የካቲት_ 2_ፆመ_ነነዌ_ይጀምራል
" ምነው_ተኝተሃል ? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።
# የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባቻ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው።
++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።
++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።
++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )
የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ ፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
@embtee
@embtee
@embtee
" ምነው_ተኝተሃል ? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።
# የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባቻ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው።
++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።
++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።
++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )
የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ ፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
@embtee
@embtee
@embtee
እባካችሁ ሠዎች አንድ ነገር ልንገራችሁ እግዚአብሔር መሀሪ እና ቸር ነው
ስለ ምን እምነታችን ጎደለ?
ስለ ምን ፍርሀት በውስጣችን ነገሰ?
ስለ ምን ወሬ ማውራት ከመፀለይ በለጠብን?
ስለ ምን ከመንበርከክ በየፋርማሲው መሰለፍ ቀለለን?
ስለ ምን ወደ እግዚአብሔር ከመጮህ ይልቅ በየሶሻል ሚድያው ሽብር መንዛትን መረጥን ?
እግዚአብሔር ሁላችንንም በማያልቀው ምህረቱ ይቅር ይበለን
እግዚአብሔር ወደእርሱ እንድንቀርብ እና እንድንማልድ ይርዳን !
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች !
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !
እግዚአብሔር በክንፎቹ ጥላ ኢትዮጵያን ይጋርድ
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
ስለ ምን እምነታችን ጎደለ?
ስለ ምን ፍርሀት በውስጣችን ነገሰ?
ስለ ምን ወሬ ማውራት ከመፀለይ በለጠብን?
ስለ ምን ከመንበርከክ በየፋርማሲው መሰለፍ ቀለለን?
ስለ ምን ወደ እግዚአብሔር ከመጮህ ይልቅ በየሶሻል ሚድያው ሽብር መንዛትን መረጥን ?
እግዚአብሔር ሁላችንንም በማያልቀው ምህረቱ ይቅር ይበለን
እግዚአብሔር ወደእርሱ እንድንቀርብ እና እንድንማልድ ይርዳን !
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች !
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !
እግዚአብሔር በክንፎቹ ጥላ ኢትዮጵያን ይጋርድ
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በ24 አካባቢ ሁለቱ ወንድሞቻችን ሰማዕታነት የተቀበሉበት ቦታ ለቤተክርስቲያን ተሰጠ።
ዛሬ አመሻሽ ከቤተክህነት አካባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለሚሰራው ህንፃ ቤተክርስትያን የመሰረት ደንጋይ ያስቅምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
💚💛❤️ @ZEMARYAN 💚💛❤️
ዛሬ አመሻሽ ከቤተክህነት አካባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለሚሰራው ህንፃ ቤተክርስትያን የመሰረት ደንጋይ ያስቅምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
💚💛❤️ @ZEMARYAN 💚💛❤️
“ሀገራዊ የጸሎት ጥሪ እንጂ ጾም አልተባለም”
ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖተ ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ
መጋቢት 28/2012 ዓ/ም
የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱን ተከትሎ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አአባቶች በአንድ ላይ ሆነው ብሔራዊ የጸሎት አዋጅ ትናንተ በ27/07/2012 ዓ.ም ማወጃቸው የሚታወስ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የታወጀው የጸሎት አዋጅ ሆኖ እያለ በተለያዩ የማኀበራዊ ድረ ገጾች ለምዕመናን የተሳሳተን መረጃ የሰጡ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ተደለ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች ያወጁት ለሁሉም ሃይማኖቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ብሔራዊ የጸሎትና የንሥሓ አዋጅ እንጅ የጾም አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጾም መሠረት ከትንሣኤ እስከ በዓለ ሃምሳ የጾም ሥርዓት እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማቱ ጉባኤ በማንኛምው ቤተ እምነት ሕግና ሥርዓት ጣልቃ የማይገባ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ እንደማይችል ጨምረው ገልጠዋል ፡፡
አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነ የሌሎች አብያተ እምነት የጋራ ጸሎትና በኮሮና ወረርሽኝ እና መሰል ጉዳዮች የትምህርትና የጸሎት መርሐ ግብር በአራት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከዛሬ ማለትም ከ28/07/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00-4፡00 ለተመልካች እንደሚደርስ ገልጠው ሁሉም እንዲከታተል ጠቁመዋል ፡፡
በመጨረሻም ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ በዘመናችን የተከሰተው ክፉ ወረርሽኝ በሽታ እንዲወገድ ሁላችንም በበረታ ክንድ ልንጸል ይገባልም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመርሐ ግብር ተራ በአራቱ ጣቢያዎች
