Forwarded from Deleted Account
AUD-20181214-WA0004.amr
1.8 MB
AUD-20181222-WA0028
<unknown>
AUD-20181224-WA0032
<unknown>
AUD-20181227-WA0005
<unknown>
++ በሦስቱ ወጣቶች እምነት የእሳት ኃይል በእሳት ጠፋ ዳን
3÷1-30!! ++
እግዚአብሔርን የካደ በጉልበቱ የተመካ ሥልጣንን ክብርን
ባዕለጠግነትን መፈራትን የሰጠውን ፈጣሪውን የዘነጋ ሰው ንጉሥ
ናቡከደነጾር በባቢሎን ምድር በዱራ ሜዳ ላይ ቁመቱ ስድሳ ክንድ
ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነ የወርቅ ምስል አቁሞ ሕዝቡ በሙሉ
ለእርሱና ለጣዖት ይሰግዱ ዘንድ አዋጅን አወጀ ፡፡ ሕዝቡም
አዋጁን ተከትለው ንጉሥ ላቆመው ጣዖት እንደ ግንድ እየተረበረቡ
እንደ ሻሽ እየተነጠፉ ይሰግዱ ጀመር ፡፡ እግዚአብሔር ሀገርን
ዘመንን ያለ ደጋግ ሰዎች አይተውምና ስቶ በጣዖት ፍቅር ነድዶ
ተጨልጦና ተገርኝቶ በጠፋው ሕዝብ መካከል በእድሜያቸው ለጋ
የነበሩ ሦስቱን ወጣቶች ለምሥክርነት አገኘ ፡፡ ሦስቱ ወጣቶች
እንደተቀረው ሕዝብ ንጉሥ ንጉስ ላቆመው ምስል ሰግደው
ለምን ? ሲባሉ
እምነት በልብ ነው አስመሰልን እንጂ አልሰገድንም
ያለነው በባዕድ ሀገር ያውም በምርኮ ነው በባዕድ ሀገር ያለ
ሰው ደግሞ ቢጭኑት አህያ ቢለጉሙት ፈረስ ነው ስለዚህ
ብንሰግድ ምንም ማለት አይደለም
የሰገድነው ወጣትነታችን አታልሎን አፍላነታችን ገፍትሮን ነው
እንኳን እኛ ሮጠን በልተን ያልጠገብነው ጎልማሶቹ ሽማግሎቹ
አዛውንቱ ሰግደው የለምን ?
ኋላ ንስሐ እንገባለን
ይገድሉናል ብለን ፈርተን ነው የሚሉና ሌሎች ብዙ ሰንካላ
ምክንያቶችን ማቅረብ ይችሉ ነበር፡፡
እነርሱ ግን ለስህተትና ለጥፋት ምክንያት አበጅተው ፈጣሪያቸውን
ክደው ለጣዖት አልሰገዱም ፡፡ በዚህም ታላቅ እምነታቸውና
ተጋድሏቸው ቅዱስ መጽሐፍ ለዘላለም ሲያወሳቸው እውነተኛ
ክርስቲያኖችም ሲመሰክሩላቸው ይኖራሉ ፡፡
+++ የሦስቱ ወጣቶች ታላቅ እምነት +++
በዚህ ዘመን ያለን ሰዎች እግዚአብሔርን የምናመልከው
የምናገለግለው አስከሞላልን እስከተሳካልን እስከጠገብንና
እስከተመቸን ብቻ እንጂ ከጎደለብን ካጣን ከተቸገርን እርሱን
ለማምለክና ለማገልገል ፈቃደኞች አይደለንም ፡፡ እነዚህ ወጣቶች
በንጉሡና ባነደደው እሳት ፊት ቆመው "ንጉሥ ሆይ አምላካችን
ከሚነደው እሳት ሊያድነን ይቻላል ባያድነን እንኳ አንተ ላቆምከው
ምስል አንሰግድም " ዳን 3÷17-18 በማለት ሲሞላልን ብቻ
ሳይሆን ሲጎድልብንም ፤ ስናገኝ ብቻ ሳይሆን ስናጣም ፤ ጤና
ስንሆን ብቻ ሳይሆን ጤናችን ሲናጋና ስንታመምም ፤ ሲሰጠን ብቻ
ሳይሆን ሲነሣንም ፤ እርሱን በእውነት በሙሉ ልብና በመንፈሳዊ
ደስታ ማምለክ ማመስገን እንደሚገባ አስተማሩን ፡፡ ኢዮባዊ
እምነት ይህ ነውና ፡፡
+++ እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ +++
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጦር ሳይሰብቁ ዝናር ሳይታጠቁ በጦር
አንደበት በፈረስ አንገት ሳይዘምቱ ንጉሥ ናቡከደነጾርንና መኳንንቱን
