✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.06K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
AUD-20190211-WA0004.m4a
6.4 MB
*ነገረ ክርስቶስ*

🎙ሊቀ ሊቃውንት ስማዕኮነ እና ሊቃውንት🎙

*👉🏾ቅብዓት እና ጸጋ ምንድን ነው*

*ተዋህዶ ማለት ምን ማለት ነው?*

@embtee @embtee

(የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 1)
----------
1፤ *📖በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።*
. . .@embtee @embtee
14፤ *ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።*
@embtee @embtee


*ማኅበረ ቅዱሳን የስብከት ወንጌል ክፍል 1⃣*👆🏼👆🏼👂🏽👂🏽
AUD-20190213-WA0005.m4a
6.3 MB
*ያለ ጭንቀት መኖር*

🎙መምህር ምእረትአብ አሰፋ


(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 6)
----------
25፤ *📖ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና ፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?*

. . .
27፤ *📖ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?*

28፤ *ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤*

29፤ *አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም።*

. . .
31፤ *እንግዲህ። ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤*

*ማኅበረ አትናትዮስ መልስ ለአህዛብ ክፍል 2⃣*👆🏼👆🏼👂🏽👂🏽
*35:26*

@embtee
@embtee 🌸🌺🌸🌺
@embtee
#የካቲት_11_ፆመ_ነነዌ_ይጀምራል
"#ምነው_ተኝተሃል? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።
#የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባጃ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው

++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።

++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።

++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )
የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ ፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
✟ ̲̲̅̅የ̫̫እ̫̫መ̫̫ብ̫̫ር̫̫ሀ̫̫ን̫̫ ል̫̫ጆ̫̫ች̫̫ ̫[ማ̲̲̅̅ህ̲̲̅̅በ̲̲̅̅ር̲̲̅̅] ✟̫̫
┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶
፠ ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፍቅር ናት ኑ ተማሩ

⛔️ የእናታችን የቅድስተ ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች ኑ እንሰባሰብ

፨ለመሳተፍ ፍላጎት ያለው ብቻ ይቀላቀል ለመቆጠር ብቻ አይሁን

ማንም ሊያመልጠው አይገባም ለበረከት ይሳተፉ
┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽
/adminlist
Creator @yitaya
https://t.me/embrhan_lijoch
Audio
*ወደ እኔ ተመለሱ*

🎙መምህር ፍቃዱ ሳህሌ

@embtee
@embtee
👉 @embtee
*📖" ከአባቶቻችሁ ዘመን ጀምር ከሥርዓቴ ፈቀቅ ብላችኋል፥ እርስዋንም አልጠበቃችሁም። ወደ እኔ ተመለሱ፥ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እናንተ ግን። የምንመለሰው በምንድር ነው? ብላችኋል። "*
(ትንቢተ ሚልክያስ 3:7)

*👇🏽የነነዌን ፃም እንዴት እንጹም?*
@embtee
@embtee
👉 @embtee
*📖" ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።* "
(ትንቢተ ዮናስ 1:2)

*ማኅበረ ቅዱሳን የስብከት ወንጌል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ይቅርታ በመዘግየታችን*👆🏼👆🏼👂🏽👂🏽

@embtee
@embtee
👉 @embtee
4_6014669336575215298.m4a
28.8 MB
🎬 የአብርሃም ጥያቄ። በክቡር ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ - ድንቅ ትምህርት አና መልአክት ለተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች።
👤 (መታየት ያለበት👂👂👂)👇👇👇👇



@embtee
@embtee
@embtee
AUD-20190223-WA0003.m4a
7.1 MB
*መልካም ባልንጀርነት*

🎙ሊቃውንት አባቶች🎙

*👇🏽ባልንጀርነት በመፀሀፍ ቅዱስ*

*📖" አትበቀልም፥ በሕዝብህም ልጆች ቂም አትያዝ፥ ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ። "*
(ኦሪት ዘሌዋውያን 19:18)

*👇🏽ከእኔ ወንድሜ ይበልጣል ማለትን*

*📖" እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድ ስንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ።"*
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎችን 10:24)

*📺የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የቴሌቭዥን የምክረ ካህን መርሃ ግብር*👆🏼👆🏼👂🏽👂🏽