ሰኞ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ማክሰኞ፡በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ረቡዕ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ሐሙስ፡ በ WALTA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
አርብ ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ቅዳሜ፡ በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
እሑድ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
©EOTC TV
ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖተ ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ
መጋቢት 28/2012 ዓ/ም
የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱን ተከትሎ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አአባቶች በአንድ ላይ ሆነው ብሔራዊ የጸሎት አዋጅ ትናንተ በ27/07/2012 ዓ.ም ማወጃቸው የሚታወስ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የታወጀው የጸሎት አዋጅ ሆኖ እያለ በተለያዩ የማኀበራዊ ድረ ገጾች ለምዕመናን የተሳሳተን መረጃ የሰጡ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ተደለ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች ያወጁት ለሁሉም ሃይማኖቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ብሔራዊ የጸሎትና የንሥሓ አዋጅ እንጅ የጾም አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጾም መሠረት ከትንሣኤ እስከ በዓለ ሃምሳ የጾም ሥርዓት እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማቱ ጉባኤ በማንኛምው ቤተ እምነት ሕግና ሥርዓት ጣልቃ የማይገባ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ እንደማይችል ጨምረው ገልጠዋል ፡፡
አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነ የሌሎች አብያተ እምነት የጋራ ጸሎትና በኮሮና ወረርሽኝ እና መሰል ጉዳዮች የትምህርትና የጸሎት መርሐ ግብር በአራት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከዛሬ ማለትም ከ28/07/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00-4፡00 ለተመልካች እንደሚደርስ ገልጠው ሁሉም እንዲከታተል ጠቁመዋል ፡፡
በመጨረሻም ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ በዘመናችን የተከሰተው ክፉ ወረርሽኝ በሽታ እንዲወገድ ሁላችንም በበረታ ክንድ ልንጸል ይገባልም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመርሐ ግብር ተራ በአራቱ ጣቢያዎች
ሰኞ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ማክሰኞ፡በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ረቡዕ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ሐሙስ፡ በ WALTA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
አርብ ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ቅዳሜ፡ በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
እሑድ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
©EOTC TV
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሳችሁ።
ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም
«መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው»
/መዝ. ፹፮፥፩/
ስለ እመቤታችን የትውልድ ሐረግ ከመወለዷ በፊት ነብያት በመንፈስ ቅዱስ በመቃኘት ትንቢት ይናገሩ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ በስፋት ያስተምረናል፡፡ ለምሳሌ ያህልም የዝማሬና የትንቢት ጸጋ በእግዚአብሔር የተሰጠው እንደ ልቤ የተባለ ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድሞ ስለ ሥርወልደቷ፣ አምላክን እንደምትወልድ፣ ስለ አማላጅነቷ በመዝሙር ተናግሯል ለምሳሌ በመዝ ፹፮፥፩ ላይ ‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን›› መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ በማለት ከቤተክህነት ከቅዱሳን እንደምትወለድ በምሳሌ ገልፆታል፡፡
ልጁም ጠቢቡ ሰሎሞን መኃ.መኃ.4.9 ‹‹እቴ መርዓት ሙሽርዬ ከሊባኖስ ነይ" እያለ የተወለደችበትን ሀገር እንደጠቀሰ መመልከት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ‹‹ትውፅእ በትር እምሥርው እሰይ ወየዐረግ ጽጌ እምኔሃ›› ትርጉሙም ከእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከርሷ ይወጣል በማለት ተናግሯል ት.ኢሳ ፲፩፩
በሐዲስ ኪዳንም እንደምንመለከተው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ መጀመሪያ የዘር ሐረጉን በዳዊት ጀምሮ እስከ ማታን ይቆጥራል በአይሁድ ልምድ ሴቶች በዘር ቆጠራ ስለማይቆጠሩ ዘፍራን በያዕቆብ ወገን አድርጎ ቆጠረ በዚህም ከዳዊት ወገን መሆኗን አሳውቋል፡፡
የእመቤታችን ወላጆች በምዕራብያውያኑና በምስራቅያውያኑ ዘንድ ታዋቂ በሆነው በመጽሐፈ ያዕቆብ (መጽሐፈ ልደታ ለማርያም) የእናቷ ስም ሐና የአባቷ ስም ኢያቄም እንደሚባል ጽፏል፡፡ ሐና በዕብራይስጥ "ውብ ተወዳጅ" ማለት ነው፡፡ ኢያቄም በዕብራይስጥ እግዚአብሔር የሠራው ያከናወነው ማለት ነው፡፡ እንዳንድ መናፍቃን ለእመቤታችን ካላቸው ጥላቻ የተነሳ አንድ ስለመውለዷ የጻፈ የለም ከአፄ ዘርዓያዕቆብ ውጪ ይላሉ፡፡ ግን ከላይ የተመለከትነው መጽሐፍ በጣም ጥንታዊ በዘመን የማይደራረስ መሆንን የታሪክ ድርሰቶች ይናገራሉ፡፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ የነበረው በ1399-1468 ባሉት ዓመታት ሲሆን ሐዋርያው ታናሽ ያዕቆብ የጻፈውን መጽሐፍ በ150-215 ዓ.ም ሊቁ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ እና ኦርገን እንደተጠቀሙበት እንመለከታለን ቀደምት አባቶቻችን ግን የሐና ቅድመ አባቶቿ ቴክታና ጴጥሪቃ ሲባሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ደግና ቅዱሳን እንደነበሩ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጠጎች ወርቅ ብር የተትረፈረፈላቸው ነበሩ፡፡ ጴጥሪቃ ሀብቱን ሁሉ ከተመለከተ በኋላ ለሚስቱ ይህን ሁሉ ሀብት ምን እናደርገዋለን እንኳን ለእኛ ለልጅ ልጆቻችን ይተርፍ ነበር ግን እኔም አንቺም መካኖች ነን ባላት ጊዜ ቴክታ እግዚአብሔር ከኔ ልጅ ባይሰጥህ ከሌላ ይሰጥህ ይሆነናልና ሌለ አግብተህ ውለድ፡፡ አለችው እሱም ይህን እንኳን ላደርገው እንደማላስበው እግዚአብሔር ያውቃል አላት፡፡ ማታ በህልሟ ቴክታ ነጭ እንቦሳ ከማኅጸኗ ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ሰባተኛዋ ደረሰ ሰባተኛዋ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይታ አድንቃ ለባሏ ነገረችው እሱም በልቡ እያደነቀ ወደ ህልም ፈቺ ጋር ሄደ፡፡ ህልም ፈቺውም ነጫጮቹ እንቦሶች ሰባት ደጋግ ልጆች ይወልዳሉ ሰባተኛዋ ግን በመላዕክት ሁሉ የከበረች ትሆናለች የፀሐይ ነገር ግን አልተገለፀልኝም በማለት ተረጎመላት፡፡ ጴጥሪቃ ሄዶ የህልሙን ፍቺ ነገራት እርሷም የእስራኤል አምላክ የሚያደርገውን እርሱ ያውቃል በማለት ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ በዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች ስሟንም ሔመን አሏት ሔመን ዴርዴን ወለደች ዴርዴም ቶናን ወለደ ቶናም ሲካርን ወለደች ሲካርም ሴትናን ወለደች ሴትናም ሔርሜላን ወለደች ሔርሜላም የተከበረችና የተመረጠች ዓለሙን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ አያት የምትሆን ሐናን ወለደች፡፡ ሐና በመልካም አስተዳደግ አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከነገደ ይሁዳ ወገን ለሚሆን የአላዛር የልጅ ልጅ ለሚሆን የቅስራ ልጅ ከሚሆን ከኢያቄም ዳሯት፡፡ ሐናና ኢያቄም በእግዚዓብሔር የሚወደዱ ደጋጎች ነበሩ ፡፡ ግን ልጅ አልነበራቸውም! ወደ ቤተ መንግስት በመሔድ እግዚዓብሔርን ደጅ ይጠኑት ነበር አንድ ቀን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከቱ በዚህን ጊዜ ሐና "አቤቱ ጌታዬ ግዑዛን እንስሳ ልጅ የሰጠህ ለኔ ለምን ነሳኸኝ" በማለት ሱባኤ ያዙ ኢያቄም ወደ ምድረ በዳ ሄደ ሐናም በቤቱ አትክልት ስፍራ አካባቢ ሱባኤ ያዘች በሱባኤያቸውም ፍፃሜ ራዕይ ተመለከቱ፡፡
ሐናም ለኢያቄም በህልሜ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ አደረች ብላ ነገረችው ምስጢሩም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን ነጭነቷ ንፅህናዋ፣ ቅድስናዋን የሚገልጽ ነው፡፡ ኢያቄምም የተመለከተውን ራዕይ ነገራት በህልሙ ሰባቱ ሰማያት እንደመጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወረደ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ብሎ ነገራት፡፡ ምስጢሩም ወፍ የተባለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ነጭነቱ ንጹሐ ባሕሪ መሆኑን ሲያመለክት ነው፡፡ ይህን ራዕይ ሐምሌ ፴ ቀን ተመልክተው ልጅ ብንወልድ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ትሁን ብለው ተሳሉ እመቤታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ በብስራተ ገብርኤል ነሐሴ ሰባት እሑድ ቀን ተፀንሳለች፡፡እመቤታችን በማኅፀንም ሆና ብዙ ተአምራትን አድርጋለች፡፡ ሁለቱን ለአብነት ያህል እናያለን፡፡
ሐና በርሴባ የምትባል አንድ ዓይና አክስት ነበረቻት ልትጠይቃት መጥታ ሳለ እግዚአብሔር በቸርነት ጎበኘሽ ብላ ማኅፀኗን በዳሰሰችበት እጇ የጠፋ ዓይኗን ብታሸው በርቶላታል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ ሆዷን እየዳሰሱ ድነዋል፡፡
ሐና የምትወደው ሳምናስ የሚባል የአጎቷ ልጅ ሞቶ በቤተሰብ ልማድ የአልጋውን ሸንኮር ይዛ ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት ሙቱ አፈፍ ብሎ ተነስቶ ሰላም ለኪ ኦ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ ሰማይና ምድርን የፈጠረ የአምላክ አያቱ ሐና ሰላም ላንቺ ይሁን ብሎ መስክሮ ተመልሶ አርፏል፡፡
በእናቷ ማኅጸን ሳለችም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአዳም ጅምሮ በዘሩ ሁሉ ሲተላለፍ የነበረው ጥንት አብሶ እመቤታችንን እንዳይነካት ከእናቷ ማኅጸን ጀምሮ ጠብቋታል፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች፡፡በሊባኖስ መወለዷም ሰሎሞን ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ መኃ.መኃ ዘሰሎሞን 4.9 ያለው ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ቤተ-ክርስቲያናችንም "ልደተ ለማርያም" በማለት በዓሉን በቅዳሴ፣ በማህሌት በታላቅ መንፈሳዊ ሐሴት ታከብረዋለች፡፡ ሐናና ኢያቄም እግዚአብሔር በሰጣቸው ልጅ ተደስተው በተወለደች በ8 ቀኗ ማርያም ብለው ስም አወጡላት፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምልጃዋ አትለየን፡፡ሀገራችንን ትጠብቅልን በዓለም ላይ የመጣውን መቅሰፍት ትመልስልን፡፡ዳግመኛ ተሰባስበን በዓሏን ለማክበር ያብቃን አሜን
ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም
«መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው»
/መዝ. ፹፮፥፩/
ስለ እመቤታችን የትውልድ ሐረግ ከመወለዷ በፊት ነብያት በመንፈስ ቅዱስ በመቃኘት ትንቢት ይናገሩ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ በስፋት ያስተምረናል፡፡ ለምሳሌ ያህልም የዝማሬና የትንቢት ጸጋ በእግዚአብሔር የተሰጠው እንደ ልቤ የተባለ ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድሞ ስለ ሥርወልደቷ፣ አምላክን እንደምትወልድ፣ ስለ አማላጅነቷ በመዝሙር ተናግሯል ለምሳሌ በመዝ ፹፮፥፩ ላይ ‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን›› መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ በማለት ከቤተክህነት ከቅዱሳን እንደምትወለድ በምሳሌ ገልፆታል፡፡
ልጁም ጠቢቡ ሰሎሞን መኃ.መኃ.4.9 ‹‹እቴ መርዓት ሙሽርዬ ከሊባኖስ ነይ" እያለ የተወለደችበትን ሀገር እንደጠቀሰ መመልከት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ‹‹ትውፅእ በትር እምሥርው እሰይ ወየዐረግ ጽጌ እምኔሃ›› ትርጉሙም ከእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከርሷ ይወጣል በማለት ተናግሯል ት.ኢሳ ፲፩፩
በሐዲስ ኪዳንም እንደምንመለከተው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ መጀመሪያ የዘር ሐረጉን በዳዊት ጀምሮ እስከ ማታን ይቆጥራል በአይሁድ ልምድ ሴቶች በዘር ቆጠራ ስለማይቆጠሩ ዘፍራን በያዕቆብ ወገን አድርጎ ቆጠረ በዚህም ከዳዊት ወገን መሆኗን አሳውቋል፡፡
የእመቤታችን ወላጆች በምዕራብያውያኑና በምስራቅያውያኑ ዘንድ ታዋቂ በሆነው በመጽሐፈ ያዕቆብ (መጽሐፈ ልደታ ለማርያም) የእናቷ ስም ሐና የአባቷ ስም ኢያቄም እንደሚባል ጽፏል፡፡ ሐና በዕብራይስጥ "ውብ ተወዳጅ" ማለት ነው፡፡ ኢያቄም በዕብራይስጥ እግዚአብሔር የሠራው ያከናወነው ማለት ነው፡፡ እንዳንድ መናፍቃን ለእመቤታችን ካላቸው ጥላቻ የተነሳ አንድ ስለመውለዷ የጻፈ የለም ከአፄ ዘርዓያዕቆብ ውጪ ይላሉ፡፡ ግን ከላይ የተመለከትነው መጽሐፍ በጣም ጥንታዊ በዘመን የማይደራረስ መሆንን የታሪክ ድርሰቶች ይናገራሉ፡፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ የነበረው በ1399-1468 ባሉት ዓመታት ሲሆን ሐዋርያው ታናሽ ያዕቆብ የጻፈውን መጽሐፍ በ150-215 ዓ.ም ሊቁ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ እና ኦርገን እንደተጠቀሙበት እንመለከታለን ቀደምት አባቶቻችን ግን የሐና ቅድመ አባቶቿ ቴክታና ጴጥሪቃ ሲባሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ደግና ቅዱሳን እንደነበሩ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጠጎች ወርቅ ብር የተትረፈረፈላቸው ነበሩ፡፡ ጴጥሪቃ ሀብቱን ሁሉ ከተመለከተ በኋላ ለሚስቱ ይህን ሁሉ ሀብት ምን እናደርገዋለን እንኳን ለእኛ ለልጅ ልጆቻችን ይተርፍ ነበር ግን እኔም አንቺም መካኖች ነን ባላት ጊዜ ቴክታ እግዚአብሔር ከኔ ልጅ ባይሰጥህ ከሌላ ይሰጥህ ይሆነናልና ሌለ አግብተህ ውለድ፡፡ አለችው እሱም ይህን እንኳን ላደርገው እንደማላስበው እግዚአብሔር ያውቃል አላት፡፡ ማታ በህልሟ ቴክታ ነጭ እንቦሳ ከማኅጸኗ ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ሰባተኛዋ ደረሰ ሰባተኛዋ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይታ አድንቃ ለባሏ ነገረችው እሱም በልቡ እያደነቀ ወደ ህልም ፈቺ ጋር ሄደ፡፡ ህልም ፈቺውም ነጫጮቹ እንቦሶች ሰባት ደጋግ ልጆች ይወልዳሉ ሰባተኛዋ ግን በመላዕክት ሁሉ የከበረች ትሆናለች የፀሐይ ነገር ግን አልተገለፀልኝም በማለት ተረጎመላት፡፡ ጴጥሪቃ ሄዶ የህልሙን ፍቺ ነገራት እርሷም የእስራኤል አምላክ የሚያደርገውን እርሱ ያውቃል በማለት ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ በዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች ስሟንም ሔመን አሏት ሔመን ዴርዴን ወለደች ዴርዴም ቶናን ወለደ ቶናም ሲካርን ወለደች ሲካርም ሴትናን ወለደች ሴትናም ሔርሜላን ወለደች ሔርሜላም የተከበረችና የተመረጠች ዓለሙን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ አያት የምትሆን ሐናን ወለደች፡፡ ሐና በመልካም አስተዳደግ አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከነገደ ይሁዳ ወገን ለሚሆን የአላዛር የልጅ ልጅ ለሚሆን የቅስራ ልጅ ከሚሆን ከኢያቄም ዳሯት፡፡ ሐናና ኢያቄም በእግዚዓብሔር የሚወደዱ ደጋጎች ነበሩ ፡፡ ግን ልጅ አልነበራቸውም! ወደ ቤተ መንግስት በመሔድ እግዚዓብሔርን ደጅ ይጠኑት ነበር አንድ ቀን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከቱ በዚህን ጊዜ ሐና "አቤቱ ጌታዬ ግዑዛን እንስሳ ልጅ የሰጠህ ለኔ ለምን ነሳኸኝ" በማለት ሱባኤ ያዙ ኢያቄም ወደ ምድረ በዳ ሄደ ሐናም በቤቱ አትክልት ስፍራ አካባቢ ሱባኤ ያዘች በሱባኤያቸውም ፍፃሜ ራዕይ ተመለከቱ፡፡
ሐናም ለኢያቄም በህልሜ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ አደረች ብላ ነገረችው ምስጢሩም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን ነጭነቷ ንፅህናዋ፣ ቅድስናዋን የሚገልጽ ነው፡፡ ኢያቄምም የተመለከተውን ራዕይ ነገራት በህልሙ ሰባቱ ሰማያት እንደመጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወረደ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ብሎ ነገራት፡፡ ምስጢሩም ወፍ የተባለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ነጭነቱ ንጹሐ ባሕሪ መሆኑን ሲያመለክት ነው፡፡ ይህን ራዕይ ሐምሌ ፴ ቀን ተመልክተው ልጅ ብንወልድ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ትሁን ብለው ተሳሉ እመቤታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ በብስራተ ገብርኤል ነሐሴ ሰባት እሑድ ቀን ተፀንሳለች፡፡እመቤታችን በማኅፀንም ሆና ብዙ ተአምራትን አድርጋለች፡፡ ሁለቱን ለአብነት ያህል እናያለን፡፡
ሐና በርሴባ የምትባል አንድ ዓይና አክስት ነበረቻት ልትጠይቃት መጥታ ሳለ እግዚአብሔር በቸርነት ጎበኘሽ ብላ ማኅፀኗን በዳሰሰችበት እጇ የጠፋ ዓይኗን ብታሸው በርቶላታል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ ሆዷን እየዳሰሱ ድነዋል፡፡
ሐና የምትወደው ሳምናስ የሚባል የአጎቷ ልጅ ሞቶ በቤተሰብ ልማድ የአልጋውን ሸንኮር ይዛ ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት ሙቱ አፈፍ ብሎ ተነስቶ ሰላም ለኪ ኦ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ ሰማይና ምድርን የፈጠረ የአምላክ አያቱ ሐና ሰላም ላንቺ ይሁን ብሎ መስክሮ ተመልሶ አርፏል፡፡
በእናቷ ማኅጸን ሳለችም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአዳም ጅምሮ በዘሩ ሁሉ ሲተላለፍ የነበረው ጥንት አብሶ እመቤታችንን እንዳይነካት ከእናቷ ማኅጸን ጀምሮ ጠብቋታል፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች፡፡በሊባኖስ መወለዷም ሰሎሞን ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ መኃ.መኃ ዘሰሎሞን 4.9 ያለው ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ቤተ-ክርስቲያናችንም "ልደተ ለማርያም" በማለት በዓሉን በቅዳሴ፣ በማህሌት በታላቅ መንፈሳዊ ሐሴት ታከብረዋለች፡፡ ሐናና ኢያቄም እግዚአብሔር በሰጣቸው ልጅ ተደስተው በተወለደች በ8 ቀኗ ማርያም ብለው ስም አወጡላት፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምልጃዋ አትለየን፡፡ሀገራችንን ትጠብቅልን በዓለም ላይ የመጣውን መቅሰፍት ትመልስልን፡፡ዳግመኛ ተሰባስበን በዓሏን ለማክበር ያብቃን አሜን
ፆመ ሐዋርያት
አንዳንዶች የሰኔ ፆም የቄስ ፆም ነው በሚል ከመፆም ወደኋላ ሲሉ ይታያሉ ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን በአዋጅ ከምትፆማቸው ሰባት አፅዋማት አንዱ እንደመሆኑ መጠን እያንዳንዱ ክርስቲያን ቢፆመው እጅግ በርካታ በረከቶችን ያገኝበታል ከነዚህም ጥቂቶችን እነሆ
1.በረከተ ሐዋርያት ይገኝበታል
ይህን ፆም መጀመርያ ፆመው እንድንፆመው ሰርዐት የሰሩልን ሐዋርያት ናቸዉ ስለዚህም ፆሙ መታሰቢያነቱ የሐዋርያት ነው የጻድቅ መታሰቢያ ደግሞ ለበረከት ነው ። ምሳ.10፥7 እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም የሐዋርያቱን በረከት እናገኛለን ሐዋ.13፥1-3 ሐዋ.14፥23
2. በስራችንና በአገልግሎታችን በረከት እናገኛለን
ሐዋርያት ይህን ፆም የፆሙት አገልግሎታቸው እንዲከናወንላቸው እንዲባረክላቸው ነው ነብዩ ነህምያም እየሩሳሌምን የመስራት ተግባሩ እንዲባረክለት በፆመው ፆም ስራው ሁሉ ተባርኮለታል። ነህም.1፥4። እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም በዕለት ተዕለት ተግባራችን በረከት እናገኛለን።
3. ዝናብ ምህረትን ጠለ በረከትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በአገራችን የክረምቱ መግቢያ ላይ የሚፆም ፆም ነው ይህም መጪው የክረምቱ ወራት የተስተካከለ የምህረት ዝናም እንዲኖረው ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል ዘመን ዝናብ ጠፍቶ ዛፎቹ ሳይቀር በደረቁ ጊዜ በፆም በፀሎት ወደ እግዚአብሔር በተማፀኑ ሰዓት ዝናመ በረከትን አግኝተዋል። ኢዩ.1፥13-14
4. በረከተ ምርትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በሃገራችን ገበሬው ዘር መዝራት በሚጀምርበት ጊዜ የሚፆም ፆም ነው ሰለዚህም በዚህ ሰዓት የሚፆመው ፆም ዘርን እንዲባረክ በረከት እንዲበዛ ያደርጋል ይህም አገር ወገን ከረሃብ ከችግር ነፃ እንዲወጣ ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል እንደተገለጸው በፆም የዕህል የመጠጥ በረከት ይገኛል ። ኢዩ.2፥12-14
5. የነፋስ በረከትን እናገኛለን
ፆም በመንፈስ የደከመች የዛለች ነፍስን ያበረታል የነፍስን ቁስል ይፈውሳል ስጋዊ ኃይልን ያደክማል የሥጋን ፈቃድ ለነፍስ ያስገዛል መዝ.108፥24 ፤ ገላ.5፥24 የዓለምን ሃሳብ ያስወግዳል ከእግዚአብሔር ያስታርቃል ማቴ. 17፥21 ሚስጥር ይገልጣል ዘስ.34፥27-28 ፤ ዳን. 10፥1-3 "በአምላካችን ፊት እራሳችንን እናዋርድ ዘንድ ከርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ ...... ፆምን አውጃለሁ " መጽሐፈ ዕዝራ.8፥21 ከመዋዕለ ፆሙ ረድኤት በረከት ያሳትፈን !
ፆሙን የኃጢአት መደምሰሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜንንንን !!!
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @Sihela_adhno 💚
💛 @Sihela_adhno 💛
❤️ @Sihela_adhno ❤
አንዳንዶች የሰኔ ፆም የቄስ ፆም ነው በሚል ከመፆም ወደኋላ ሲሉ ይታያሉ ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን በአዋጅ ከምትፆማቸው ሰባት አፅዋማት አንዱ እንደመሆኑ መጠን እያንዳንዱ ክርስቲያን ቢፆመው እጅግ በርካታ በረከቶችን ያገኝበታል ከነዚህም ጥቂቶችን እነሆ
1.በረከተ ሐዋርያት ይገኝበታል
ይህን ፆም መጀመርያ ፆመው እንድንፆመው ሰርዐት የሰሩልን ሐዋርያት ናቸዉ ስለዚህም ፆሙ መታሰቢያነቱ የሐዋርያት ነው የጻድቅ መታሰቢያ ደግሞ ለበረከት ነው ። ምሳ.10፥7 እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም የሐዋርያቱን በረከት እናገኛለን ሐዋ.13፥1-3 ሐዋ.14፥23
2. በስራችንና በአገልግሎታችን በረከት እናገኛለን
ሐዋርያት ይህን ፆም የፆሙት አገልግሎታቸው እንዲከናወንላቸው እንዲባረክላቸው ነው ነብዩ ነህምያም እየሩሳሌምን የመስራት ተግባሩ እንዲባረክለት በፆመው ፆም ስራው ሁሉ ተባርኮለታል። ነህም.1፥4። እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም በዕለት ተዕለት ተግባራችን በረከት እናገኛለን።
3. ዝናብ ምህረትን ጠለ በረከትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በአገራችን የክረምቱ መግቢያ ላይ የሚፆም ፆም ነው ይህም መጪው የክረምቱ ወራት የተስተካከለ የምህረት ዝናም እንዲኖረው ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል ዘመን ዝናብ ጠፍቶ ዛፎቹ ሳይቀር በደረቁ ጊዜ በፆም በፀሎት ወደ እግዚአብሔር በተማፀኑ ሰዓት ዝናመ በረከትን አግኝተዋል። ኢዩ.1፥13-14
4. በረከተ ምርትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በሃገራችን ገበሬው ዘር መዝራት በሚጀምርበት ጊዜ የሚፆም ፆም ነው ሰለዚህም በዚህ ሰዓት የሚፆመው ፆም ዘርን እንዲባረክ በረከት እንዲበዛ ያደርጋል ይህም አገር ወገን ከረሃብ ከችግር ነፃ እንዲወጣ ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል እንደተገለጸው በፆም የዕህል የመጠጥ በረከት ይገኛል ። ኢዩ.2፥12-14
5. የነፋስ በረከትን እናገኛለን
ፆም በመንፈስ የደከመች የዛለች ነፍስን ያበረታል የነፍስን ቁስል ይፈውሳል ስጋዊ ኃይልን ያደክማል የሥጋን ፈቃድ ለነፍስ ያስገዛል መዝ.108፥24 ፤ ገላ.5፥24 የዓለምን ሃሳብ ያስወግዳል ከእግዚአብሔር ያስታርቃል ማቴ. 17፥21 ሚስጥር ይገልጣል ዘስ.34፥27-28 ፤ ዳን. 10፥1-3 "በአምላካችን ፊት እራሳችንን እናዋርድ ዘንድ ከርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ ...... ፆምን አውጃለሁ " መጽሐፈ ዕዝራ.8፥21 ከመዋዕለ ፆሙ ረድኤት በረከት ያሳትፈን !
ፆሙን የኃጢአት መደምሰሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜንንንን !!!
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @Sihela_adhno 💚
💛 @Sihela_adhno 💛
❤️ @Sihela_adhno ❤
Watch "|| እግዚአብሔርን የምትወዱ || በሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ tewodros yosef ||| Ethiopia mezmure" on YouTube
https://youtu.be/F0BtpQ7nMIg
https://youtu.be/F0BtpQ7nMIg
YouTube
|| እግዚአብሔርን የምትወዱ || በሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ tewodros yosef ||| Ethiopia mezmure
የእኛን መንፈሳዊ አገልግሎት መደገፍ ማስቀጠል ይፈልጋሉ እንግዲያውስ #SUBSCRIBE በማድረግ ብቻ እኛን ማበረታታት ይችላሉ ።
➠ ለ Telegram
https://t.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
➠ ለ Telegram
https://t.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
Watch "ብፁዕነታቸው ለምን አይናገሩም | Ethiopia" on YouTube
https://youtu.be/7Zb8lymP8Ac
https://youtu.be/7Zb8lymP8Ac
YouTube
ብፁዕነታቸው ለምን አይናገሩም | Ethiopia
የእኛን መንፈሳዊ አገልግሎት መደገፍ ማስቀጠል ይፈልጋሉ እንግዲያውስ SUBSCRIBE በማድረግ ብቻ እኛን ማበረታታት ይችላሉ ማንም ሰው ይህን አይቶ በቸልተኝነት እንዳያልፍ በእግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። ስለ ትብብርዎ ከልብ እናመሰግናለን
➠ ለ Telegram
https://t.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema…
➠ ለ Telegram
https://t.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema…
Watch "በስራዬ የት ይሆን መግቢያዬ ortodox mezmur" on YouTube
https://youtu.be/uDA2hwu1404
https://youtu.be/uDA2hwu1404
YouTube
በስራዬ የት ይሆን መግቢያዬ ortodox mezmur
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
ሰላም ለእናንተ በአይነቱ ለየት ያለ የእናንተን የቮይስ ቅጂ ዝማሬ #ቻሌንጅ የምናቀርብበት ቻናል ይቀላቀሉንን ይማሩበታል በዝማሬ አምላክን ያመሰግኑበታል 👇👇👇👇👇👇👇👇
@tewahidoortodox
@tewahidoortodox
Inbox👇
@kidanemiherat_bot
@tewahidoortodox
@tewahidoortodox
Inbox👇
@kidanemiherat_bot
🎚🎚🎚🎚
"🎚🎚 እግዚአብሔር ታማኝ ነው"
እግዚአብሔር ታማኝ ነው። የእኛ አለመታመን የእግዚአብሔርን ታማኝነት አያጎድለውም።የእኛ በደለኛነት የእግዚአብሔርን አባትነት አይቀንሰውም።እግዚአብሔር ሁልጊዜም እግዚአብሔር ነው።ከገዘፈው ነውራችን ይልቅ ጥቃቅኗን ጽድቃችንን እየቆጠረ ለተሻለ ክብርና ለላቀ ጸጋ የሚሻን ርኅሩኅ አባት ነው።ስንረቀው ይቀርበናል፣ስንሸሽው ይከተለናል፣ስንጠፋም ይፈልገናል።ዲያብሎስ ሰብሮ ሲጥለን እግዚአብሔር ጠግኖ ያቆመናል።ዓለም ንቃ ስታዋርደን፣እግዚአብሔር ግን ወዶ ያከብረናል ።በበድልና በኃጢአታችን ምክንያት ሕይወታችን ጣዕም አልባ ልባችን እረፍት አልባ ሲሆን እግዚአብሔር ግን በፍጹም ይቅርታና ምኅረት ዳግመኛ ሌላ እድል እየሰጠ አፋችንን በሳቅ ከንፈራችንን በእልልታ ይሞላል።የውርደት ማቃችንን ቀዶ ደስታን ያስታጥቀናል።
የሰው ልጅ ባልተጠራበት ቦታ ትርፍ በተጠራበት ቦታ ግን ዋና ነው።የተጠራ ነው ለክብር ነው ፣የልጁ መልክ በእኛ እስኪሳል፤ክብርና ባለጠግነት የሕይወታችን አክሊል እስኪሆን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት ቀርበን የመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች እስክንሆን እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቶናል።ዋናችን ክርስቶስ ክብራችንም መንግስቱ ነው።በጽድቃችን ሳይሆን በጸጋው የሚያወርሰንን ርስት በልግስና ለመስጠት እግዚአብሔር የታመነ ነው።
አልገባ ብሎን ነው እንጂ ዓለም የእኛ እኛም የዓለም አይደለንም።በዓለም እየኖርን ከዓለም የተለየን የመንግስተ ሰማያት ዜጎች ነን።ከሰማያዊ ጥሪ ተካፋይ የሆናችሁ ወገኖች ሆይ የእምነታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህን የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ተመልክተን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ።ሀገራችን በሰማይ ነው።ይህ ድንኳን የሆነው የምድራዊ ኑሯችን ፍጹም ከንቱና ጊዚያዊ ነው።ለጊዚያዊ የድንኳን ኑሮ እንዴት ሰው በወገኑ ደም ላይ ይቆማል ፣እንኳንስ ለጸብ ለፍቅር በማትበቃ እድሜስ እንዴት ሰው የወንድሙን መቃብር ይምሳል።የይቅርታን ድምጽ ከመስቀል ላይ የሰማ አማኝ ፣ የሰላምን ወንጌል ከፍቅር መምህር ያደመጠ ክርስቲያን እንዴት ለኩርማን መሬትና ለቁራሽ እንጀራ ፍቅርን በጸብ ይለውጣል።እንኳን ደረቅ መሬት እኛስ አፈር አይደለንም ወይ?እግዚአብሔር ያልባረከው በደም የተገኘ ርስት እርሱ አኬልዳማ የደም መሬት ነው።ቢዘሩበት እሾህ ቢያርሱበት አሜኬላ የሚያበቅል የእርግማን ምድር ነው።
እርስትም ብቻ አደለም ባለን ጥቂት ነገር እንኳ በፍቅር ተካፍለን እንኑር። በጥቂቱ ያልታመነ በብዙ አይሾምምና። ለትንሽ ነገር ስግብግቦች ራስ ወዳዶች አንሁን እግዚአብሔር ከሌለበት ጎተራ እግዚአብሔር ያለበት ጥቂት ነገር ይበልጣል። ስስት ሲኖር ፍቅር ይጠፋል፣ ፍቅር ሲጠፋ ጭካኔ እና ጥላቻ ይሰፍንብናል። በፍቅር የማካፈል ልምድ የምንጀምረው ከጥቂቷ ነገር ነውና ለኛ ይጠቅመናል ብለን የምናስባትን ትንሿ መልካም ነገር ለሌላውም እንመኛት።
በክርስቶስ ወንድሜ የሆንክ ወገኔ እባክህ ወደ ልብህ ተመለስ ደም ዘርተህ ደም አትጨድ ፤የወንድምህን ነፍስ አጥፍተህ ተናጥቀህ የምትይዘው ርስት ደዌና ደረመን በሕይወትህ ያመጣል እንጂ በረከትና ጥጋብ አይሆንልህም።በፍቅር ከሆነ ግን በኩርማን መሬት ላይ ጎተራህን ሊሞላ እግዚአብሔር የታመነ ነው።
እግዚአብሔር የልጁ የክርስቶስ ልብ እንዲኖረን በልዩ መለኮታዊ ክብር ጦርቶናልና የጠላት ዲያብሎስን ሐሳብ ጠንቅቀን አውቀን ጸብን በይቅርታ ጥላቻንም በፍቅር እንተካ።
"🎚🎚 እግዚአብሔር ታማኝ ነው"
እግዚአብሔር ታማኝ ነው። የእኛ አለመታመን የእግዚአብሔርን ታማኝነት አያጎድለውም።የእኛ በደለኛነት የእግዚአብሔርን አባትነት አይቀንሰውም።እግዚአብሔር ሁልጊዜም እግዚአብሔር ነው።ከገዘፈው ነውራችን ይልቅ ጥቃቅኗን ጽድቃችንን እየቆጠረ ለተሻለ ክብርና ለላቀ ጸጋ የሚሻን ርኅሩኅ አባት ነው።ስንረቀው ይቀርበናል፣ስንሸሽው ይከተለናል፣ስንጠፋም ይፈልገናል።ዲያብሎስ ሰብሮ ሲጥለን እግዚአብሔር ጠግኖ ያቆመናል።ዓለም ንቃ ስታዋርደን፣እግዚአብሔር ግን ወዶ ያከብረናል ።በበድልና በኃጢአታችን ምክንያት ሕይወታችን ጣዕም አልባ ልባችን እረፍት አልባ ሲሆን እግዚአብሔር ግን በፍጹም ይቅርታና ምኅረት ዳግመኛ ሌላ እድል እየሰጠ አፋችንን በሳቅ ከንፈራችንን በእልልታ ይሞላል።የውርደት ማቃችንን ቀዶ ደስታን ያስታጥቀናል።
የሰው ልጅ ባልተጠራበት ቦታ ትርፍ በተጠራበት ቦታ ግን ዋና ነው።የተጠራ ነው ለክብር ነው ፣የልጁ መልክ በእኛ እስኪሳል፤ክብርና ባለጠግነት የሕይወታችን አክሊል እስኪሆን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት ቀርበን የመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች እስክንሆን እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቶናል።ዋናችን ክርስቶስ ክብራችንም መንግስቱ ነው።በጽድቃችን ሳይሆን በጸጋው የሚያወርሰንን ርስት በልግስና ለመስጠት እግዚአብሔር የታመነ ነው።
አልገባ ብሎን ነው እንጂ ዓለም የእኛ እኛም የዓለም አይደለንም።በዓለም እየኖርን ከዓለም የተለየን የመንግስተ ሰማያት ዜጎች ነን።ከሰማያዊ ጥሪ ተካፋይ የሆናችሁ ወገኖች ሆይ የእምነታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህን የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ተመልክተን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ።ሀገራችን በሰማይ ነው።ይህ ድንኳን የሆነው የምድራዊ ኑሯችን ፍጹም ከንቱና ጊዚያዊ ነው።ለጊዚያዊ የድንኳን ኑሮ እንዴት ሰው በወገኑ ደም ላይ ይቆማል ፣እንኳንስ ለጸብ ለፍቅር በማትበቃ እድሜስ እንዴት ሰው የወንድሙን መቃብር ይምሳል።የይቅርታን ድምጽ ከመስቀል ላይ የሰማ አማኝ ፣ የሰላምን ወንጌል ከፍቅር መምህር ያደመጠ ክርስቲያን እንዴት ለኩርማን መሬትና ለቁራሽ እንጀራ ፍቅርን በጸብ ይለውጣል።እንኳን ደረቅ መሬት እኛስ አፈር አይደለንም ወይ?እግዚአብሔር ያልባረከው በደም የተገኘ ርስት እርሱ አኬልዳማ የደም መሬት ነው።ቢዘሩበት እሾህ ቢያርሱበት አሜኬላ የሚያበቅል የእርግማን ምድር ነው።
እርስትም ብቻ አደለም ባለን ጥቂት ነገር እንኳ በፍቅር ተካፍለን እንኑር። በጥቂቱ ያልታመነ በብዙ አይሾምምና። ለትንሽ ነገር ስግብግቦች ራስ ወዳዶች አንሁን እግዚአብሔር ከሌለበት ጎተራ እግዚአብሔር ያለበት ጥቂት ነገር ይበልጣል። ስስት ሲኖር ፍቅር ይጠፋል፣ ፍቅር ሲጠፋ ጭካኔ እና ጥላቻ ይሰፍንብናል። በፍቅር የማካፈል ልምድ የምንጀምረው ከጥቂቷ ነገር ነውና ለኛ ይጠቅመናል ብለን የምናስባትን ትንሿ መልካም ነገር ለሌላውም እንመኛት።
በክርስቶስ ወንድሜ የሆንክ ወገኔ እባክህ ወደ ልብህ ተመለስ ደም ዘርተህ ደም አትጨድ ፤የወንድምህን ነፍስ አጥፍተህ ተናጥቀህ የምትይዘው ርስት ደዌና ደረመን በሕይወትህ ያመጣል እንጂ በረከትና ጥጋብ አይሆንልህም።በፍቅር ከሆነ ግን በኩርማን መሬት ላይ ጎተራህን ሊሞላ እግዚአብሔር የታመነ ነው።
እግዚአብሔር የልጁ የክርስቶስ ልብ እንዲኖረን በልዩ መለኮታዊ ክብር ጦርቶናልና የጠላት ዲያብሎስን ሐሳብ ጠንቅቀን አውቀን ጸብን በይቅርታ ጥላቻንም በፍቅር እንተካ።
የ"7" ቁጥር ምስጢራት"
= = =
➭ሰባት ቁጥር ጥልቅ ምሳሌና ትርጓሜ አለው።በዕብራውያን ዘንድ ሰባት ቁጥር ፍጹም ቁጥር ነው።
➭እግዚአብሔር ከሰኞ እስከ ዕሁድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል።(መ.ምሳሌ 24፥16)
➭እስራኤላውያን ከግብፅ ባርነት ነጻ ወጥተው በሲና በረሃ ሲጓዙ ይመሩ የነበረው በሰባት ደመና ነበር።(ዘዳ 13፥21)
➭እስራኤላውያን ኢያሪኮን ለሰባት ተከታታይ ቀናቶች እንዲዞሯት፣በሰባተኛው ቀን ደግሞ ሰባት ጊዜ እንዲዞሯት ታዘው ነበር። (ኢያሱ 6፥15)
➭ጴጥሮስ ወንድሙን ይቅር እንዲለው የታዘዘው እስከ ሰባት ጊዜ ሰባ እንጂ ሰባት ጊዜ ብቻ አልነበረም።
(ማቴዎስ 18፥21, 22)
➭ሌላው የሰባት ቁጥር ምሳሌዎች በጥቂቱ እንደሚከተለው ይቀርባሉ።
ሰባቱ አባቶች
= = =
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ሰባቱ ዲያቆናት
= = =
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሰባት የጌታ ቃላት(እኔ ነኝ)
= = =
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
ሰባቱ ሰማያት
= = =
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
= = =
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
= = =
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰባቱ ተዐምራት
= = =
➭ጌታ የሰው ልጆችን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት፦
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
= = =
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
= = =
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
= = =
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች (ምሳ 16፥6-19)
= = =
1. ትዕቢተኛ ዓይን
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
= = =
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ሰባቱ የዳዊት ሐብታት
= = =
1. ሐብተ ፈውስ
2. ሐብተ ትንቢት
3. ሐብተ በገና
4. ሐብተ መንግስት
5. ሐብተ መዊዕ
6. ሐብተ ኃይል
7. ሐብተ ክህነት
7 ቀናት፣7 ፊደላት፣7 ሰው የተፈጠረበት ባህርያት፣......
= = =
➭ሰባት ቁጥር ጥልቅ ምሳሌና ትርጓሜ አለው።በዕብራውያን ዘንድ ሰባት ቁጥር ፍጹም ቁጥር ነው።
➭እግዚአብሔር ከሰኞ እስከ ዕሁድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል።(መ.ምሳሌ 24፥16)
➭እስራኤላውያን ከግብፅ ባርነት ነጻ ወጥተው በሲና በረሃ ሲጓዙ ይመሩ የነበረው በሰባት ደመና ነበር።(ዘዳ 13፥21)
➭እስራኤላውያን ኢያሪኮን ለሰባት ተከታታይ ቀናቶች እንዲዞሯት፣በሰባተኛው ቀን ደግሞ ሰባት ጊዜ እንዲዞሯት ታዘው ነበር። (ኢያሱ 6፥15)
➭ጴጥሮስ ወንድሙን ይቅር እንዲለው የታዘዘው እስከ ሰባት ጊዜ ሰባ እንጂ ሰባት ጊዜ ብቻ አልነበረም።
(ማቴዎስ 18፥21, 22)
➭ሌላው የሰባት ቁጥር ምሳሌዎች በጥቂቱ እንደሚከተለው ይቀርባሉ።
ሰባቱ አባቶች
= = =
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ሰባቱ ዲያቆናት
= = =
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሰባት የጌታ ቃላት(እኔ ነኝ)
= = =
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
ሰባቱ ሰማያት
= = =
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
= = =
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
= = =
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰባቱ ተዐምራት
= = =
➭ጌታ የሰው ልጆችን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት፦
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
= = =
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
= = =
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
= = =
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች (ምሳ 16፥6-19)
= = =
1. ትዕቢተኛ ዓይን
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
= = =
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ሰባቱ የዳዊት ሐብታት
= = =
1. ሐብተ ፈውስ
2. ሐብተ ትንቢት
3. ሐብተ በገና
4. ሐብተ መንግስት
5. ሐብተ መዊዕ
6. ሐብተ ኃይል
7. ሐብተ ክህነት
7 ቀናት፣7 ፊደላት፣7 ሰው የተፈጠረበት ባህርያት፣......
Watch "ቅድስት እንባ መሪና (kidest inba merina) Ethiopia ortodox tewahido" on YouTube
https://youtu.be/oIOUpGvnL8c
https://youtu.be/oIOUpGvnL8c
YouTube
ቅድስት እንባ መሪና (kidest inba merina) Ethiopia ortodox tewahido
ዝግጅታችን ጊዜ ሰተው ስለተመለከቱ እናመሰግናለን ዝግጅቱ ሌሎች ቢመለከቱትና ቢያውቁት መልካም ነው ብለው ካሰቡ #ኪነ_ተዋህዶ #share #like subscribe
Watch "የኤፍራጥስ ወንዝ | Ethiopian ortodox tewhido | ye ephratos wanze | Hana dagnew |" on YouTube
https://youtu.be/F-oSpBHzAQA
https://youtu.be/F-oSpBHzAQA
YouTube
የኤፍራጥስ ወንዝ | Ethiopian ortodox tewhido | ye ephratos wanze | Hana dagnew |
ዝግጅታችን ወደው ጊዜ ሰተው ስለተመለከቱ እናመሰግናለን ዝግጅቱ ሌሎች ይመለከቱት ዘንድ Share like በማድረግ እናጋራ
Thanks Waching .....
#Kinetewahido #ኪነተዋህዶ #Subscribe
Thanks Waching .....
#Kinetewahido #ኪነተዋህዶ #Subscribe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🎬 ©አለምን የያዙት መዳፎቹ" ዘማሪ አብርሐም ያደታ | zemary abrham yadeta
👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ
⚠️ ዝማሬውን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ
⚠️ ዝማሬውን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
https://youtu.be/F26Nnc6DHyk
ውድ የተዋህዶ ልጆች እስቲ ዛሬ አንድ ነገር ላስቸግራቹ በፎቶው እንዳያቹች እናት ቤተክርስትያናችን በዩቱብ ተከታይ ያላትና መስቀል ከሚያስበጥሰው ebs ያለውን ልዩነት እዩት ያሳዝናል እውነት ebs ሰብስክራይብ አድርገን EOTC TV ካላደረግን በጣም ያሳዝናል
EOTC 21.8 ሺ
EBS 1.05 ሚሊዮንንንን
አሁን ሁላችንም EOTC TV & ማህበረ.ቅዱሳን SEBSCRIBE እናድርግ
ለሌሎች ያጋሩ
@embtee
EOTC 21.8 ሺ
EBS 1.05 ሚሊዮንንንን
አሁን ሁላችንም EOTC TV & ማህበረ.ቅዱሳን SEBSCRIBE እናድርግ
ለሌሎች ያጋሩ
@embtee
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM