✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.06K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
🎬 ©ንስሀ" ሐና ዳኘው |Niseha| Hana dagnew

⭕️ሊደመጥ ሚገባ⭕️

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ለማዳመጥ ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!

https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
ዐቢይ_ጾም

ጾም ማለት ሰውን ከምግብ መከልከል ነው፡፡ (ፍትሃ ነገስት አንቀፅ.15) “ጾምሰ ተከልኦተ ብዕሊ ዕምመብልዕ በጊዜ እውቅ” ጾም ማለት በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡ መብል መጠጥ የኀጢአት መሠረት ነው በመብል ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ላይ መጣ “ይችን ዕፀ በለስ ብትበሉ ሞትን ትሞታላችሁ” ዘፍጥረት 2፥17 ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው። መብል መጠጥ ከልክ ሲያልፍ ከተዘወተረም ከእግዚአብሔር ይለያል፤ “ያዕቆብ በላ ጠገበ ወፈረ ገዘፈ ደነደነ ፈጣሪው እግዚአብሔርን ተወ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ተለየ” ዘዳግም 32፥15-17 “የእግዚአብሔር መንግሥት መብልና መጠጥን አትሰብክም” ሮሜ 14፥16፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፥8-13 “ዛሬ የሚራቡ የሚጠሙ ብፁአን ናቸው ይጠግባሉና ማቴዎስ 5፥6 ጾም የሥጋ መቅጫ ነው፤ “ነፍሴን /ሰውነቴን/ በጾም ቀጣኋት መዝሙር 68፥10 ጾም በነቢያት የተመሠረተ በክርስቶስ የጸና በሐዋርያትም የተሰበከና የተረጋገጠ ለክርስቲያኖች ዲያብሎስን ድል የምንነሣበት መንፈሳዊ የጦር ዕቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደምታስተምረን ይህን ጾም ከምግብ ለመከልከል ጋር ጸሎትን፥ ስግደትን፥ ምጽዋትንና የንስሐ ዕንባን ጨምረን እንጹመው፡፡ ጌታችንና ነቢያት፣ ሐዋርያት የተውልን መንፈሳዊ መሣሪያ ነውና

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጾም የጾመው ለአብነት፣ ለማስተማር፣ ለአርዓያ ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ጾም ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ፣ ከሰው የሥጋ ጠባይ የሚመጣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ድል የተነሱበት ነው፡፡ እኛም ይህን እያሰብን በተለያየ መንገድ የሚመጣብንን ፈተና ለማራቅ ከዚህ ታላቅ ጾም በረከት እንድናገኝ እንጾማለን፡፡ ጸልዮ ጸልዩ፣ ጾሞ ጹሙ ብሎናል፡፡ ማቴዎስ 6፥16 ስለዚህም ትእዛዙን ለማክበር እንጾማለን

የዚህ ታላቅ ጾም ስያሜዎች፦

ዐቢይ_ጾም
ባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል

ጾመ_ሁዳዴ
በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል

የካሳ_ጾም
አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ

የድል_ጾም
አርዕስተ ኃጣውእ /ማቴዎስ 4/ ድል የተነሱበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል

የመሸጋገሪያ_ጾም
ጌታችን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሸጋግረን የጾመው ጾም በመሆኑ የመሸጋገሪያ ጾም ተብሏል

ጾመ_አስተምህሮ
ጌታችን የጾመው ለትምህርት ነው፡፡ እርሱ መጾም ያለበት ሆኖ አይደለም፡፡ ስለዚህም ይህ ጾም ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ። ማቴዎስ 4፥2

የቀድሶተ_ገዳም_ጾም
ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል

የመዘጋጃ_ጾም
ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል
++ ዛሬ ነገ ነው? ++

‘‘አባዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ
አባት እየተበሳጨ ‘ምንድን ነው የምትለኝ?’ አለ፡፡
ልጅ ‘ዛሬ ነገ ነው ወይ?’
አባት እንቅልፉ ስላልቀቀው ‘ሂድና እናትህን ጠይቃት በቃ ልተኛበት’ አለና እየተበሳጨ ፊቱን ሸፈነ፡፡
ልጅ ወደ እናት ሔዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት
‘’እማዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ እናት ፈገግ አለች
‘ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?’’ አለች የልጅዋን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች
‘ትናንት አስተማሪያችን ‘ነገ ትምህርት የለም’ ብላን ነበር ፤ ዛሬ ነገ ነው?’’
እናት ‘እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው’ አለች እየሳቀች፡፡
ይህ ለሕጻኑ ጥያቄ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም፡፡ ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው፡፡ ለነገ እንማራለን ፣ ለነገ እንሠራለን ፣ ለነገ እንገነባለን፡፡ የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ፡፡ ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን፡፡ ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን፡፡ እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን፡፡ መጽሐፍ ‘’ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና’ ‘ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ! ይላል፡፡ /ያዕ 4፡15 ፤ ማቴ 6፡34/
ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሣሪያም አንዱ ‘ነገ’ በሚል ቃል ማዘናጋት ነው፡፡ ነገ እማራለሁ ፣ ነገ እሔዳለሁ ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ ፣ ነገ ንስሓ እገባለሁ ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሠራለሁ ነገ ነገ ነገ
ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉሥ በመቅሠፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር፡፡ በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ ፦ ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው፡፡ ፈርኦንም ፦ ነገ አለ፡፡
እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው፡፡ ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት ክፉ አመል አለብህ ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ ፣ አልስተካከል ያለህ ድክመት ፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? ‘አቤቱ አሁን አድን’ ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ
ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ ፣ ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ ፣ ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም፡፡ ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግሥቱም መልሳችን ነገ ነው፡፡ ‘ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው’ እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሠራ የማንፈልገውን እየሠራን እንኖራለን፡፡ ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም ‘የተወደደው ሰዓት አሁን ነው’ መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትሥጥ፡፡ ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው፡፡ ማንም ሊሠራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት፡፡
አሁኑኑ ተነሥ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመሥራት ፣ ክፉውን ነገር ለመተው ነገ አደርገዋለሁ አትበል
ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅህ ‘ነገ አደርገዋለሁ’ ብለህ ነበር ፤ ዛሬም ‘ነገ’ አትበል ምክንያቱም ሕጻኑ እንዳለው ‘ዛሬ ነገ ነው’

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ሌሎች እንዲያነቡትም ሼር ያድርጉ

╔═★══════════📄══╗
@Zemaryan
@Zemaryan
@Zemaryan
╚══📃══════════★═╝
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ወንድሞቻችሁ እና እህቶቻችሁ እንዲያነቡት ተጋሩት(share it)


ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ
ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዓይን ናቸው። ጻድቁን መንካት የቤተ ክርስቲያንን ዓይኗን መጠንቆል ነው።
ተክለ ሃይማኖት እንደ ሊቃውንት ሊቅ፣ እንደ ሐዋርያት ሰባኬ ወንጌል፣ እንደ ሰማዕታት ብዙ ግፍ የተቀበሉ፣ እንደ ጻድቃን ትሩፋት የበዛላቸው፣ እንደ ደናግል ንጽሕናን ያዘወተሩ፣ እንደ ባሕታውያን ግኁስ፣ እንደ መላእክትም ባለ ክንፍ አባት ናቸው። ለዚህ ነው ተክለ ሃይማኖትን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዓይኔ የምትላቸው።

ልደት

መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ፣ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል።
በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል።
ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት ፳፬ ቀን በ፲፪፻፮ ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን በ፲፪፻፯ ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል።

ዕድገት

የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይህንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት፣ ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ጳጳስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል።

መጠራት

አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ።
የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ።" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ።

አገልግሎት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከጳጳሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮጵያ ሁለት መልክ ነበራት።
፩ኛ.ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል።
፪ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር።
ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡንና መሳፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው ማርያኖችን (ጠንቋዮችን) አጥፍተዋል።

ገዳማዊ ሕይወት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮጵያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በሦስት ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል።
እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለአሥራ ሁለት ዓመታት፣ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለሰባት ዓመታት፣ በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለሰባት ዓመታት በአጠቃላይ ለሃያ ስድስት ዓመታት አገልግለዋል።
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለሃያ ሁለት ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም ስድስት ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለሰባት ዓመታት ጸልየዋል።

ስድስት ክንፍ

ኢትዮጵያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እስራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ፣ እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር።
የወቅቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው። ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር።
ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ፦
በቤተ መቅደስ ብስራቱን፣
በቤተ ልሔም ልደቱን፣
በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን፣
በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን፣
በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር።
የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ።
በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ አባታችንን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። @zemaryan
በዚያም፦
የብርሃን ዓይን ተቀብለው፣
ስድስት ክንፍ አብቅለው፣
የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው፣
ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው፣
ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው፣
ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው "ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል።

ተአምራት

የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው።
ሙት አንስተዋል፣
ድውያንን ፈውሰዋል፣
አጋንንትን አሳደዋል፣
እሳትን ጨብጠዋል፣
በክንፍ በረዋል፣
ደመናን ዙፋን አድርገዋል።
ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕፃናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና። @zemaryan

ዕረፍት

ጻድቅ፣ ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው፣ መከራን በብዙ ተቀብለው፣ እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው በተወለዱ በዘጠና ዘጠኝ ዓመት ከስምንት ወር ከአንድ ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ ቀን በ፲፫፻፮ ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ፣ ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። አሥር ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።
አምላከ ቅዱሳን ከጻድቁ አባታችን በረከትን ይክፈለን።
መጋቢት ፳፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ

የቅዱሳን በዓላት

፩.ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት (ጽንሰታቸው)
፪.ቅዱሳን እግዚእ ኃረያና ጸጋ ዘአብ
፫.ቅዱስ አባ መቃርስ ሊቀ ጳጳሳት
ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ አጋቢጦስ ጻድቅ
፪.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፫.ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፬.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፭.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፮.ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ
"በረከት በጻድቅ ሰው ራስ ላይ ነው። የኀጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል። የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው። የኀጥአን ስም ግን ይጠፋል።"
(ምሳሌ ፲፥፮-፯)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

╔═★══════════📄══╗
@Zemaryan
@Zemaryan
╚══📃══════════★═╝
ሰላም የደጓ እናቴ ማርያም ቻናል አባላት
አዲስ ዜና አለ 🌍🌍🌍
አዲስ የማስተማርያ bot ከፍተናል ገብታቹ ተማሩ
ሊንኩ 👉👉👉 @maryamawit_bot
እንኩዋን አደረሳችሁ

"' በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ "'

+*" ሰማዕታተ ኢትዮጵያ "*+

አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡

ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡

ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡፡

ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡

ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡"

አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡

አሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡

ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡"

በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡"

በረከቶሙ: ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡

ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ፡፡
ምስለ ሰማዕታት ዘግብጽ መከራቲክሙ ዘሐብራ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶሳዊት ሐራ፡፡
እፎ ክህልክሙ ተዐግሦ ጽኑዕ መከራ፡፡
እስከ ክሳውዲክሙ በአሲስ ተመትራ፡፡
(ኢያዕመርኩ ከመ መኑ ጸሐፎ)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ይትባረክ አምላከ አባዊነ ያብፅአነ እስከ ዘአቲ ሰአት
እስከዚህ ሰዓት ያደረሰን የአባቶቻችን አምላክ ይባረክ
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዚያ 12
✞✞✞ እንኩዋን ለጻድቅ ሰው "አባ ሳሙኤል
ዘቆየጻ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
✞✞✞

+*" አባ ሳሙኤል ዘቆየጻ "*+

=>በኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ መካከለኛው ዘመን
(በተለይ ከ13ኛው እስከ 15ኛው መቶ ክ/ዘመን ድረስ
ያለው) የብርሃን ዘመን ይባላል:: ምክንያቱም ዘመኑ
*ክርስትና ያበበበት::
*መጻሕፍት የተደረሱበት::
*ስብከተ ወንጌል የተስፋፋበት::
*ገዳማዊ ሕይወት የሠመረበት ወቅት በመሆኑ ነው::

+ለዚህ ትልቁ አስተዋጽኦ ደግሞ:-
¤አቡነ ተክለ ሃይማኖት::
¤አቡነ ኤዎስጣቴዎስ::
¤አባ ሰላማ ካልዕ::
¤አቡነ ያዕቆብ::
¤ቅዱሱ ንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብ::
¤አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ::
¤አቡነ መድኃኒነ እግዚእን የመሰሉ አበው መነሳታቸው
ነው::

+በተጨማሪም:-
¤12ቱ ንቡራነ ዕድ::
¤7ቱ ከዋክብት::
¤47ቱ ከዋክብት::
¤5ቱ ከዋክብት የሚባሉ አበው አስተዋጽኦም ልዩ ነበር::

ከእነዚህ መካከልም የ7ቱ እና የ47ቱ ከዋክብት
አስተማሪ: የአበው 3ቱ ሳሙኤሎች (ዘዋልድባ: ዘጣሬጣና
ዘቆየጻ): የሌሎችም እልፍ አእላፍ ቅዱሳን አባት የሆኑት
አባ መድኃኒነ እግዚእ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ::

+ጻድቁ ቅዱሳኑን ሰብስበው: አስተምረው: አመንኩሰው:
መርቀው ሰደው: ሃገራችንን እንዲያበሩ በማድረጋቸው
እንደ አባ ኢየሱስ ሞዐ እርሳቸውም "ወላዴ አእላፍ
ቅዱሳን" ይባላሉ:: ታላቁ ጻድቅና ሰባኬ ወንጌል አባ ዓቢየ እግዚእም (ጐንደር ውስጥ እባብና ጅብ እንዳይጐዳ
የገዘቱ አባት ናቸው) የእርሳቸው ደቀ መዝሙር ነበሩ
ይባላል::

=>ከ7ቱ ከዋክብት አንዱ የሆኑት የቆየጻው አባ ሳሙኤል
የመድኃኒነ እግዚእ ደቀ መዝሙር ናቸው:: ፋሾ ውስጥ
(ትግራይ አካባቢ) ተወልደው : እንደሚገባ አድገው :
መጻሕፍትን ተምረው ደብረ በንኮል ገብተዋል::
+በዚያም ከ6ቱ ባልንጀሮቻቸው ጋር የምናኔን ምሥጢርና
ተጋድሎን አጥንተው በመነኮሱበት ቀን ብርሃን
ወርዶላቸዋል:: በጻድቁ መምህራቸው ለአገልግሎት
ሲላኩም ለእርሳቸው ቆየጻ (ትግራይ) ደርሷቸዋል::
+በዚያም በጾም በጸሎት እየተጉ : ስብከተ ወንጌልን
እያስፋፉ : ደቀ መዛሙርትን እያፈሩ ለዘመናት ኑረዋል::
አባ ሳሙኤል በተለየ መንገድ ቅዱሳት መጻሕፍትን ይጽፉ
ነበርም ይባላል::

+በጊዜው 72ቱ ከዋክብት (70ው ሊቃናት) ከሚባሉ
አበው ጋር በመተባበር 4ቱ ወንጌል በብራና : በልዩ ጌጥ :
በ120 ሐረግ : በ4 ዓምድ ተጽፏል:: ያንንም ወስደው
በመቃብራት አካባቢ ቢያስቀምጡት 211 ሰዎች ከሞት
ተነስተዋል::

+"ማን አስነሳችሁ?" ሲባሉም "አምላከ ጻድቃን ወሰማዕት
: ወአምላከ ሳሙኤል ጻድቅ" ሲሉ መስክረዋል:: ይህን
ወንጌል ሲጽፉም ቅዱሳን መላእክት ረድተዋቸዋል::
+ጻድቁ አባ ሳሙኤል ዘቆየጻ ከብዙ ድካምና ተጋድሎ
በሁዋላ እዚያው በገዳማቸው ዐርፈዋል::
መቃብራቸውንም 5 አናምርት (5 ነብሮች) ቆፍረውላቸው
ተቀብረዋል::
(ስዕሉ የአባ ሳሙኤል ዘቆየጻ ነው)

=>አምላከ ቅዱሳን ከጻድቁ በረከት ይክፈለን::

=>+"+ በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ
ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው::
+"+ (ምሳ. 10:7)

=>+"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 36:28-31)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
#ክብረ_እመቤታችን_ድንግል_በክልዔ_ንጽሕተ_ንጹሐን_ቅድስተ_ቅዱሳን_ድንግል_ማርያም
እግዚአብሔር ዘላለማዊ ኃይሉንና አምላክነቱን ለዓለም ከገለጸበት ታላቅ ሥራ መካከል በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም የገለጸው ድንቅ ሥራው በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ይህንን ኹኔታ ድንግል ማርያም ‹‹ብርቱ የኾነ እርሱ ታላቅ ሥራን በእኔ አድርጓል፤ ስለዚህም ፍጥረት ኹሉ ያመሰግኑኛል›› /ሉቃ.፩፥፵፱/ በማለት ገለጸችው፡፡
ቅድስት ኤልሳቤጥም ‹‹የጌታዬ እናት›› አለቻት /ሉቃ.፩፥፵፫/፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ›› አላት /ሉቃ.፩፥፳፰/፡፡ ቅዱስ ዳዊት ደግሞ ‹‹ልጄ›› ይላታል /መዝ.፵፬፥፱/፡፡ ሰሎሞንም ‹‹እኅቴ›› ይላታል /መኃ.፭፥፩/፡፡ ለወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም እናት ኾና ተሰጥታዋለች /ዮሐ.፲፱፥፳፮/፡፡ ይህን ድንቅ ምሥጢር ውስንና ደካማ የኾነ አእምሮ ሊገነዘበው ከሚችለው በላይ ነው፡፡
ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በጻፈው መልእክቱ እንደገለጸው ‹‹የቅድስት ማርያም ዘለዓለማዊ ድንግልና፤ አማኑኤልን መውለዷና የማይሞተው ጌታ መሞቱ›› እነዚህ ሦስቱ ከዚህ ዓለም ጥበበኞችና ገዢዎች የተሰወሩ ምሥጢራት ናቸው፡፡ ቅዱስ አግናጥዮስ ‹‹እነዚህ ድንቅ ምሥጢራት በራሳቸው ከንግግርና ከቋንቋዎች ኹሉ በላይ ኾነው የሚነገሩ በእግዚአብሔር የዝምታ መጐናጸፊያ የተጠቀለሉ ድብቅና ጣፋጭ ምሥጢሮች ናቸው›› ይላል፡፡
የእመቤታችን ምስጋናዋ የበዛለት ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊም ‹‹አቤቱ መሰንቆ ልቡናዬን አነቃቃ፤ የልቤንም እንዚራ፡፡ ድምፁን ከፍ አድርጎ የዳዊት ልጅ የኾነችውን፣ የጌታውን እናት ድንግል ማርያምን ያመሰግናት ዘንድ፤ ለዓለም ሕይወት የሚሰጠውን የወለደች እናቱ የኾነች እርሷን ከፍ ከፍ ያደርጋት ዘንድ›› ብሏል፡፡ በሌላም አንቀጽ ደግሞ ‹‹ከሕሊናት ኹሉ በላይ ለኾነ ለዚህ ነገር አንክሮ ይገባል፡፡ ምድራዊት ሴት ፈጣሪዋን ወለደችው፤ እርሱም እናቱን ፈጠረ›› አለ፡፡ ስለእነዚህ ነገሮች ኹሉ ምን ማለትን እንችላለን? እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ያልተናገረበት ጊዜ፤ ያላናገረው ቅዱስ እንደሌለ እንመለከታለን፡፡
‹‹በእግዚአብሔር፣ በመላእክትና በሰው ፊት የከበረ ሰው መታሰቢያው ለዘለዓለም ነው፡፡ በቤቱ በቅጥሩ የማይጠፋ የዘለዓለም ስምን ይቀበላልና›› /ኢሳ.፶፭፥፫/፡፡ ይህንን ታላቅ በረከት እንደሚሰጣቸው የተናገረው የማይዋሸው ቅዱስ እግዚአብሔር ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ወልድ እናት ከድንግል ማርያም የበለጠ በሰውና በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ማንን ልንጠራ እንችላለን? እንደ እርሷስ ሊታሰብ፣ ሊከበርም የሚችል በቅድስና ሕይወት ያለፈ ማን ይኖራል?
ቅዱስ እግዚአብሔር ፍጥረቱንና ዓለሙን ለማዳን የወሰነው ጊዜ በደረሰ ጊዜ ከድንግል ማርያም በድንግልና ተወለደ፡፡ አስቀድሞ በመልአኩ አፍ እንዳናገረ ክብሩ በእርሷ ላይ ታየ /ኢሳ.፷፥፪/፡፡ ማኅፀኗን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በእርስዋ አደረ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእመቤታችን ላይ የማደሩ ምሥጢር ያነጻቸው፤ ይቀድሳቸው፤ በሥጋም በነፍስም መርቶ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ያገባቸው ዘንድ በነቢያት፣ በሐዋርያት ላይ እንዳደረው ዓይነት አይደለም፡፡ ከሦስቱ አካል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ (ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ) ከሥጋዋ ሥጋን፣ ከነፍስዋ ነፍስን ነስቶ ፍጹም ሰው፣ ፍጹም አምላክ ኾነ እንጂ፡፡ ቅዱስ ሉቃስ ይህን ዘለዓለማዊ እውነት ‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑል ኃይልም ይጸልልሻል፡፡ ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል›› በማለት ገልጾታል /ሉቃ.፩፥፵፭/፡፡
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ደራሲና ገጣሚ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም ‹‹የእስራኤል ንጉሥ በእስራኤል ልጅ አደረ፤ የዳዊት አምላክ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ለበሰ፡፡ የዕብራውያን ጌታ በዕብራውያን ልጅ ማኅፀን ተወሰነ፡፡ ለአብርሃም የዕብራይስጥ ልሳን ያስተማረው ከቀድሞም ያልሰማውን ልሳን እንዲናገር አፉን ጆሮውን የከፈተለት ከዕብራዊት ድንግል ተወለደ፤ በድንግልና ወተት ጥቂት ጥቂት እያለ አደገ፡፡ የሕፃናትን ሥርዓት እንዳያጎድል አፉን የሚፈታባት ዘመን እስኪፈጸም ጥቂት ጥቂት እያለ በዕብራይስጥ ልሳን ሲናገር ኖረ፡፡ ለሙሴ በዕብራይስጥ ልሳን በጣቶቹ የተጻፉትን ዐሠርቱ ቃላትን የሰጠ የዕብራይስጥ ፊደል ለመማር ከመምህር እግር በታች ተቀመጠ፡፡ የባቢሎን አውራጃ በምትኾን ሰናዖርም የፍጥረትን ሁሉ ቋንቋ የበተነ እርሱ የአሕዛብን ቋንቋ እንደማያውቅ ኹሉ እናቱ አፍ በፈታችበት ልሳን በዕብራይስጥ ልሳን ሲናገር ኖረ፡፡ ጆሮ ይህንን ነገር ከመስማት የተነሣ የሚለመልምበት ይህ ነገር ዕፁብ ድንቅ ነው፡፡ ለዚህ አንክሮ ይገባል›› አለ፡፡ ይህ በሰው ጥበብ በብራናና በቀለም የተጻፈ እውነት ሳይኾን ለድኅነት በተጠሩ ሰዎች ሁሉ ልቡና በአምላክ ጥበብ የተጻፈ እውነት ነው፡፡
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ይደርብን፤ የልጇ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክረስቶስ ጸጋ ይብዛልን፡፡
✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
✞✞ ወለወላዲቱ ድንግል
✞✞ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን 🙏🙏🙏
+ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑሻል +

የመላእክት አንድነት ኹሉ ያመሰግኑሻል በንፅህና ሥርዓት እነርሱን ትመስያለሽና።

የነቢያት አንድነት ያመሰግኑሻል ተስፋ ትንቢታቸው እውን ሆኖ በአንቺ ተፈፅሟልና።

የሐዋርያት አንድነት ሁሉ ያመሰግኑሻል የተወደደው ልጅሽ ወንድሞች አድርጓቸዋልና።

ድለ መልካሞች ሰማዕታት ያመሰግኑሻል የልጅሽ
መከራ አንድነት በሥጋቸው ተሸክመዋልና

ደናግልና መነኮሳት ያመሰግኑሻል ሕይወታቸውን ለንፅሕናሽ ምሳሌ ብፅዕት አድርገዋልና።

ሊቀ ጳጳሳትና ኢጲስ ቆጶሳት ያመሰግኑሻል ለማዕረገ
ክህነታቸው ልጅሽ አለቃ ሆኗልና።

አንባቢዎችና መዘምራን ያመሰግኑሻል ልጅሽን ለማመስገን እንደ ወርቅ ጸናጽሎች በቤተ መቅደስ ይጮኻሉና።

የክርስቲያን አንድነት ኹላቸው ያመሰግኑሻል ከልጅሽ
ጎን በፈሰሰው ውሃ የጥምቀት መጎናጸፊያን ለብሰዋልና።

(አርጋኖን - ሊቁ አባ ጊዮርጊስ)
++ እመቤታችን በቅዱስ ኤፍሬም ++

" ጌታ ሆይ አንተን ምን ብሎ መጥራት እንዳለበት የሚያውቅ ሰው ማን ነው? ጌታ ሆይ እናትህን ድንግል ብለን እንጥራትን? እንዲያ ብለን እንዳንጠራት የአንተ እናት መሆኑዋ ምስክር ይሆንብናል፤ ጌታ ሆይ እናት እንበላትን? እንዲህ እንዳንል ወንድ የማታውቅ ድንግል ናት፤ የእናትህ ነገር ለመረዳት የረቀቀ ከሆነ አንተን ሊረዳ የሚችል ሰው ማን ነው? ሁሉን በቀላሉ የምታከናውን የሁሉ አስገኝ የሆንክ ክብር ምስጋና ለአንተ ይሁን፡፡

እርሷ ብቻ ያንተ እናት ናት፤ ከሁሉ ጋር ደግሞ እኅትህም ናት፤ ስለዚህም እርሷ ለአንተ እናትም፣ እኅትም፣ ሙሽራም ሆናለች። እንደ ሌሎች ቅዱሳኖችህ፤ የእናትህን ደም ግባት ገንዘብህ
ያደረግህ አንተ እርሱዋን በበረከት ሁሉ አስጌጥኻት፡፡

አንተ ወደ እርሷ ከመምጣትህ በፊት ቅድስት ድንግል ማርያም በልማዳዊ መንገድ ይጠብቃት ዘንድ ለዮሴፍ ተሰጠች፤ አንተ ወደ እርሱዋ ከመጣህ በኋላ ግን ከተፈጥሯዊ ሥርዓት ውጪ አንተን በድንግልና ፀነሰችህ፤ አንተ ብቻ ቅዱስ የሆንክ ጌታ ሆይ እርሷ አንተን ቅዱስ በሆነ ልደት በድንግልና ወለደችህ፤ ጌታ ሆይ ቅድስት እናትህ ድንግል ሳለች አንተን ፀንሳ በመውለድ እናትህነትን ገንዘቧ አደረገች።

ድንግል ሆና ሳለች ከጡቶቿ ወተት ፈሰሰ፤ ድንግል ከሆነች መሬት ንጹሕ ምንጭ እንዲፈልቅ፤ እንዲሁ ድንግል ከሆነችው እናትህ ጡቶች ወተት ፈለቀ፡፡ እርሱዋ አንተን ብትሸከምህ አንተ ጽንዕ ሰጥተሃት ነው፤ በተራብክ ጊዜ አንተን ከጡቶቿ ትመግብህ ዘንድ፣ ነቢዩ ዳንኤል በታላቅ ተራራ የመሰለህ አንተን አንደ ሕፃናት ታቀፈችህ። በፈቃድህ የተጠማህ አንተን በእጆቹዋ በፍቅር ትዳብስህ ዘንድ፤ የምህረት እሳት የሆንኽ አንተ ክንዶቿን መለኮታዊው እሳት እንዳያቃጥላቸው ጠበቅኻቸው፡፡

ጌታ ሆይ እናትህ ግሩም የሆኑ ተአምራት የተፈጸሙበት መካን ናት፤
ከዚህ ቻናል leave ከማለት
የሚስተካከል ነገር አለ ብላችሁ ብትጠይቁ የተሻለ ይመስለኛል
ለዚህም ነው በዚህ ቻናል
ጥሩ ጎንም ሆነ መጥፎ
@asrategabriel
ወይም
@yita21
ላይ አድርሱን እንላለን
እናመሰግናለን። 🙏🙏🙏🙏
#ነገረ_ማርያም


💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓💓
#ርዕሱን ወደተመለከተው ወደ ዋናው ትምህርት ከመግባታች አስቀድሞ የርዕሱን ትርጉም ማወቅ ይቀድማልና ነገረ ማርያም የሚለውን ትርጉም እናያለን። ነገረ ማርያም ማለት የእመቤታችንን ነገር (ስለ እመቤታችን) የሚያወሳ ነገር ወይም ትምህርት ማለት ነው። ይህም አስቀድማ በአምላክ ሕሊና መታሰቧን፣ ትንቢት የተነገረላት፣ ምሳሌ የተመሰለላት መሆኗን ልደቷን፣ እድገቷን፣ አምላክን ፀንሳ መውለዷን ዕረፍቷን ትንሣኤዋን ወዘተ የሚተርክ የሚያስተምር ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማርያም በሚል ስም የሚጠሩ ብ ሴቶች አሉ። እነዚህም በብሉይና በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ላ ተጠቅሰው ይገኛሉ። እነርሱም፡-
1ኛ. #የሙሴ_እህት_ማርያም፡- ይህች ማርያም ሙሴ በወንዝ ዳ በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን ነገር ስትከታተል ነበር ዘፀ.2፥4-8
– እስራኤል ባሕረ ኤርትራን ሲሻገሩ ከበሮ በመያዝ በመዝሙ እግዚአብሔርን አመስግናለች። ዘፀ. 15፥20-22
2ኛ. የዕዝራ የልጅ ልጅ (የዬቴር ልጅ) ማርያም 1ኛ. ዜና. 4፥17
3ኛ. #የማርታና_የአልዓዛር_እኅት_ማርያም ዮሐ. 11፥1
– ክርስቶስ ወደ ቤታቸው እየሄደ ይጎበኛቸው ያስተምራቸው ነበር።
– ቃሉን ለመስማት ትተጋ ስለነበር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመስግኗታል። ሉቃ. 10፥39-42
-ጌታን ሽቱ ቀባችው እግሩንም በጠጉርዋ አበሰችው። ዮሐ. 11፥2፣ ዮሐ.12፥1-8
4ኛ. #መግደላዊት_ማርያም
– ክርስቶስ ሰባት አጋንንትን አወጣላት። ሉቃ. 8፥2
– ከትንሣኤው በኋላ በአትክልት ቦታ ለእርሷ ለብቻዋ ታያት ተገለጠላት። ዮሐ. 20፥1-8
5ኛ. #የታናሹ_የያዕቆብና_የዮሳ_እናት_ማርያም ማር. 15፥40
6ኛ. #የቀለዮጳ_ሚስት_ማርያም- ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ከመስቀሉ አጠገብ ቆማ ነበር። ዮሐ. 19፥25
7ኛ. #የማርቆስ_እናት_ማርያም ሐዋ. 12፥12
8ኛ. #የኢየሱስ_ክርስቶስ_እናት_ቅድስት_ድንግል_ማርያም
ከላይ የተዘረዘሩት ማርያም በሚል ስም የተጠሩ ሴቶች እንዳሉ ለማመልከት እንጂ ስለ ሁሉም ለመተረክ ተፈልጎ አይደለም ከዚህ በኋላ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለወለደ ስለቅድስት ድንግል ማርያም እንፅፋለን።
ሀ) #የእመቤታችን_መወለድ (ልደታ ለማርያም)
የወደቀው ሰው ከውድቀቱ ይነሳ፣ ከርኩሰቱ ይቀደስ ዘን አምላክ ከእርሷ እንዲወለድ የወላዲተ አምላክ የአማናዊው ፀሐይ የክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ግድ ነበር። ስለዚህም ነው “እግዝእትነ ማርያም ነበረ እምቅድመ ዓለም በሕሊና አምላክ” (እመቤታችን ማርያም ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር) የተባለው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ እንደምናገኘው ብዙ ሰዎች ልጅ በማጣት አዝነው እግዚአብሔርን ፀንተው በመለመን ልጅ ያው ታላላቅ ልጆችን እንዳገኙ እናነባለን። እንዲያውም አንዳንዶ ካረጁና የመውለጃ ጊዜአቸው ከተላለፋቸው በኋላ ነው ልጅ የሚያገኙት። የሳራና የአብርሃም፣ የኤልሳቤጥና የካህኑ ዘካርያስ የሐና እና የሕልቃና ወዘተ. ታሪክ ለዚህ ማስረጃ ይሆነናል። ዘፍ. 21፥1-8፣ ሉቃ. 1፥8-23፣ ሉቃ. 1፥57-67፣ 1ኛ ሳሙ. 1፥1-21። የእመቤታችን እናት ሐና እና አባቷ ኢያቄም ከላ እንዳየናቸው ሁሉ መካን ሆነው ይኖሩ ነበር። በኋላ ግን ለሳራ አብርሃም ይስሐቅን፣ ለኤልሳቤጥና ዘካርያስ መጥምቀ መለኮ ዮሐንስን፣ ለሐና እና ለሕልቃና ሳሙኤልን የሰጣቸው እግዚአብሔር ለሐና እና ለኢያቄምም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሰጣቸው።
እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተፀነሰች። ገና በማሕፀን ሳለች አንድ ዓይነ ስውር ዘመዷ ኤልሳቤጥ ፀነሰች ቢሏት ዳስ ካላረጋገጥኩ አላምንም ብላ የሐናን ሆድ ነክታ መፅነሷ ስታረጋግጥ በአድናቆት እጇን ዓይኗ ላይ ብታደርገው በሐ ማሕፀን ያለችው የአምላክ እናት ናትና የዓይነ ስውሯ ዓይ በራላት። የሞተ ሰው ይዘው ሲሄዱ የሐና ጥላ በሙቱ ላይ ሲያር የሞተው ሰው ተነስቷል። ከዚህ በኋላ ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተራራ ተወለደች። የእመቤታችን የዘር ሐረግ በአባቷ ከነገ ይሁዳ በእናቷ ደግሞ ከነገደ አሮን ነው።
ለ) #እመቤታችን_ወደ_ቤተ_መቅደስ_መግባት (በአ ለማርያም)
በአታ ለማርያም ማለት የማርያም ወደ ቤተ መቅደስ መግባ ማለት ነው። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእናት ከአባቷ ጋር አብራ የኖረችው ለሦስት ዓመታት ብቻ ነው የብፅዓት ልጅ ናትና ሦስት ዓመት ሲሆናት እናትና አቧ በስእለታቸው መሠረት ለእግዚአብሔር ቤት ለመስጠት ወ ቤተመቅደስ ወሰዷት። በጊዜው የነበረው ሊቀ ካህን ዘካርያስ ነበርና ወደ ዘካርያስ አቀረቧት። እርሱም ምን እንደሚያደርግ ግ ገብቶት ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ፋኑኤል ፅዋ ሰማያዊ ኅብስት ሰማያዊ ይዞ ወረደ። ዘካርያስ፣ ካህና ኢያቄምና ሐና ወደ መልአኩ ቢቀርቡ እርሱ ግን ራቃቸ የመጣው ለእነርሱ አይደለምና። እመቤታችንን ብቻዋን ሲተዋት ግን መልአኩ ወርዶ በክንፎቹ ጋርዶ መግቧት አርጓል። ዘካርያስ የሆነውን ሁሉ አይቶ ፈቃደ እግዚአበሔር መሆኑን ተረድቶ ከቤተ መቅደስ አስገብቷታል።
እመቤታችን በቤተመቅደስ የኖረችው ለአሥራ ሁለት ዓመ ሲሆን ከዚህ በኋላ አይሁድ ቤተመቅደሳችንን ታረክሳለች ትውጣ ብለው ቢያምፁ ዘካርያስ አይሁድ እንዲህ አሉ ም ላድርግ አላት። እመቤታችንም እኔ ምን አውቃለሁ አለችው። ወ እግዚአብሔር ቢያመለክት ከነገደ ይሁዳ ሚስቶቻቸ የሞቱባቸውን ወንዶች በትር ሰብስበህ ከቤተመቅደስ አስገብተህ ጸልይበት እኔም ምልክት እሰጥሀለሁ አለው ዘካርያስም እንደተባለው በትር ላይ “ዮሴፍ ሆይ ማርያምን ጠብቃት” የሚል ምልክት ሰጠው ዕጣ ቢጣል ለዮሴፍ ወ ርግብም በዮሴፍ ራስ ላይ አረፈች። በእነዚህ ሁሉ ምልክቶች ተረድቶ ካህኑ ዘካርያስ እመቤታችንን ለዮሴፍ ሰጣት። ይህ ሁ የሆነው በጥበበ እግዚአብሔር ነው። በብሉይ ኪዳን ህግ አንዲ ሴት ያለ ባል የፀነሰች እንደሆነ በድንጋይ ተወግራ በእሳት ተቃጥላ ትገደል ነበርና እመቤታችን ይህ ሞት እንዳያገኛት በእጮኛ ስም ለዮሴፍ ተሰጠች። እመቤታችን በሄሮድ ምክንያት የሚደርስባት ስደትና መከራ አለና ረዳቷና ጠባቂ እንዲሆን ለዮሴፍ በእጮኝነት ስም ተሰጠች። ኃይል አርያማዊት አለመሆኗ ከአዳም ዘር የተገኘች ሰው መሆኗ ይገለጥ ይታወቅ ዘንድ ለዮሴፍ በእጮኝነት ስም ተሰጠች።
ሐ) #አምላክን_መውለዷ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለማሕደረ ሥሉስ ቅዱስ አስቀድማ ተመርጣለችና እግዚአብሔር አብ ለአፅንኦ (ለማፅናት እግዚአብሔር ወልድ ለተሰብኦ (ሰው ለመሆን) እግዚአብሔ መንፈስ ቅዱስ ለአንፅሖ (ሊያነፃት) አድረውባታል። በተለ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆነ ረቂቁ መለኮት ግዙፉን ሥጋ ተዋሐደ አምላክ ሰ ሰውም አምላካ ሆነ። እመቤታችን ደግሞ ይህ ታላቅ ምስጢ የተከናወነባት ሙዳየ ምሥጢር ሆነች። ይህ ምሥጢር በእመቤታችን ማሕፀን ሲከወን በፍፁም ድንግልና ነው። ይህ ማለት እመቤታችን ከመፅሷ በፊት፣ በፀነሰችም ጊዜ፣ ከፀነሰችም በኋላ እንዲሁም ከመውለዷ በፊት በወለደችም ጊዜ ከወለደችም በኋላ “ወትረ ድንግል” ሁሌም ፍፁም ድንግል ናት። ሕዝ.44፥1-4፣ ኢሳ.7፥14።