@embtee
@embtee
@embtee
የጸሎት ጊዜ የለኝም

በጃፓን ሀገር የምትኖር አንዲት አረማዊ የነበረች ሴት በኋለኛዋ ዘመን ክርስቲያን ትሆናለች፡፡ ነገር ግን ከድህነቷ የተነሳ የጸሎት ጊዜ አልነበራትም፡፡ አንድ ቀን ክርስቲያን ጎረቤቶችዋ መጥተው አንቺ ክርስቲያን ሆኛለሁ ብለሽ የለ እንዴ? ታድያ እንደ ክርስቲያኖች ስትጸልይ ድምጽሽን ሰምተን አናውቅም አሏት፡፡ እርሷም እኔ ድሃ ስለሆንኩ ስራ ስለሚበዛብኝ ጸሎት ለማድረስ የእረፍት ጊዜ የለኝም አለቻቸው፡፡ ነገር ግን በየጊዜው ጸሎት አቋርጬ አላውቅም፤ ጠዋት ከመኝታዬ ስነሳ ቀሚሴን ስለብስ አቤቱ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንደዚህ አልብሰኝ እለዋለሁ፡፡ ውሃ አቅርቤ ፊቴን ስታጠብ አቤቱ የልቤን እድፍ በመንፈስ ቅዱስ አጥበህ ንጹህ አድርግልኝ እለዋለሁ፡፡እሳት አቅርቤ ብዙ እንጨት ጨምሬ ሲነድ ባየሁ ጊዜ አቤቱ ልቤ በፍቅረ መንፈስ ቅዱስ እንዲህ እንዲቃጠል አድርግልኝ እለዋለሁ፡፡ መልካም ሩዝ ቀቅዬ በስሎ በምበላበት ጊዜ አቤቱ ከረሀበ ነፍስ እንድድን መንፈሳዊ ምግብ አዘጋጅልኝ እለዋለሁ፡፡ ልብሴን አጥቤ በመተኮሻ ተኩሼ ቀጥ ሲል ባየሁት ጊዜ አቤቱ ቀጥ ያለና የቀና ልብ ስጠኝ እለዋለሁ፡፡ እንደዚህ እያደረግሁ ሥራዬንና ጸሎቴን በአንድነት እጨርሳለሁ እንጂ የተወሰነ የጸሎት ጊዜ የለኝም አለቻቸው፡፡

ምንጭ፡- ጎሀ ጽባህ ገጽ 97
✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧
(ሳናቋርጥ መጸልይ እንዳለብን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል "ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተፀምዶ መዋል አይችልም አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው ድምፅ ሳይኾን አሳብ ነው፤ እጅ ሳይኾን እደ ልቦናን ማንሣት ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፣ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከኾነ ጸሎትህ ሥልጡን ነው።")

አት ገድላት ቻናል የተገኘ

@embtee
@embtee
👉@embtee
💒#እንኳን_ለመላዕኩ_ለቅዱስ_ኡራኤል_ወርሃዊ_መታሰቢያ_በዓል_በሠላም_አደረሳችሁ!!!💒

♦️ዑራኤል የሚለው ስም `ዑር' እና 'ኤል' ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
#ዑር ማለት በእብራይስጥ #ብርሃን ማለት ሲሆን
#ኤል ማለት ደግሞ #አምላክ ማለት ነው ።

አንድ ላይ ሲነበብ #ኡራኤል ማለት #የብርሃን #አምላክ ወይም #የብርሃን #ጌታ ማለት ነው ።

ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ፣ ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልዓክ ነዉ። በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መጽ/ሄኖክ 6 ፡ 2 ፣ ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሀይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መጽ/ሄኖክ 28 ፡13

የቅዱስ ኡራኤል በረከት ረድኤቱ ይደርብን !
ምልጃ ጥበቃዉ አይለየን!