እግዚአብሔርን ይዘው ድል የነሱ እነዚህን ወጣቶች "እነርሱ
በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ" ዕብ 11÷33 ብሎ
ይመሠክርላቸዋል ፡፡ በዚህም "ዓለምን የሚያሸንፈው እምነታችን
ነው" 1ኛ ዮሐ 5÷4 የሚለውን ቃል አማናዊነት አረጋገጡልን ፡፡
ቤተክርስቲያንም የሐዋርያውን ቃል ቃል አድርጋ ይህን
እምነታቸውንና ተጋድሏቸውን ለዓለም ሁሉ ትመሠክራለች
ቤተክርስቲያን (ምእመናን) በፈተናና በመከራ ያለች ተጋዳይ
(millitant) እንዲሁም ድል አድራጊ መሆኗንም ከእነርሱ
ተጋድሎና ድል አድራጊነት ተምረናልና ፡፡ ዛሬ የመጠጥ ሱስ ߹
የወሬ ሱስ ߹ ሰውና ሰው የማጋጨት ሱስ ሰውነታችንን ድንኳን
ልቡናችንን ዙፋን አድርጎ መንግሥት የሆነብን እንዲሁም የዚህ
ዓለም (ፈጣሪውን የካደ ዓለም) ገዥ የተባለ ዲያብሎስ ከእምነት
ሊያስወጣን ስፍራችንን ሊያስለቅቀን በመጨረሻም እንደ
መንግሥት በራሳችን ላይ ነግሦ ወደ ወረደበት ጥልቅ ሊያወርደን
የሚታገለን ሰዎች ካለን በእምነት ሁሉን ማሸነፍ እንደሚቻል ሦስቱ
ወጣቶች የተግባር መምህራን ይሆኑናል ፡፡
+++ የእሳትን ኃይል አጠፉ +++
ሠለስቱ ደቂቅ ለጣዖት ባለመስገዳቸው ወደ እቶን እሳት
እንዲወረወሩ ተፈረደባቸው ተወረወሩም ፡፡ ያመኑት የታመኑበት
ፈጣሪያቸው መልአኩን ልኮ የእሳቱን ኃይል አጠፋላቸው ፡፡ የእነርሱ
ሰናፊላቸውን እንኳ ሳይለበልብ እነርሱን የጣሉ በእሳቱ ወላፈን
ነድደው ሞቱ ፡፡ ይህን የሚንበለበል እሳት እግዚአብሔር መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤል ያጠፋው በእነዚህ ወጣቶች እምነት ምክንያት
እንደሆነ ሐዋርያው ሲመሰክር "በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ"
ዕብ 11÷ 34 ብሏል :: ክፉዎች ባቀጣጠሉት እሳት ሲነድዱ
በወላፈኑም ሲለበለቡ ደጋጎቹ ግን በእምነት የዘረኝነትን የዕብሪትን
የዝሙትን የጥንቆላን የመተትንና ሌሎች እንደ እሳት የሚፈትኑ
ነገሮችን ሊያጠፉ እንደሚችሉ ሐዋርያት አስተምረውናል 1ጴጥ
4÷12 ፡፡
+++ እሳት የእሳትን ኃይል አጠፋ +++
ቅዱሳን መላእክት እሳታውያን ናቸው ዕብ 1÷7 ፡፡ እሳታውያን
በመሆናቸውም አንድ መልአክ ሲገለጥ ከክብሩ የተነሳ ምድር
እንኳን ይበራል "ሌላም ብርቱ መልአክ ደመና ተጎናጽፎ ከሰማይ
ሲወርድ አየሁ ፊቱም እንደ ፀሐይ እግሮቹም እንደ እሳት አምዶች
ነበሩ " ራእይ 10÷1 "ከዚያ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ
መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች"
ራእይ 18÷1 ተብሎ እንደተጻፈ ፡፡ ሊቀ መላእክት መጋቤ ሐዲስ
አብሣሬ ትስብዕት የሆነ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ እሳታውያን
ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነውና ወደ እቶን እሳት ከተወረወሩት
ሦስቱ ወጣቶች ጋር አራተኛ ሆኖ በመግባት እሳቱ እየነደደ
የእሳቱን ኃይል አጠፋ እሳቱ እየነደደ የማቃጠል ኃይሉን አበረደው
፡፡ ይህ እንዴት ያለ ተአምር ነው ? እንግዲህ ምን እንላለን ?
በዚህ ዘመን እንደ እሳት እየነደደ ከሚፈትነን ነገር ሁሉ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ያድነን የጌታ መልአክ
በሚፈሩት ዙርያ ይሰፍራል ያድናቸውማልና መዝ 33÷7 ፡፡
የሠለስቱ ደቂቅ በረከታቸው እምነታቸው ይደርብን መልአኩም
ጥበቃ አይለየን !!
በመምህር ቢትወደድ ወርቁ
👉 @Embtee
👉 @Embtee
👉 @Embtee
3÷1-30!! ++
እግዚአብሔርን የካደ በጉልበቱ የተመካ ሥልጣንን ክብርን
ባዕለጠግነትን መፈራትን የሰጠውን ፈጣሪውን የዘነጋ ሰው ንጉሥ
ናቡከደነጾር በባቢሎን ምድር በዱራ ሜዳ ላይ ቁመቱ ስድሳ ክንድ
ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነ የወርቅ ምስል አቁሞ ሕዝቡ በሙሉ
ለእርሱና ለጣዖት ይሰግዱ ዘንድ አዋጅን አወጀ ፡፡ ሕዝቡም
አዋጁን ተከትለው ንጉሥ ላቆመው ጣዖት እንደ ግንድ እየተረበረቡ
እንደ ሻሽ እየተነጠፉ ይሰግዱ ጀመር ፡፡ እግዚአብሔር ሀገርን
ዘመንን ያለ ደጋግ ሰዎች አይተውምና ስቶ በጣዖት ፍቅር ነድዶ
ተጨልጦና ተገርኝቶ በጠፋው ሕዝብ መካከል በእድሜያቸው ለጋ
የነበሩ ሦስቱን ወጣቶች ለምሥክርነት አገኘ ፡፡ ሦስቱ ወጣቶች
እንደተቀረው ሕዝብ ንጉሥ ንጉስ ላቆመው ምስል ሰግደው
ለምን ? ሲባሉ
እምነት በልብ ነው አስመሰልን እንጂ አልሰገድንም
ያለነው በባዕድ ሀገር ያውም በምርኮ ነው በባዕድ ሀገር ያለ
ሰው ደግሞ ቢጭኑት አህያ ቢለጉሙት ፈረስ ነው ስለዚህ
ብንሰግድ ምንም ማለት አይደለም
የሰገድነው ወጣትነታችን አታልሎን አፍላነታችን ገፍትሮን ነው
እንኳን እኛ ሮጠን በልተን ያልጠገብነው ጎልማሶቹ ሽማግሎቹ
አዛውንቱ ሰግደው የለምን ?
ኋላ ንስሐ እንገባለን
ይገድሉናል ብለን ፈርተን ነው የሚሉና ሌሎች ብዙ ሰንካላ
ምክንያቶችን ማቅረብ ይችሉ ነበር፡፡
እነርሱ ግን ለስህተትና ለጥፋት ምክንያት አበጅተው ፈጣሪያቸውን
ክደው ለጣዖት አልሰገዱም ፡፡ በዚህም ታላቅ እምነታቸውና
ተጋድሏቸው ቅዱስ መጽሐፍ ለዘላለም ሲያወሳቸው እውነተኛ
ክርስቲያኖችም ሲመሰክሩላቸው ይኖራሉ ፡፡
+++ የሦስቱ ወጣቶች ታላቅ እምነት +++
በዚህ ዘመን ያለን ሰዎች እግዚአብሔርን የምናመልከው
የምናገለግለው አስከሞላልን እስከተሳካልን እስከጠገብንና
እስከተመቸን ብቻ እንጂ ከጎደለብን ካጣን ከተቸገርን እርሱን
ለማምለክና ለማገልገል ፈቃደኞች አይደለንም ፡፡ እነዚህ ወጣቶች
በንጉሡና ባነደደው እሳት ፊት ቆመው "ንጉሥ ሆይ አምላካችን
ከሚነደው እሳት ሊያድነን ይቻላል ባያድነን እንኳ አንተ ላቆምከው
ምስል አንሰግድም " ዳን 3÷17-18 በማለት ሲሞላልን ብቻ
ሳይሆን ሲጎድልብንም ፤ ስናገኝ ብቻ ሳይሆን ስናጣም ፤ ጤና
ስንሆን ብቻ ሳይሆን ጤናችን ሲናጋና ስንታመምም ፤ ሲሰጠን ብቻ
ሳይሆን ሲነሣንም ፤ እርሱን በእውነት በሙሉ ልብና በመንፈሳዊ
ደስታ ማምለክ ማመስገን እንደሚገባ አስተማሩን ፡፡ ኢዮባዊ
እምነት ይህ ነውና ፡፡
+++ እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ +++
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጦር ሳይሰብቁ ዝናር ሳይታጠቁ በጦር
አንደበት በፈረስ አንገት ሳይዘምቱ ንጉሥ ናቡከደነጾርንና መኳንንቱን
እግዚአብሔርን ይዘው ድል የነሱ እነዚህን ወጣቶች "እነርሱ
በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ" ዕብ 11÷33 ብሎ
ይመሠክርላቸዋል ፡፡ በዚህም "ዓለምን የሚያሸንፈው እምነታችን
ነው" 1ኛ ዮሐ 5÷4 የሚለውን ቃል አማናዊነት አረጋገጡልን ፡፡
ቤተክርስቲያንም የሐዋርያውን ቃል ቃል አድርጋ ይህን
እምነታቸውንና ተጋድሏቸውን ለዓለም ሁሉ ትመሠክራለች
ቤተክርስቲያን (ምእመናን) በፈተናና በመከራ ያለች ተጋዳይ
(millitant) እንዲሁም ድል አድራጊ መሆኗንም ከእነርሱ
ተጋድሎና ድል አድራጊነት ተምረናልና ፡፡ ዛሬ የመጠጥ ሱስ ߹
የወሬ ሱስ ߹ ሰውና ሰው የማጋጨት ሱስ ሰውነታችንን ድንኳን
ልቡናችንን ዙፋን አድርጎ መንግሥት የሆነብን እንዲሁም የዚህ
ዓለም (ፈጣሪውን የካደ ዓለም) ገዥ የተባለ ዲያብሎስ ከእምነት
ሊያስወጣን ስፍራችንን ሊያስለቅቀን በመጨረሻም እንደ
መንግሥት በራሳችን ላይ ነግሦ ወደ ወረደበት ጥልቅ ሊያወርደን
የሚታገለን ሰዎች ካለን በእምነት ሁሉን ማሸነፍ እንደሚቻል ሦስቱ
ወጣቶች የተግባር መምህራን ይሆኑናል ፡፡
+++ የእሳትን ኃይል አጠፉ +++
ሠለስቱ ደቂቅ ለጣዖት ባለመስገዳቸው ወደ እቶን እሳት
እንዲወረወሩ ተፈረደባቸው ተወረወሩም ፡፡ ያመኑት የታመኑበት
ፈጣሪያቸው መልአኩን ልኮ የእሳቱን ኃይል አጠፋላቸው ፡፡ የእነርሱ
ሰናፊላቸውን እንኳ ሳይለበልብ እነርሱን የጣሉ በእሳቱ ወላፈን
ነድደው ሞቱ ፡፡ ይህን የሚንበለበል እሳት እግዚአብሔር መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤል ያጠፋው በእነዚህ ወጣቶች እምነት ምክንያት
እንደሆነ ሐዋርያው ሲመሰክር "በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ"
ዕብ 11÷ 34 ብሏል :: ክፉዎች ባቀጣጠሉት እሳት ሲነድዱ
በወላፈኑም ሲለበለቡ ደጋጎቹ ግን በእምነት የዘረኝነትን የዕብሪትን
የዝሙትን የጥንቆላን የመተትንና ሌሎች እንደ እሳት የሚፈትኑ
ነገሮችን ሊያጠፉ እንደሚችሉ ሐዋርያት አስተምረውናል 1ጴጥ
4÷12 ፡፡
+++ እሳት የእሳትን ኃይል አጠፋ +++
ቅዱሳን መላእክት እሳታውያን ናቸው ዕብ 1÷7 ፡፡ እሳታውያን
በመሆናቸውም አንድ መልአክ ሲገለጥ ከክብሩ የተነሳ ምድር
እንኳን ይበራል "ሌላም ብርቱ መልአክ ደመና ተጎናጽፎ ከሰማይ
ሲወርድ አየሁ ፊቱም እንደ ፀሐይ እግሮቹም እንደ እሳት አምዶች
ነበሩ " ራእይ 10÷1 "ከዚያ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ
መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች"
ራእይ 18÷1 ተብሎ እንደተጻፈ ፡፡ ሊቀ መላእክት መጋቤ ሐዲስ
አብሣሬ ትስብዕት የሆነ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ እሳታውያን
ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነውና ወደ እቶን እሳት ከተወረወሩት
ሦስቱ ወጣቶች ጋር አራተኛ ሆኖ በመግባት እሳቱ እየነደደ
የእሳቱን ኃይል አጠፋ እሳቱ እየነደደ የማቃጠል ኃይሉን አበረደው
፡፡ ይህ እንዴት ያለ ተአምር ነው ? እንግዲህ ምን እንላለን ?
በዚህ ዘመን እንደ እሳት እየነደደ ከሚፈትነን ነገር ሁሉ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ያድነን የጌታ መልአክ
በሚፈሩት ዙርያ ይሰፍራል ያድናቸውማልና መዝ 33÷7 ፡፡
የሠለስቱ ደቂቅ በረከታቸው እምነታቸው ይደርብን መልአኩም
ጥበቃ አይለየን !!
በመምህር ቢትወደድ ወርቁ
👉 @Embtee
👉 @Embtee
👉 @Embtee
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሦ ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው::
እርሷ የባህርያችን መመኪያ ናትና በእርሷ በእናቱ አማላጅነት ጌታችን ይጠብቀንና ያድነን ዘንድ መታሰቢያዋን እያደረግን ወደርሷ እንለምን ዘንድ ይገባናል::
ዛሬ ዕለት ሰንበት ነው የእመቤታችንም በዓሏ ነው በቃል ኪዳኗ የሚገኘውን በረከት ለማፈስ በዚህ ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ በረከቷን ማፈስ ነው። ለነፍሳችን ስንቅ የሚሆኑትን መልካም ነገር ለመስራት መፋጠንም መባረክ ነው። አዲስም በፀሎታችሁ አስቡት።
የሰንበት ዛቲ
ቤተ ክርስቲያን ስለ እመቤታችን አማላጅነት የምትሰብከው የምታስተምረው ፍጹም በሆነ ሐዋርያዊ ትውፊት ነው::
እመቤታችን ድንግል ማርያም ከሰው ወገን የሰው ችግር ቶሎ የሚገባት ቶሎ የሚታያትና የሚሰማት ርህርህት ናት::
ለምሳሌ በዮሐንስ ወንጌል ያለውን ምንባብ ብንመለከት ሠርግ ደግሰው ተጋባዥ ጠርተው ተጋባዥ ሕዝብ በመጋበዝ ላይ እንዳለ ድጎሳቸው በመቋረጡ ደጋሾቹ አፈሩ::
የሰዎቹ ችግር ቶሎ ገብቷት ለልጅዋ ነገረችው ከዚህም አስከትላ ልጄ ያዘዛችሁን ሁሉ አድርጉ ብላ አሳላፊ ለነበሩ ሰዎች ምክር ሰጠቻቸው ልጅዋም የእናቱን አማላጅነት ተቀብሎ አሳላፊዎችን ውኃ እንዲቀዱ አዘዛቸው።
አሳላፊዎቹም የእመቤታችን ምክር ሰምተው የጌታቸውን ትእዛዝ ስለፈጸሙ የሠርጉ ቤት ከፍርሃት ድኗል::
ይህ አስደናቂ ነገር ሊደረግ የቻለው በእመቤታችን አማላጅነት መሆኑን ቤተ ክርስቲያን ታምናለች::
ምእመናን ከዚህ ሕይወት ሲለዩ በዚህም በሚያልፈው የሕይወታቸው ጉዞ ለሚደርስባቸው ችግር ሁሉ እመቤታችን በአማላጅነት እንደማትለያቸው የታመነ ነው::
በዮሐንስ ወንጌል እንሆ ልጅሽ እንሆ እናትህ ብሎ አደራ በሚሰጥ ሰው ቋንቋ ጌታ የተናገረው ቃል እናቱ ድንግል ማርያም ከእርሱ በቀር ሌላ ልጅ እንዳልነበራት ከማሳየቱም በላይ ምሥጢራዊ አደራው እናቱን ለቤተ ክርስቲያን የተሰጣትን አደራ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ጠብቃ በእመቤታችን ስም እየተማፀነች ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ታካሂዳለች::
እመቤታችንም በተሰጣት አደራ የቤተ ክርስቲያን ጉዞ የተሳካ እንዲሆን ልጅዋን በየጊዜው ትለምነዋለች ታስታውሰዋለች::
እርሷን ለሕይወታችን መድኃኒትን አድርጎ ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን::
መልካም ዕለት ሰንበት ።
┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
┗━━° •❈• ° ━━┛
👆👂👂👈
እርሷ የባህርያችን መመኪያ ናትና በእርሷ በእናቱ አማላጅነት ጌታችን ይጠብቀንና ያድነን ዘንድ መታሰቢያዋን እያደረግን ወደርሷ እንለምን ዘንድ ይገባናል::
ዛሬ ዕለት ሰንበት ነው የእመቤታችንም በዓሏ ነው በቃል ኪዳኗ የሚገኘውን በረከት ለማፈስ በዚህ ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ በረከቷን ማፈስ ነው። ለነፍሳችን ስንቅ የሚሆኑትን መልካም ነገር ለመስራት መፋጠንም መባረክ ነው። አዲስም በፀሎታችሁ አስቡት።
የሰንበት ዛቲ
ቤተ ክርስቲያን ስለ እመቤታችን አማላጅነት የምትሰብከው የምታስተምረው ፍጹም በሆነ ሐዋርያዊ ትውፊት ነው::
እመቤታችን ድንግል ማርያም ከሰው ወገን የሰው ችግር ቶሎ የሚገባት ቶሎ የሚታያትና የሚሰማት ርህርህት ናት::
ለምሳሌ በዮሐንስ ወንጌል ያለውን ምንባብ ብንመለከት ሠርግ ደግሰው ተጋባዥ ጠርተው ተጋባዥ ሕዝብ በመጋበዝ ላይ እንዳለ ድጎሳቸው በመቋረጡ ደጋሾቹ አፈሩ::
የሰዎቹ ችግር ቶሎ ገብቷት ለልጅዋ ነገረችው ከዚህም አስከትላ ልጄ ያዘዛችሁን ሁሉ አድርጉ ብላ አሳላፊ ለነበሩ ሰዎች ምክር ሰጠቻቸው ልጅዋም የእናቱን አማላጅነት ተቀብሎ አሳላፊዎችን ውኃ እንዲቀዱ አዘዛቸው።
አሳላፊዎቹም የእመቤታችን ምክር ሰምተው የጌታቸውን ትእዛዝ ስለፈጸሙ የሠርጉ ቤት ከፍርሃት ድኗል::
ይህ አስደናቂ ነገር ሊደረግ የቻለው በእመቤታችን አማላጅነት መሆኑን ቤተ ክርስቲያን ታምናለች::
ምእመናን ከዚህ ሕይወት ሲለዩ በዚህም በሚያልፈው የሕይወታቸው ጉዞ ለሚደርስባቸው ችግር ሁሉ እመቤታችን በአማላጅነት እንደማትለያቸው የታመነ ነው::
በዮሐንስ ወንጌል እንሆ ልጅሽ እንሆ እናትህ ብሎ አደራ በሚሰጥ ሰው ቋንቋ ጌታ የተናገረው ቃል እናቱ ድንግል ማርያም ከእርሱ በቀር ሌላ ልጅ እንዳልነበራት ከማሳየቱም በላይ ምሥጢራዊ አደራው እናቱን ለቤተ ክርስቲያን የተሰጣትን አደራ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ጠብቃ በእመቤታችን ስም እየተማፀነች ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ታካሂዳለች::
እመቤታችንም በተሰጣት አደራ የቤተ ክርስቲያን ጉዞ የተሳካ እንዲሆን ልጅዋን በየጊዜው ትለምነዋለች ታስታውሰዋለች::
እርሷን ለሕይወታችን መድኃኒትን አድርጎ ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን::
መልካም ዕለት ሰንበት ።
┏━━° •❈• ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
┗━━° •❈• ° ━━┛
👆👂👂👈
#እስከ_መቼ_ነው?
እውነት ቅዱስ ጊዮርጊስን የምንወደው ከሆነ ድምፃችንን እናሰማ እንቃወም፡፡ እስከ መቼ ነው በቅዱሱ አባታችን ስም የሚነገደው? መቼ ነው ታዲያ ስዕሉ የሚከበረው መቼ መቼ? እስከ መቼ ነው ጭፈራ ቤት እና የአህዛብ መቀለጃ ሚያደርጉት፡፡ የቅዱሱ አባታችን ምስል እና ስም ማስነሳት ያቃተን ለምንድነው? ወይስ አንወደውም? ለምን ዝም አልን? መቼስ አያገባኝም አንልም ስለ ዶክተር አብይ እንኳን ስንቱ ነው #ዋ ማንም እንዳይነካዉ እያለ Post የሚያደርገው፡፡ እስቲ ማናችን ነን ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበቃ የቆምነዉ? እስቲ ማናችን ነን የተከራከርነው? መልሱን እናውቀዋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ጊዜው አልረፈደም ሁላችንም FB ላይ post አናድርግ ለሚመለከተው አካል እናድርስ በእርግጥ እኛን ነው የሚመለከተው ነገር ግን መፍትሄ የሚሰጠን አካል ያስፈልገናል። ቅዱስ ስሙ እና ምስሉ ይነሳ ብለን ድምፃችንን እናሰማ መቼም በአባታችን በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ሲነገድ ማየት እሚያስደስተው የለም።
ይህን ያነበበ፣ያየ በሙሉ በተለያዩ ድህረ-ገፅ ላይ POST AND SHARE አድርጉ አደራችሁን።
👉 @embtee
@embtee
እውነት ቅዱስ ጊዮርጊስን የምንወደው ከሆነ ድምፃችንን እናሰማ እንቃወም፡፡ እስከ መቼ ነው በቅዱሱ አባታችን ስም የሚነገደው? መቼ ነው ታዲያ ስዕሉ የሚከበረው መቼ መቼ? እስከ መቼ ነው ጭፈራ ቤት እና የአህዛብ መቀለጃ ሚያደርጉት፡፡ የቅዱሱ አባታችን ምስል እና ስም ማስነሳት ያቃተን ለምንድነው? ወይስ አንወደውም? ለምን ዝም አልን? መቼስ አያገባኝም አንልም ስለ ዶክተር አብይ እንኳን ስንቱ ነው #ዋ ማንም እንዳይነካዉ እያለ Post የሚያደርገው፡፡ እስቲ ማናችን ነን ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበቃ የቆምነዉ? እስቲ ማናችን ነን የተከራከርነው? መልሱን እናውቀዋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ጊዜው አልረፈደም ሁላችንም FB ላይ post አናድርግ ለሚመለከተው አካል እናድርስ በእርግጥ እኛን ነው የሚመለከተው ነገር ግን መፍትሄ የሚሰጠን አካል ያስፈልገናል። ቅዱስ ስሙ እና ምስሉ ይነሳ ብለን ድምፃችንን እናሰማ መቼም በአባታችን በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ሲነገድ ማየት እሚያስደስተው የለም።
ይህን ያነበበ፣ያየ በሙሉ በተለያዩ ድህረ-ገፅ ላይ POST AND SHARE አድርጉ አደራችሁን።
👉 @embtee
@embtee
ከጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ያገኘነው ምንድን ነው?
ዳግም ልደት
በአዳም በደል ምክንያት አጥተነው የነበረው ልጅነታችንን ክርስቶስ በልደቱ ዳግመኛ እንደመለሰልን ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው።” ዮሐ 1፥12 በማለት ገልጾታል።
ሰላም
በጌታችን ልደት ለዓለም ሁሉ የሚሆን ዘላለማዊ ሰላም ተገኝቷል። ይህም “ክብር እግዚአብሔር በሰማያት ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጐ ፈቃድ” እያሉ ቅዱሳን መላእክት በመዘመራቸው ተረጋግጧል። ሉቃ 2፥14። ስለዚህ በክርስቶስ ያገኘነው እውነተኛ ሰላም በእኛ ጸንቶ እንዲኖር ዘወትር በጾምና በጸሎት እየተጋን ስለሰላም የምንማፀን ሆነን ልንገኝ ይገባል። ሰላም የክርስትና መታወቂያ አርማ ነውና።
ብርሃን
“በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃንን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።” ኢሳ 9፥2። ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ያህል በዲያብሎስ ቁራኝነት ተይዞ የነበረው አዳም ወደሚደነቀው ብርሃን የተሸጋገረው በክርስቶስ ልደት ነው። እኛም በልደቱ ያገኘነውን የጽድቅ ብርሃን ጠብቀን ለመኖር (ብርሃነ ወንጌልን) ፈጽመን ከኃጢአት ርቀን በጽድቅ ሥራ ተወስነን ብርሃን ሆነን ልንኖር ይገባል።
ነጻነት
“በነጻነት እንኖር ዘንድ ክርስቶስ ነጻ አወጣን። ከእንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደገና በባርነት ቀንበር አትያዙ”። ገላ 5፥1። የሰው ልጅ እግዚአብሔርን በነጻነት እያመሰገነ ይኖር ዘንድ ተፈጥሯልና። ኃጢአት በመሥራት የዲያብሎስ ባርያ ሳንሆን በተሰጠን ነጻነት በመጠቀም የጽድቅ አገልጋዮች ሆነን ልንመላለስ ይገባል።
ይቅርታ
በአዳም በደል ምክንያት ከአብራኩ የተከፈሉ በሙሉ በደለኛ ሆነው የነበሩበትን ዘመን ለውጦ አዳምንና የልጅ ልጆቹን በደል ደምስሶ ፍቅርን ይመሰርት ዘንድ ጌታ ተወለደ። በምድርና በሰማይ ላሉት ፍቅርን መሠረተ። እርሱ የሰው ልጆችን በደል ሳይቆጥር ሁሉን ይቅር እንዳለ ክርስቲያንም የበደሉትን ሁሉ ይቅር ይል ዘንድ የፈጣሪው ትዕዛዝ ነውና ዘወትር ሊፈጽማት የምትገባ ከእግዚአብሔር ጸጋ የምታስደምር የልደቱን ብርሃን ለማየት እንደበቁ በዚህም ደስ እንደተሰኙ እንደ ቅዱሳን መላእክት ለእውነተኛ ምስጋና የምታደርስ የጽድቅ መሠረት የበረከት በር ናት። ማቴ 18፥21-23፣ ማቴ 5፥23-25። መባህን ትተህ ሂድ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ የሚለው አምላካዊ ቃል ይቅርታ የክርስትና ሕይወት መመሪያ መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልንፈጽማት ይገባል።
ፍቅር
ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተናገረው እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጅን በደል ሳይቆጥር በዙፋኑ ሆኖ ምሬሃለሁ ማለት ሲችል ፍቅሩን ይገለጽ ዘንድ በከብቶች በረት ተወለደ። እውነተኛ ፍቅሩ ለክርስትናችን መሠረት ለጽድቃችን ፋና እንደሆነ መጻሕፍት ያረጋግጣሉ።
እንግዲህ በልደቱ ያገኘነውን ