✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.05K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
ፍልሰታ ማለት ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ
ቦታ ማዛወር የነበሩበትን ሀገር ለቆ ወደ ሌላ ሀገር መሰደድ መፍለስ ማለት ነው፡፡
ጾመ ፍልሰታ ሲባልም የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለስን
በኋላም በገነት በእፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት ሲባል ነው
የሚነገርነው፡፡
21
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 64 ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ በሞት
ከተለየች በኋላ እንደ አንድ ልጅዋ ሞታ መነሣቷንና እርገቷን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት
ከነሐሴ 1 እስከ 16 የጾሙት ጾም ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ከሰባቱ አበይት አጽዋማት
አንዱ ሆኖ በቀኖና እንዲጾም ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ምእመናን ይጾሙታል፡፡
እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐና “እም ሊባኖስ ትወጽእ
መርዓት(ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች)” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን
ተጸነሰች፡፡ ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ወረዳ በብጽአት እንደተወለደች
የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ እመቤታችን በጾም በጸሎት
በአስተብቁዖት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ እግዚአብሔር
ሆናለች፡፡
እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ከዮሐንስ
ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር ጠቅላላ ድምር 64 ዓመት
ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
21 21 21
ነቢያት አስቀድመው ስለ እመቤታችን እረፍትና ትንሳኤ በምሥጢር ተናግረዋል፡፡
ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ፡- መዝ 136፡8 “አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነሥ አንተና
የመቅደስህ ታቦት” ብሎአል፡፡ ፈጣሪዬ ሆይ ምእመናንን ወደምታሳርፍበት ወደ
መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህን ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ ሲል
ነው፡፡ ይህም እመቤታችን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ መነሣቷን የሚያመለክት ነው፡፡
ታቦት ያላትም ማደሪያው ስለሆነች ነው፡፡
16
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይ እነሆ ክረምት አለፈ
ዝናቡም አልፎ ሄደ አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፡፡ የዜማም ጊዜ ደረሰ የቀረ…
ቃል በምድራችን ተሰማ፡፡ በለሱ ጐመራ ወይኖችም አበቡ መዓዛቸውንም ሰጡ፡፡
ወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይ” ሲል ስለ እመቤታችን በምሳሌ ተናግሮአል፡፡
መኃ2፡10-13
+
ወዳጁን ውበቱን ተነሺ ነይ እያለ የተጣራው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ተጠሪዋም
እመቤታችን ናት፡፡ እነሆ ክረምት አለፈ ማለት በስደት በአይሁድ የዘወትር
ጠላትነት በልጅዋ መከራና ስቅላት ስምዖን በቤተ መቅደስ እንደተናገረ ልቧ
በሀዘን ሠይፍ የተከፈለበት በሀዘን ፍላጻ የተወጋበት የመከራ ክረምት /ወቅት/
አልፎ የክርስቶስ ሕማሙ ፣ ሞቱ፣ ቤዛነቱ ተፈጽሟል፡፡ ትንሣኤው በምድር ላይ
ተገልጧል፣ ተሰብኳል ማለት ነው፡፡ በምድራችን አበባ ታይቷል ማለት የሐዋርያት
ድምፅ በምድር ሁሉ ደርሷል ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹ ድምፃቸው ወደ ምድር
ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ › ብሎ ስለ ሐዋርያት የተናገረው
በዓለም ያለውን መከራ ስደት ሲገልጽ ነው፡፡ /መዝ 18¸4/
+
‹የዜማም ጊዜ ደረሰ ያለው የመከራን ጊዜ ነው፡፡ ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ
በደስታ ይጮሃሉ፣ ይዘምራሉም› ተብሏል፡፡ መዝ 14፡13 የመከር ጊዜ ደረሰ
የተባለው መከር የፍሬ ጊዜ በመሆኑ ክርስትና አፍርቷል ማለት ነው፡፡ በለሱ
ጐመራ ማለት ደግሞ በጐ ምግባረ ፍሬ ሳያፈሩ የነበሩ ሰዎች በጐ ምግባር
መሥራት መጀመራቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በመጨረሻም ወይኖች አብበዋል፣
መዓዛቸውንም ሰጥተዋል እንደተባለ በመላው ዓለም አ።ብያተ ክርስቲያናት
በሃይማኖት ማበብ መዓዛ ምግባራቸውን ማቅረብ ከጀመሩ በኋላ እመቤታችን
አረፈች፡፡
21 21 21
እመቤታችን ጥር 21 ቀን እረፍት በሆነበት እለት ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ
ለማሳረፍ ወደ ጌቴሰማኒ መካነ እረፍት ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅንዓት መንፈስ
ተነሣሥተው “ቀድሞ ልጅዋን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ፡፡ በአርባኛው ቀን
ወደ ሰማይ አረገ፡፡ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል፡፡ እያሉ
በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት
እርሷንም እንደ ልጅዋ ተነሣች አረገች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ
አይደለምን; ኑ ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት ” ብለው ተማክረው መጥተው
ከመካከላቸው ‹ ታውፋኒያ › የተባለው ጐበዝ አይሁዳዊ ተመርጦ ሄዶ
የእመቤታችንን ሥጋ የተሸከሙትን አልጋ ሽንኮር ያዘ፡፡ የአልጋውን ሽንኮር በያዘ
ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሠይፍ ሁለት እጁን ስለ ቆረጣቸው
ከአልጋው ሽንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ ‹ ታውፋንያ › በፈጸመው ድርጊት
ተጸጽቶ ወደ እመቤታችን ስለተማጸነ በኅቡእ ተአምር የተቆረጡ እጆቹን እንደ
ቀድሞ አድርጋ ፈውሳዋለች (ስንክሳር ዘጥር፡፡)
+
የእግዚአብሔር መልአክ የእመቤታችን ሥጋ ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ተድላ ደስታ
ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቁ፡፡ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ ታወጣ
ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፡፡ እነርሱም
ትወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት፡፡ ያን ጊዜም ከእፅ ሕይወት በታች ካለ
መቃብር የእመቤታችን የማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ ጌታችንም ዘላለማዊ ወደሆነ
መንግሥተ ሰማያት መላእክት እና ሰማእታት እየሰገዱላት አሳረጓት፡፡ ንጉሥ
ዳዊት “በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋ ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች”
እንዳለ፡፡ መዝ 44፡9
+
ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ተመልሶ ከሰማይ ወረደ፡፡
ሐዋርያት ተሰብስበው ስለ እመቤታችን ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡
እርሱም እንዳየ እንደሰማ ሥጋዋም በታላቅ ክብር ማረጉን ነገራቸው፡፡
ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ፡፡ የነሐሴም ወር በባተ /በገባ/ ቀን ዮሐንስ እንዲህ
አላቸው፡፡ የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት ኑ፤ ሁለት ሱባኤ በመጾም እንለምን
አለ፡፡ በጾም በጸሎት ሱባኤ ያዙ፤ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ አምጥቶ
ስለሰጣቸው በታላቅ ዝማሬ፣ በውዳሴና በጽኑ ምሕላ ወስደው ቀድሞ በተዘጋጀው
መካነ እረፍት በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡
16 16 16
የእመቤታችን የቀብር ሥነ ሥርዓት በተፈጸመ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ቶማስ
አልነበረምና ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ
እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ
ያገኛታል፡፡ ትንሣኤዋን ሌሎቹ ሐዋርያት አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት
ተበሳጭቶ “በመጀመሪያ የልጅሽን ትንሣኤ አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሳኤ ሳላይ
ቀረሁ” ብሎ ከማዘኑ የተነሣ ከደመናው ተወርውሮ ሊወድቅ ቃጣው፡፡
እመቤታችንም ከእርሱ በቀር ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሳኤዋን እንዳላዩ ነግራው
አጽናንታው ሄዶም ለሐዋርያት የሆነውን ሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው ምልክት
ይሆነው ዘንድ ሰበኗን -መግነዟን ሰጥታው አረገች፡፡
+
ሐዋርያው ቶማስም ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ እመቤታችንን እኮ ቀበርናት ብለው
ነገሩት እርሱም “ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይሆናል?” አላቸው፡፡ “አንተ
እንጂ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንምን;” ብለው በቅዱስ
ጴጥሮስ መሪነት ወደ እመቤታችን መካነ መቃብር ይዘውት ሄደው መቃብሩን
ቢከፍቱ ሥጋዋን አጡት፡፡ ደነገጡም፡፡ ቶማስም “አታምኑኝም ብዬ እንጂ
እመቤታችን ተነሥታ አርጋለች” ብሎ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፡፡ ለማረጋገጫ
ምልክት እንዲሆን የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡ ሰበኗን - መግነዟን ለበረከት
ቆራርጠው ከተከፋፈ
ሉ በኋላ ወደ የአህጉረ ስብከታቸው ሄደዋል፡፡
+
ሐዋርያትም ትንሣኤሽን ቶማስ አይቶ እኛ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ
አንድ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገቡ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ በነሐሴ አሥራ ስድስት ቀን
ጌታችን ጸሎታቸውን ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቅ
ረዳት ቄስ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ ዋና ዲያቆን አድርጐ ቀድሶ ሁሉንም
ከአቆረባቸው በኋላ የእመቤታችንን እርገቷን ለማየት አብቅቷቸዋል፡፡
21 21 21
ቤተክርስቲያናችንም ሥርዓት ሠርታ ከሰባቱ ዓበይት አጽዋማት ተርታ አስገብታ
ይህን ታላቅ የበረከትና የምሥጢር መግለጫ ጾም እንድንጾም አድርጋናለች፡፡
ሐዋርያት ያዩትን ድንቅ ምሥጢር የእመቤታችንን ትንሳኤና እርገት ለማየትና
ከሐዋርያት አበው በረከት ለመሳተፍ ጌታችን “ልጆቼ” ይላቸው ለነበሩ ሐዋርያት
አምሳል ሕፃናትና ወጣቶች፣ ሴቶችና ወንዶች፣ አረጋውያንም የጻመ ፍልሰታን
መድረስ በናፍቆት እየጠበቁ በየዓመቱ በጾም በጸሎት ያሳልፉታል፡፡
+
የእመቤታችን ትንሣኤና እርገት መታሰቢያ - በጾመ ፍልሰታ ወቅት ብዙዎች
ከቤታቸው ተለይተው በመቃብር ቤት ዘግተው፣ አልጋና ምንጣፍ ትተው፣ በመሬት
ላይ ተኝተው ዝግን ጥሬ እፍኝ ውኃ እየቀመሱ በጾምና በጸሎት በመትጋት በታላቅ
ተጋድሎ ይሰነብታሉ፡፡ በሰሙነ ፍልሰታ ምእመናን ለእመቤታችን ያላቸውን ጽኑና
ጥልቅ ፍቅር የሚያሳዩበት ነው፡፡
+
ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር ቆይቶ ሙስና መቃብር
ሳያገኘው፣ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በሥልጣኑ እሑድ በመንፈቀ
ሌሊት እንደተነሣ ሁሉ እርሷም በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማኅደረ መለኮት
ናትና ሙስና መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል
የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗት መነሣቷን ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ፤ እንደ
ልጅዋ ትንሣኤ” ነው ተብሎ ሲከበርላት ይኖራል፡፡
+ + +
በዚሁ በነሐሴ 16 ቀን የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሰቱ ነው፡፡ ሥጋው ከፋርስ
ሀገር ወደ ሀገሩ ወደ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው፡፡ ፍልሰቴን ከፍልሰትሽ
አድርጊልኝ፣ ብሎ ለምኗት ስለነበር ፍልሰቱ ከእመቤታችን ፍልሰት ጋር
እንዳሰበው ሆኖለታል፡፡ ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥእሉን ከሥእሏ
አጠገብ ይስላሉ፡፡ በስሙ ለሚማጸኑ የድኅነት ወደብ ይሆን ዘንድ፡፡
Forwarded from Deleted Account
ከ ኢትዮ ሶማሌ ክልል ለተጎዱ ቤተ ክርስቲያናትና ለተሰው ሰማዕታት ቤተሰቦችማቋቋሚያ ይሆን ዘንድ በቤተክርስቲያናችን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ተከፍቷል ሁላችሁም እጃችሁን ዘርጉ እንላለን።
አካውንት ቁጥር 1000254922898

የሞቱትን ነብሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን።

ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ሼር በማድረግ ግዴታችንን እንወጣ

╔═★══════════📄══╗
@Zemaryan
@Zemaryan
@Zemaryan
╚══📃══════════★═╝
የቆራጥነት መልክት
@embtee
.ሁሉም ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሀይማኖቱን እሚያስከብርበት ግዜ ነው።
ብፅእ አባታችን አቡነ ዲዮስቆሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ስራ
አስኪያጅ እንዲህ የሚል የቆራጥነት መልክት አስተላልፈዋል። የኦርቶዶክስ ሀይማኖት መብት ይጠበቅ። የኦርቶዶክስ ሀይማኖት አማኞች መብት ይጠበቅ።
የኦርቶዶክስ ሀይማኖት ወጣቶች መብት ይጠበቅ። ይህ ካልሆነ ግን ከአሁን ቡሃላ ቤተ ክርስቲያን በዝምታ አታልፍም። ካህናቶቻችን ሲታረዱ አቢያተ ክርስቲይኖቻችን ሲቃጠሉ ማየት ለየ አንዳንዳችን ሞት ነው ብለዋል። እንዲህ ነው ቆራጥነት። ዛሬ ቤተ ክርስቲያ ከመቼውም በላይ መብቷን እምታስከብርበት ግዜ ነው። የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ የሆነ ሁሉ ከሁሉም በላይ ለእምነቱ ቦታ ሰጥቶ ሀይማኖቱን
የሚያስከብርበት ግዜ ነው።ዛሬ ችላ ባይነት የለም።
ዛሬ ትግስት የለም።
ዛሬ ግድየለሽነት የለም።
ዛሬ ፍራቻ የለም። @embtee
ዛሬ መጠቃት የለም።
ዛሬ መሞት የለም።
ዛሬ መናቅ የለም።
ዛሬ መዘረፍ የለም። @embtee
ዛሬ መደፈር የለም።
ዛሬ መሰደብ የለም።
ዛሬ መዘለፍ የለም።
ዛሬ ግራ ሲመታ ቀኝህን ስጥ የለም።
ሁሉም ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሀይማኖቱን እሚያስከብርበት ግዜ ነው። በመግደል ፋንታ መሞትን የመረጥነው መግደልን ስላልተማርን ነው።
@embtee
ዛሬ ግን ባንገል እንኳን እንከላከላለን። ሀይል እና ጉልበትም እንዳለንም ይታወቃል። ስለዚህ ጠላት እጅህን አንሳ ሳይገጥምህ አበሳ። በዝምታ ውስጥ ፍራቻ ሳይሆን ጀግንነትም አለ። ዝም ያለ ሁሉ ፈሪ አይደለም። ትግስት እንጂ። የቤተ ክርስቲያን መብት መጠበቅ አለበት የምትሉ አስተያየታችሁን አስቀምጡ።
ብፅእ አባታችን አቡነ ዲዮስቆሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጅ እንዲህ የሚል የቆራጥነት መልክት አስተላልፈዋል። ሀላፊነትዎን ይወጡ።
Share Share
@embtee
@embtee
936813289803913
#ማርያም♥️ #ዕጣን #ናት

#እርሷ #ዕጣን #ናት#ልጅዋ♥️ #የዕጣኑ #መዓዛ #ነው#የሰው #ልጅ #ክፉ #ሽታ የራቀባት እጣን፡ ምክንያተ ድኂን #ድንግል #ማርያም #ናት

#ጌታችንን #ዕጣን ይለዋል። " አንተ ውእቱ ዕጣን ኦ መድኅኒነ እስመ መጻእከ ወአድኅንከነ ተሳሀለነ" መድኅኒታችን ሆይ ዕጣን አነተ ነህ
🌿የ️ አቡነ ኪሮስ ታሪክ ባጭሩ 🌿❤️

🌹 በስምአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አሞላክ አሜን እንኻን አደረሳቹ ለአቡነ ኪሮስ ሰኔ 8 ️

🌿❤️ አባ ኪሮስ አባቱ ንጉስ ዮናስ እናቱ አንስራ ይባላሉ፡፡ ሀገሩ ሮም ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ወለዱ፡፡ አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡
🌿❤️ በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስቶ ወስዶ ገነት አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰቷቸዋል።
@like
🌿❤️ ቃል ኪዳናቸውም ፡- መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በህግ በስጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው ሐምሌ 8 አርፈዋል።
ረድኤት በረከታቸው አማላጅነታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
@embtee

💓💖💛💚❤️💖💞🌹💚
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
AUD-20180925-WA0029
<unknown>
*አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል (ማቴ ፮፥ ፴፫)*
በመጋቤ ሐዲስ ያሬድ እንግዳወርቅ
ለመምህራችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን

@embee
† ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን †
→በወርኃ መስከረም ብቻ በዓለ መስቀልን አራት ጊዜ ታከብራለች፡፡
የመጀመሪያው ምክንያተ ክብረ በዓል፣ በኢትዮጵያ ነግሦ የነበረው ዓፄ ዳዊት ከግብፅ ንጉሥና ሊቃነጳጳሳት የተላከለትን በቅዱስ ሉቃስ እጅ የተሳለችውን ስዕለ ማርያምን፣ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የተሳለውን ኩርዓተ ርእሱን ፣ ሌሎች ንዋያተ ቅድሳትን እና የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ግማደ መስቀል የግብፅ እና ኢትዮጵያ ድንበር ከነበረችው አስዋን ከተባለችው ቦታ ተረክቧል።ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደ ኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር ” የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል ፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል፡፡
ሁለተኛው መስቀሉን በቁፋሮ ያገኘችው ንግሥት እሌኒ ደመራ ያስደመረችበት እና የእጣኑ ጢስ መስቀሉ ወደተቀበረበት ድልብ አከል ተራራ ያመለከተበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል በዚሁ ዕለት ይከበራል፡፡
መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ደግሞ ቁፋሮ ያስጀመረችበት ዕለት ሲሆን መጋቢት ዐሥር ቀን መስቀሉን አግኝታለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን አሠርታ፣ መስቀሉን አስገብታ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረችበት ዕለት ግን መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው፡፡ የመስቀሉ መገኘት ጥንተ በዓሉ መጋቢት ዐሥር ቀን ቢሆንም አባቶቻችን በታወቀና በተረዳ ነገር ዋናው የመስቀል በዓል የሚከበርበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን እንዲሆን አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም መስከረም ሃያ አንድ ቀን በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት በግሸን ደብረ ከርቤ መስቀሉ ያረፈበት ዕለት ስለሆነ
“ በልደቱ ፍስሐ ፤
በጥምቀቱ ንስሐ ፤
በመስቀሉ አብርሃ፤ ” እያልን በማኅሌት፣ በዝማሬና በቅዳሴ ለዘለዓለም ስናከብረው እንኖራለን ፡፡
የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ተብሎ እንደተጻፈ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለመስቀል የሚከናወን ሥርዓት የለም፡፡ ከካህናት አክሊል ከመነኮሳት አስኬማ ከእናቶች ቀሚስ እስከ አባቶች እጀጠባብ ድረስ የመስቀል ምልክት እያደረግን በሰውነታችን እየተነቀስን በአንገታችን እያሰርን ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር እንገልጣለን፡፡
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን እውነተኛ ፍቅር በተለያየ መንገድ አሳይቷል፡፡ ሰማይና ምድር የእርሱ የሆነ አምላክ በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡ የተነገረው ትንቢት የተቆጠረው ሱባዔ ሲያልቅ በመስቀሉ ተፈጸመ ብሎ ሕይወትን በመስጠት ሞታችንን በመውሰድ ፍቅሩን ገለጠ መስቀል ፍቅረ እግዚአብሔርን የሚያሳስበን የስብከታችን ርእስ የኑሮአችን መርሕ ስለሆነ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዘወትር እናስበዋለን፡፡
ከዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ በደጋግ ነገሥታቶቻችን አማካይነት ቅዱሱ መስቀል ወደ ሀገራችን እንዲገባ የዘወትር ጥረት አድርገዋል፡፡ የለመኑትን የማይረሳ የፈለጉትን የማይነሣ አምላክ መስቀሉ በሀገራችን እንዲቀመጥ ፈቃዱ ሆኖአል፡፡

💚 💚💛💛💖💖ወስብሓት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን

@embtee
ጥልን_በመስቀሉ_ገደለ_New_sebket_by_Memher
<unknown>
#ጥልን #በመስቀሉ #ገደለ

🌼 #መምህር #ዘላለም #ወንድሙ


#ጥልንም #በመስቀሉ #ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል #ከእግዚአብሔር ጋር #ያስታርቅ ዘንድ ነው።

መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ #ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስ

@Embtee
@EMbtee
@Embtee
➕️➕️➕️መስቀል➕️➕️በመምህር_ሳሙኤል_አስረስ
<unknown>
መስቀል

🌼 መምህር ሳሙኤል አስረስ

" ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።"
(ወደ ገላትያ ሰዎች 6:14)

┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@ EMbtee
@EMbtee
AUD-20180927-WA0038
<unknown>
*ጌታሆይ አድነን ጠፋን*
*ማቴዎስ ፰፥፳፭*
በመጋቤ ሐዲስ ቀሲስ አበበ
ለመምህራችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን
┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
┗━━° •❈• ° ━━┛
AUD-20180928-WA0039
<unknown>
ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ
(ዮሐ ፫፥ ፲፬-፲፭)
በወንድም አቤል ተፈራ
ለወንድማችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን

👆🏻👂🏻👂🏻👈🏻
┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
680437252108186
<unknown>
++ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ++

++ኢየሱስ ክርስቶስ እና ሙሴ ++

💖 በ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 💖


┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
┗━━° •❈• ° ━━┛
ለአስተያየቶ ይላኩልን 👉 @yitaya