ቅድስት ሀገራችንን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን!!!
💚💛❤️
@embtee
@embtee
🌿💚💛❤️🌿
@embtee
AUD-20190303-WA0006.opus
1.4 MB
አቡይ ፆም ለምን አብይ ተባለ

🍃 ስንፆ እንዴት መሆን አለበት

የ10 ደቂቃ ነው አዳምጡት 👂👂👂

መልካም ፆም ለሁላችን💒

@embtee
@embtee
@embtee
✟ ̲̲̅̅የ̫̫እ̫̫መ̫̫ብ̫̫ር̫̫ሀ̫̫ን̫̫ ል̫̫ጆ̫̫ች̫̫ ̫[ማ̲̲̅̅ህ̲̲̅̅በ̲̲̅̅ር̲̲̅̅] ✟̫̫
┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶
፠ ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፍቅር ናት ኑ ተማሩ

⛔️ የእናታችን የቅድስተ ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች ኑ እንሰባሰብ

፨ለመሳተፍ ፍላጎት ያለው ብቻ ይቀላቀል ለመቆጠር ብቻ አይሁን

ማንም ሊያመልጠው አይገባም ለበረከት ይሳተፉ
┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽
/adminlist
Creator @yitaya
https://t.me/embrhan_lijoch
Audio
#ከሰማይ #ሰማያት #ወረደ

🎙አባ ሃይለማርያም🎙

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 18)
----------
11፤ የሰው ልጅ የጠፋውን ለማዳን መጥቶአልና።

12፤ ይመስላችኋል? ለአንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩት ከእነርሱም አንዱ ቢባዝን፥ ዘጠና ዘጠኙን በተራራ ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን?

ማኅበረ ቅዱሳን የስብከት ወንጌል👆🏼👆🏼👂🏽👂🏽

@embtee
@embtee
@embtee
📣📣📣📣📣📣📣📣📣🔴

አስቸኳይ ማስታወቂያ ይነበብ

በስ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

ከፊታችን የሚካሄደው የህዝብ ቆጠራ ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ሀይማኖቶች የኦክቶዶርስን እምነት ሊያጠፉ ይፈልጋሉ !!!
እናም ቆጠራ በሚካሄድበት ጊዜ ሀይማኖቶን ይንገሩ ኦ ር ቶ ዶ ክ ስ በሉ
😟😟 አስተውሉ 😟😟
በክርስቲያን እምነት ውስጥ ከ 35.000 በላይ የሚሆኑ እምነቶች አሉ እናም ኦክቶዶርስ ነኝ በማለት እምነታችን እንዳይጠፋ እንጠብቅ።
አስቡት እስቲ አሁን የመንግስት ሰራተኖች እረፍታቸው በሰንበት (እሁድ) ነው እረፍታቸው ግን የሀይማኖታችን ቁጥር ካነሰ ይቀየራል ለምሳሌ እስላሞች አርብ ጁማቸው ነው የእነሱ ቁጥር ከበለጠ የመንግስት ሰራተኖች እረፍታቸው የሚሆነው አርብ ቀን ነው እናስብ ሀይማኖታችን እንዳይጠፍ ጥር 11 የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ በአልም ሊቀር ይችላል እባካችሁ ሀይማኖታችንን እንጠብቅ ሆነም ቀረም የሚጎል የለም ከቤታችን ግን በስም ስተት ኦርቶዶክስ ባለማለታችን ወደሌላ እምነት ነውና የሚቆጠረው እንጠንቀቅ ባለማወቅ ክርስትያን ለሚሉ ይንገሩ {ኦርቶዶክስ} ብቻ ብቻ እያያቹት አስመዝግቡ ። ቢያንስ አንድ ኦክቶዶስ ለጋደኞቹ 10 ሰው ቢልክ ሀይማኖቱን ይጠብቃል
የመድሀኒታች እናት ቅድስት ድንግል ማርያም እቅፍ ድግፍ ታድርገን
@zemaryan
ለተዋህዶ ቤ/ን የተደገሰ ቀላል የሚመስል ግን ከባድ አደጋ!!!!!!!!!!
ማንም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ የሆነ ሁሉ Share Share ማድረግ አለበት።
~አባቶቻችን ወዴት ሄዱ?
_÷÷÷÷÷____________
ለተዋህዶ ቤ/ን የተደገሰ ቀላል የሚመስል ግን ከባድ አደጋ!!!!!!!!!!
የህዝብና ቤት ቆጠራ ፎርም ላይ ስለተቆጣሪዎች ሃይማኖት ሲያስቀምጥ ኦርቶዶክስ የሚለውን ሦስት ቦታ ተዋህዶ ፀጋ እና ቅባት በማለት ከፋፍሎታል፡፡ ይሄ ላይላዩን ሲያዩት ቀላል የሚመስል ነገር ግን ለቤተክርስቲያናችን ቀጣይ ሰቆቃና ክፍፍልን ለመደገስ የተቀበረ አደገኛ ፈንጅ ሆኖ ይታየኛል!!
ከዚህ በፊት የእምነት ልዩነት ሳይኖር በአስተዳደር ጉዳይ እንኳ ለሩብ ክፍለ ዘመን መዘባበቻ ሆነን እየተወጋገዝን ኖረናል፡፡ የሚያስታርቅ መስቀል ይዘዉ የማይታረቁ እየተባልንም ተስቆብናል፡፡ ይህንን ልዩነት እያዩ የተለዩንም ብዙዎች ናቸዉ፡፡ ችግራችን ተፈታ እፎይ አንድ ሆንን ብለን አንድ ዓመት ሳይሞላን ቤ/ንን አስከወዲያኛው የሚበታትን ድምጽ አልባ ፈንጅ እየተቀበረልን ነው፡፡ የአሁኑ ይባስ! ለመሆኑ ከሐሜት በዘለለ የቅባት እምነት ተከታይ ነኝ የሚሉ ሰዎች በተቋም ደረጃ በአሁኑ ጊዜ አሉ ወይ??? ፀጋ ነን የሚሉስ ??? ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ ብላ አንድ ሆና የቆመችን ዓለም አቀፋዊት ተቋም እኔ አውቅልሻለሁ ብሎ በሦስት መክፈልስ አግባብ ነዉ ወይ???? ይህንን የማድረግ ስልጣኑ ያለዉ ማነው??? ተሃድሶ ነን ብለው ከሁሉም እምነት ተቋማት ዉጭ የቆሙትን አይቶ ያላካተተ ፎርም እነዚህ ምናባዊ ነገሮች እንዴት ታዩት??? ስጋቴ፦ 1.የቤተክርስቲያናችንን በጎ የማይፈልጉ አካላት ባልዋሉበትና በማያዉቁት ቅባትና ፀጋ ነን እያሉ ሊቆጠሩ ይችላሉ፡፡
2.አንዳንዶችንም በጥቅም በመደለል እንዲቆጠሩ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡
3.ከትንሽ ጊዜ በኃላ መንግሥት እውቅና ሰጥቶ ቆጥሮናል ስለዚህ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስር አንቀጥልም እንገነጠላለን ሊሉ ይችላሉ፡፡
4.የሰራናቸዉን አብያተ ክርቲያኖች እና ህዝብ ከፍለው ይወጡና ቤ/ንንም እሰከ መጨረሻዉ ሊለያዩዋት ይችላሉ፡፡ ይህና የመሳሰለዉ የእኔ ስጋት ነው፡፡ መፍትሔ የምለዉ ደግሞ በቅድሚያ ይህንን ሴራ አውጥተው ለጠቆሙን ድርጅቱ ዉስጥ ለሚሰሩት የተዋህዶ ልጆች ምስጋና እያቀረብኩ መፍትሔ የምለው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ ተብሉ ፎርሙ እንዲቀየር ማስደረግ ብቻ ነው ፡፡ ይህ የሚሆነው ደግሞ ሁላችንም በየ ሀገረ ስብከታችን ሊቃነ ጳጳሳት ዘንድ ቀርበን ጉዳዩን በማስረዳትና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወያይተዉ እንዲያስቀይሩት በማድረግ ነዉ!!! ፡፡ ስጋቴን የምትጋሩ ሃሳቤን አጋሩት (ሼር) አድርጉት፡፡
           #ሳልፆም_ሊፈሰክ_ነው አይ የኔ ነገር !


እርግጥ አልበላሁም #ስጋም ሆነ #ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ #አመፀኛ_ልቤ
ካምናና ካቻምና #የዘንድሮ_ብሶ
መላ ማንነቴ #በሀጢያት_ተለውሶ
#ስዋሽ_ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
#ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
#አይ_እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
#ጌታ_ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
#እስቲ_የቀረውን ለበረከት በለው
#አመፀኛ_ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር"
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM