✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.06K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
ሰላም ለእናንተ በአይነቱ ለየት ያለ የእናንተን የቮይስ ቅጂ ዝማሬ #ቻሌንጅ የምናቀርብበት ቻናል ይቀላቀሉንን ይማሩበታል በዝማሬ አምላክን ያመሰግኑበታል 👇👇👇👇👇👇👇👇
@tewahidoortodox
@tewahidoortodox

Inbox👇
@kidanemiherat_bot
🎚🎚🎚🎚

"🎚🎚 እግዚአብሔር ታማኝ ነው"

እግዚአብሔር ታማኝ ነው። የእኛ አለመታመን የእግዚአብሔርን ታማኝነት አያጎድለውም።የእኛ በደለኛነት የእግዚአብሔርን አባትነት አይቀንሰውም።እግዚአብሔር ሁልጊዜም እግዚአብሔር ነው።ከገዘፈው ነውራችን ይልቅ ጥቃቅኗን ጽድቃችንን እየቆጠረ ለተሻለ ክብርና ለላቀ ጸጋ የሚሻን ርኅሩኅ አባት ነው።ስንረቀው ይቀርበናል፣ስንሸሽው ይከተለናል፣ስንጠፋም ይፈልገናል።ዲያብሎስ ሰብሮ ሲጥለን እግዚአብሔር ጠግኖ ያቆመናል።ዓለም ንቃ ስታዋርደን፣እግዚአብሔር ግን ወዶ ያከብረናል ።በበድልና በኃጢአታችን ምክንያት ሕይወታችን ጣዕም አልባ ልባችን እረፍት አልባ ሲሆን እግዚአብሔር ግን በፍጹም ይቅርታና ምኅረት ዳግመኛ ሌላ እድል እየሰጠ አፋችንን በሳቅ ከንፈራችንን በእልልታ ይሞላል።የውርደት ማቃችንን ቀዶ ደስታን ያስታጥቀናል።

የሰው ልጅ ባልተጠራበት ቦታ ትርፍ በተጠራበት ቦታ ግን ዋና ነው።የተጠራ ነው ለክብር ነው ፣የልጁ መልክ በእኛ እስኪሳል፤ክብርና ባለጠግነት የሕይወታችን አክሊል እስኪሆን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት ቀርበን የመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች እስክንሆን እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቶናል።ዋናችን ክርስቶስ ክብራችንም መንግስቱ ነው።በጽድቃችን ሳይሆን በጸጋው የሚያወርሰንን ርስት በልግስና ለመስጠት እግዚአብሔር የታመነ ነው።

አልገባ ብሎን ነው እንጂ ዓለም የእኛ እኛም የዓለም አይደለንም።በዓለም እየኖርን ከዓለም የተለየን የመንግስተ ሰማያት ዜጎች ነን።ከሰማያዊ ጥሪ ተካፋይ የሆናችሁ ወገኖች ሆይ የእምነታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህን የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ተመልክተን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ።ሀገራችን በሰማይ ነው።ይህ ድንኳን የሆነው የምድራዊ ኑሯችን ፍጹም ከንቱና ጊዚያዊ ነው።ለጊዚያዊ የድንኳን ኑሮ እንዴት ሰው በወገኑ ደም ላይ ይቆማል ፣እንኳንስ ለጸብ ለፍቅር በማትበቃ እድሜስ እንዴት ሰው የወንድሙን መቃብር ይምሳል።የይቅርታን ድምጽ ከመስቀል ላይ የሰማ አማኝ ፣ የሰላምን ወንጌል ከፍቅር መምህር ያደመጠ ክርስቲያን እንዴት ለኩርማን መሬትና ለቁራሽ እንጀራ ፍቅርን በጸብ ይለውጣል።እንኳን ደረቅ መሬት እኛስ አፈር አይደለንም ወይ?እግዚአብሔር ያልባረከው በደም የተገኘ ርስት እርሱ አኬልዳማ የደም መሬት ነው።ቢዘሩበት እሾህ ቢያርሱበት አሜኬላ የሚያበቅል የእርግማን ምድር ነው።

እርስትም ብቻ አደለም ባለን ጥቂት ነገር እንኳ በፍቅር ተካፍለን እንኑር። በጥቂቱ ያልታመነ በብዙ አይሾምምና። ለትንሽ ነገር ስግብግቦች ራስ ወዳዶች አንሁን እግዚአብሔር ከሌለበት ጎተራ እግዚአብሔር ያለበት ጥቂት ነገር ይበልጣል። ስስት ሲኖር ፍቅር ይጠፋል፣ ፍቅር ሲጠፋ ጭካኔ እና ጥላቻ ይሰፍንብናል። በፍቅር የማካፈል ልምድ የምንጀምረው ከጥቂቷ ነገር ነውና ለኛ ይጠቅመናል ብለን የምናስባትን ትንሿ መልካም ነገር ለሌላውም እንመኛት።

በክርስቶስ ወንድሜ የሆንክ ወገኔ እባክህ ወደ ልብህ ተመለስ ደም ዘርተህ ደም አትጨድ ፤የወንድምህን ነፍስ አጥፍተህ ተናጥቀህ የምትይዘው ርስት ደዌና ደረመን በሕይወትህ ያመጣል እንጂ በረከትና ጥጋብ አይሆንልህም።በፍቅር ከሆነ ግን በኩርማን መሬት ላይ ጎተራህን ሊሞላ እግዚአብሔር የታመነ ነው።

እግዚአብሔር የልጁ የክርስቶስ ልብ እንዲኖረን በልዩ መለኮታዊ ክብር ጦርቶናልና የጠላት ዲያብሎስን ሐሳብ ጠንቅቀን አውቀን ጸብን በይቅርታ ጥላቻንም በፍቅር እንተካ።
​​የ"7" ቁጥር ምስጢራት"
= = =
➭ሰባት ቁጥር ጥልቅ ምሳሌና ትርጓሜ አለው።በዕብራውያን ዘንድ ሰባት ቁጥር ፍጹም ቁጥር ነው።

➭እግዚአብሔር ከሰኞ እስከ ዕሁድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል።(መ.ምሳሌ 24፥16)

➭እስራኤላውያን ከግብፅ ባርነት ነጻ ወጥተው በሲና በረሃ ሲጓዙ ይመሩ የነበረው በሰባት ደመና ነበር።(ዘዳ 13፥21)

➭እስራኤላውያን ኢያሪኮን ለሰባት ተከታታይ ቀናቶች እንዲዞሯት፣በሰባተኛው ቀን ደግሞ ሰባት ጊዜ እንዲዞሯት ታዘው ነበር። (ኢያሱ 6፥15)

➭ጴጥሮስ ወንድሙን ይቅር እንዲለው የታዘዘው እስከ ሰባት ጊዜ ሰባ እንጂ ሰባት ጊዜ ብቻ አልነበረም።
(ማቴዎስ 18፥21, 22)

➭ሌላው የሰባት ቁጥር ምሳሌዎች በጥቂቱ እንደሚከተለው ይቀርባሉ።

ሰባቱ አባቶች
= = =
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት

ሰባቱ ዲያቆናት
= = =
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ

ሰባት የጌታ ቃላት(እኔ ነኝ)
= = =
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ

ሰባቱ ሰማያት
= = =
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር

ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
= = =
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል

ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
= = =
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን

ሰባቱ ተዐምራት
= = =
➭ጌታ የሰው ልጆችን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት፦
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ

ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
= = =
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
= = =
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል

ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
= = =
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት

ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች (ምሳ 16፥6-19)
= = =
1. ትዕቢተኛ ዓይን
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ

ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
= = =
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)


ሰባቱ የዳዊት ሐብታት
= = =
1. ሐብተ ፈውስ
2. ሐብተ ትንቢት
3. ሐብተ በገና
4. ሐብተ መንግስት
5. ሐብተ መዊዕ
6. ሐብተ ኃይል
7. ሐብተ ክህነት

7 ቀናት፣7 ፊደላት፣7 ሰው የተፈጠረበት ባህርያት፣......
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🎬 ©አለምን የያዙት መዳፎቹ" ዘማሪ አብርሐም ያደታ | zemary abrham yadeta

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ዝማሬውን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
ውድ የተዋህዶ ልጆች እስቲ ዛሬ አንድ ነገር ላስቸግራቹ በፎቶው እንዳያቹች እናት ቤተክርስትያናችን በዩቱብ ተከታይ ያላትና መስቀል ከሚያስበጥሰው ebs ያለውን ልዩነት እዩት ያሳዝናል እውነት ebs ሰብስክራይብ አድርገን EOTC TV ካላደረግን በጣም ያሳዝናል

EOTC 21.8
EBS 1.05 ሚሊዮንንንን

አሁን ሁላችንም EOTC TV & ማህበረ.ቅዱሳን SEBSCRIBE እናድርግ

ለሌሎች ያጋሩ
@embtee
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🎬 ©ኑ ተመልከቱልኝ" ዘማሪት ሊዛ በየነ| zemarit Liza beyene

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ዝማሬውን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/KNnawxfZjc4
https://youtu.be/KNnawxfZjc4
🎬 ©ንስሀ" ሐና ዳኘው |Niseha| Hana dagnew

⭕️ሊደመጥ ሚገባ⭕️

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ለማዳመጥ ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!

https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
🎬 ©ንስሀ" ሐና ዳኘው |Niseha| Hana dagnew

⭕️ሊደመጥ ሚገባ⭕️

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ለማዳመጥ ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!

https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
ዐቢይ_ጾም

ጾም ማለት ሰውን ከምግብ መከልከል ነው፡፡ (ፍትሃ ነገስት አንቀፅ.15) “ጾምሰ ተከልኦተ ብዕሊ ዕምመብልዕ በጊዜ እውቅ” ጾም ማለት በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡ መብል መጠጥ የኀጢአት መሠረት ነው በመብል ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ላይ መጣ “ይችን ዕፀ በለስ ብትበሉ ሞትን ትሞታላችሁ” ዘፍጥረት 2፥17 ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው። መብል መጠጥ ከልክ ሲያልፍ ከተዘወተረም ከእግዚአብሔር ይለያል፤ “ያዕቆብ በላ ጠገበ ወፈረ ገዘፈ ደነደነ ፈጣሪው እግዚአብሔርን ተወ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ተለየ” ዘዳግም 32፥15-17 “የእግዚአብሔር መንግሥት መብልና መጠጥን አትሰብክም” ሮሜ 14፥16፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፥8-13 “ዛሬ የሚራቡ የሚጠሙ ብፁአን ናቸው ይጠግባሉና ማቴዎስ 5፥6 ጾም የሥጋ መቅጫ ነው፤ “ነፍሴን /ሰውነቴን/ በጾም ቀጣኋት መዝሙር 68፥10 ጾም በነቢያት የተመሠረተ በክርስቶስ የጸና በሐዋርያትም የተሰበከና የተረጋገጠ ለክርስቲያኖች ዲያብሎስን ድል የምንነሣበት መንፈሳዊ የጦር ዕቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደምታስተምረን ይህን ጾም ከምግብ ለመከልከል ጋር ጸሎትን፥ ስግደትን፥ ምጽዋትንና የንስሐ ዕንባን ጨምረን እንጹመው፡፡ ጌታችንና ነቢያት፣ ሐዋርያት የተውልን መንፈሳዊ መሣሪያ ነውና

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጾም የጾመው ለአብነት፣ ለማስተማር፣ ለአርዓያ ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ጾም ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ፣ ከሰው የሥጋ ጠባይ የሚመጣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ድል የተነሱበት ነው፡፡ እኛም ይህን እያሰብን በተለያየ መንገድ የሚመጣብንን ፈተና ለማራቅ ከዚህ ታላቅ ጾም በረከት እንድናገኝ እንጾማለን፡፡ ጸልዮ ጸልዩ፣ ጾሞ ጹሙ ብሎናል፡፡ ማቴዎስ 6፥16 ስለዚህም ትእዛዙን ለማክበር እንጾማለን

የዚህ ታላቅ ጾም ስያሜዎች፦

ዐቢይ_ጾም
ባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል

ጾመ_ሁዳዴ
በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል

የካሳ_ጾም
አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ

የድል_ጾም
አርዕስተ ኃጣውእ /ማቴዎስ 4/ ድል የተነሱበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል

የመሸጋገሪያ_ጾም
ጌታችን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሸጋግረን የጾመው ጾም በመሆኑ የመሸጋገሪያ ጾም ተብሏል

ጾመ_አስተምህሮ
ጌታችን የጾመው ለትምህርት ነው፡፡ እርሱ መጾም ያለበት ሆኖ አይደለም፡፡ ስለዚህም ይህ ጾም ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ። ማቴዎስ 4፥2

የቀድሶተ_ገዳም_ጾም
ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል

የመዘጋጃ_ጾም
ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል