ከፍ አድርገው ካላሳዩ አይኾንላቸውም፡፡ የጠቢቡ ሰሎሞን ዜና መዋዕል ኢትዮጵያን ካላነሣ ያነክሳል፡፡ ከዐበይት እስከ ደቂቀ ነቢያት ኢትዮጵያ የትንቢታቸው ማዕከል ናት፡፡ ነቢየ ልዑል ኢሳይያስን ጠይቁት ነቢዩ ሶፎንያስን ወይም ነቢዩ ዕንባቆምን፡፡ ነቢዩ ኤርሚያስ ከኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ ታሪክ አንፃር ኢትዮጵያን እንዴት ቀሽሮ እንደገለጣት እንጠይቀው፡፡ ትንቢተ ኤርሚያስ ያለ ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አድራሻውን ያጣል፡፡ ወንጌለ ክርስቶስ ልደተ ክርስቶስን ሲያመጣው እዚያ
ውስጥ ኢትዮጵያ በደርዝ ገብታለች፡፡
ከሰብአ ሰገል አንዱ ኢትዮጵያዊ ነውና! ጌታም በንግሥተ አዜብ ወይም በንግሥተ ሳባ እርሷም ንግሥት ማክዳ በተባለችው አድርጎ የምድር ዳርቻ ሲል ይጠቅሳታል፡፡ ቅዱስ ሉቃስም ግብረ ሐዋርያትን ሲጽፍ የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ እምነት ከኦሪት እስከ ሐዲስ ተንትኖልናል፡፡ እምነቱም በቅዱስ ጴጥሮስ እምነት መጠን እንደኾነ እጥር ምጥን አድርጎ ጽፏል፡፡ የዓለም ድኅነት ሕገ ልቡና፣ ሕገ ኦሪት፣ ሕገ ወንጌል ያለ ኢትዮጵያ መልክ ያጣል፡፡ እኛም እግዚአብሔር አድሎን አዚህች ሀገር ተወልደናል፡፡
ሀገረ እስራኤል ያልተመቻት ታቦተ ጽዮን መሥዋዕቷ ወደ ሰመረላት ኢትዮጵያ መጥታ ማረፊያ አግኝታለች፡፡ ለአማናዊቷ ጽዮን ድንግል ማርያምም የስደቷ ማረፊያ የኾነችው ይህችው ቅድስት ሀገር ናት እኮ፡፡ ጣና ከእነ ስሙ ጣና ቂርቆስ ገዳሙ ይናገረዋል ይህንን፡፡ በእስራኤል ከኖረችው ይልቅ በኢትዮጵያ የኖረችበት ዘመን ይልቃል፡፡ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ጠቢቡ ሰሎሞን ለ፮፻ ዓመታት ብቻ የቆየች ሲኾን ይኸው ለ፪ሺህ ፱፻ ዓመታት በኢትዮጵያ ናት፡፡ አምስት እጥፍ ያኸል ጊዜ በኢትዮጵያ ኖራለች፡፡ ዓለም አድራሻው የጠፋበት የመስቀለ ክርስቶስ ግማዱ የት ነው? ከተባለ ኢትዮጵያ ነው ሀገሩ፡፡ ሌሎቹ ወይ ታሪኩ ጠፍቶባቸዋል ወይ ተሰውሯቸዋል፡፡ ዓለም ስለመስቀሉ ዝምተኛ ሲኾን ተናጋሪ መልእክተኛ ኾና የተሰየመችው ኢትዮጵያ ብቻ ናት፡፡ እናም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ኢትዮጵያን በፍለጋ ሳይኾን በስፋት በደመቀ ታሪክ በጎላ ዕውቀት እናገኛታለን፡፡
ከቤተ ክርስቲያን ከቅጽሯ ስትደርስ ብቻ ሳይኾን ከሩቅ ጉልላቷን ስታይ ደወሏን ስትሰማ ኢትዮጵያዊነት ከላይ እስከ ታች እንደ ጠበል ይፈስስብሃል፡፡ አምስቱ ፊደላት እንደ አምስቱ አዕማደ ምስጢራት የሚተረጎምልህ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ የሰንደቅ ዓላማዋ ትርጉም የሚገባህ ቤተ ክርስቲያን ስትኖር ነው፡፡
ኢትዮጵያ ያልተፈተተች ሥረ ወጥ፣ አመንዝራነትን የተጸየፈች ግን በሕግ እየኖረች ወላድ ደግሞ ተፈትሖ ማኅፀን የሌለባት ድንግል፣ መከፈት መዘጋት ሳይኖርባት የምታስገባ የምታስወጣ፣ ምስጢረ መለኮትን በልቧ የምትጠብቅ ምስጢረኛ፣ የእግዚአብሔር ሦስት አዝማናት ብቸኛ ምሥክር መኾኗን የነገረችኝ ቤተ ክርስቲያኔ ናት።ኢትዮጵያ ብዬ የምጽፍበትንም ፊደል የሰጠችኝ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡አባይ ነህ
አንድ ሲኖዶስ ~ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስያን ቅዱስ ሲኖዶስ
• አንድ መንበር ~ መንበረ ተክለ ሃይማኖት
• አንድ ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ
• አንዲት ሃገር… ኢትዮጵያ 💚💛❤️
"…ሐዋርያት በሰበሰቡአት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን" ጸሎተ ሃይማኖት
⚫️ @ethale ⚫️
ኢትዮጵያን ኦርቶዶክሳውያን የበለጠ የሚወድዷት በነገረ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአግባቡ ስለምትጠቀስ ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያኔን ሳያት ኢትዮጵያን ዐያታለሁ፡፡ እንኳን እና ኦርቶዶክሳውያን ቀርቶ ሌሎች መጽሐፍ
ቅዱስን የሚመለከቱ ሁሉ ኢትዮጵያን ያዩአት ዘንድ ይገደዳሉ፡፡
ኢትዮጵያ ጉልኅ ናት፣ ኢትዮጵያም ምስጢር ናት፡፡ ኢትዮጵያን አጉልታ የምታሳየኝ ቤተ ክርስቲያኔ እንደኾነች ሁሉ ምስጢርነቷንም የምትተረጉምልኝ ቤተ ክርስቲያኔ ናት፡፡ ኢትዮጵያዊነትን ኹለት ጊዜ ተቀብያለሁ፡፡ አንድ ጊዜ ከአባቴ አብራክ ከእናቴ ማኅፀን ስከፈል ሌላ ጊዜ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ስወለድ፡፡ እናም የሀገሬን ነገር ከቤተ ክርስቲያኔ ልነጥለው አልችልም፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ከብሉይ እስከ ሐዲስ ሳይታክት የሚያነሣሣትን የቅድስት ሀገር ነገር ትቼ መኖር አልፈልግም አልችልምም፡፡
የመጀመሪያው መጽሐፍ የመጽሐፈ ሔኖክ ሀልዎት ያለ ኢትዮጵያ ምሉዕ አይደለም፡፡ የአበ ብዙኀን አብርሃም ታሪክ ያለ ኢትዮጵያ ከዳር አይደርስም፡፡ የሊቀ ነቢያት መጻሕፍተ ኦሪት ዘፍጥረት፣ ዘጸአት እና ዘኁልቊ ያለ ኢትዮጵያ ይጎድላሉ፡፡ የቃል ኪዳኑ ታቦት ታሪክ ኢትዮጵያ ካልገባችበት ዝርው ይኾናል፡፡ የሊቀ ነቢያት ሙሴ ሕይወት ከኢትዮጵያ ጋር ካልተቆራኘ ይጎድላል፡፡ ገና እንደተወለደ እናቱ በሣጥን አድርጋ የዓባይ ወንዝ ላይ ስትጥለው የሚጀምረው ታሪኩ ኢትዮጵያዊቷን ሲጳራ የትዳር አጋሩ እስከማድረግ ይቀጥላል፡፡ በኢትዮጵያዊው ካህን ምርጥ ትምህርት አስተዳደሩን እንዳቀና ካላወቅን እንዴት የመጽሐፍ ቅዱስ ወዳጆች እንባል ዘንድ እንችላለን?
ቅዱስ ዳዊት በምጡቅ መዝሙሩ፣ ቅኔው እና ትንቢቱ ኢትዮጵያን ከፍ አድርጎ ይሞሽራታል፡፡ መጻሕፍተ ነገሥት ኢትዮጵያን ከፍ አድርገው ካላሳዩ አይኾንላቸውም፡፡ የጠቢቡ ሰሎሞን ዜና መዋዕል ኢትዮጵያን ካላነሣ ያነክሳል፡፡ ከዐበይት እስከ ደቂቀ ነቢያት ኢትዮጵያ የትንቢታቸው ማዕከል ናት፡፡ ነቢየ ልዑል ኢሳይያስን ጠይቁት ነቢዩ ሶፎንያስን ወይም ነቢዩ ዕንባቆምን፡፡ ነቢዩ ኤርሚያስ ከኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ ታሪክ አንፃር ኢትዮጵያን እንዴት ቀሽሮ እንደገለጣት እንጠይቀው፡፡ ትንቢተ ኤርሚያስ ያለ ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አድራሻውን ያጣል፡፡ ወንጌለ ክርስቶስ ልደተ ክርስቶስን ሲያመጣው እዚያ
ውስጥ ኢትዮጵያ በደርዝ ገብታለች፡፡
ከሰብአ ሰገል አንዱ ኢትዮጵያዊ ነውና! ጌታም በንግሥተ አዜብ ወይም በንግሥተ ሳባ እርሷም ንግሥት ማክዳ በተባለችው አድርጎ የምድር ዳርቻ ሲል ይጠቅሳታል፡፡ ቅዱስ ሉቃስም ግብረ ሐዋርያትን ሲጽፍ የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ እምነት ከኦሪት እስከ ሐዲስ ተንትኖልናል፡፡ እምነቱም በቅዱስ ጴጥሮስ እምነት መጠን እንደኾነ እጥር ምጥን አድርጎ ጽፏል፡፡ የዓለም ድኅነት ሕገ ልቡና፣ ሕገ ኦሪት፣ ሕገ ወንጌል ያለ ኢትዮጵያ መልክ ያጣል፡፡ እኛም እግዚአብሔር አድሎን አዚህች ሀገር ተወልደናል፡፡
ሀገረ እስራኤል ያልተመቻት ታቦተ ጽዮን መሥዋዕቷ ወደ ሰመረላት ኢትዮጵያ መጥታ ማረፊያ አግኝታለች፡፡ ለአማናዊቷ ጽዮን ድንግል ማርያምም የስደቷ ማረፊያ የኾነችው ይህችው ቅድስት ሀገር ናት እኮ፡፡ ጣና ከእነ ስሙ ጣና ቂርቆስ ገዳሙ ይናገረዋል ይህንን፡፡ በእስራኤል ከኖረችው ይልቅ በኢትዮጵያ የኖረችበት ዘመን ይልቃል፡፡ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ጠቢቡ ሰሎሞን ለ፮፻ ዓመታት ብቻ የቆየች ሲኾን ይኸው ለ፪ሺህ ፱፻ ዓመታት በኢትዮጵያ ናት፡፡ አምስት እጥፍ ያኸል ጊዜ በኢትዮጵያ ኖራለች፡፡ ዓለም አድራሻው የጠፋበት የመስቀለ ክርስቶስ ግማዱ የት ነው? ከተባለ ኢትዮጵያ ነው ሀገሩ፡፡ ሌሎቹ ወይ ታሪኩ ጠፍቶባቸዋል ወይ ተሰውሯቸዋል፡፡ ዓለም ስለመስቀሉ ዝምተኛ ሲኾን ተናጋሪ መልእክተኛ ኾና የተሰየመችው ኢትዮጵያ ብቻ ናት፡፡ እናም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ኢትዮጵያን በፍለጋ ሳይኾን በስፋት በደመቀ ታሪክ በጎላ ዕውቀት እናገኛታለን፡፡
ከቤተ ክርስቲያን ከቅጽሯ ስትደርስ ብቻ ሳይኾን ከሩቅ ጉልላቷን ስታይ ደወሏን ስትሰማ ኢትዮጵያዊነት ከላይ እስከ ታች እንደ ጠበል ይፈስስብሃል፡፡ አምስቱ ፊደላት እንደ አምስቱ አዕማደ ምስጢራት የሚተረጎምልህ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ የሰንደቅ ዓላማዋ ትርጉም የሚገባህ ቤተ ክርስቲያን ስትኖር ነው፡፡
ኢትዮጵያ ያልተፈተተች ሥረ ወጥ፣ አመንዝራነትን የተጸየፈች ግን በሕግ እየኖረች ወላድ ደግሞ ተፈትሖ ማኅፀን የሌለባት ድንግል፣ መከፈት መዘጋት ሳይኖርባት የምታስገባ የምታስወጣ፣ ምስጢረ መለኮትን በልቧ የምትጠብቅ ምስጢረኛ፣ የእግዚአብሔር ሦስት አዝማናት ብቸኛ ምሥክር መኾኗን የነገረችኝ ቤተ ክርስቲያኔ ናት።ኢትዮጵያ ብዬ የምጽፍበትንም ፊደል የሰጠችኝ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡አባይ ነህ
አንድ ሲኖዶስ ~ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስያን ቅዱስ ሲኖዶስ
• አንድ መንበር ~ መንበረ ተክለ ሃይማኖት
• አንድ ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ
• አንዲት ሃገር… ኢትዮጵያ 💚💛❤️
"…ሐዋርያት በሰበሰቡአት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን" ጸሎተ ሃይማኖት
⚫️ @ethale ⚫️
❤4👍4👏1
መፅሐፈ ፍልስፍና ሥጋዊ ወመንፈሳዊ.pdf
17.3 MB
ከመቶ ሀምሳ ዓመት በፊት የአጼ ቴዎድሮስ ጸሐፌ ትዕዛዝ የነበሩት አለቃ ዘነብ ኢትዮጵያዊ አማካኝነት የተጻፈ ድንቅ የፍልስፍና መጻሕፍ ነው።
@ethale
@ethale
@ethale
@ethale
@ethale
@ethale
❤8👍3
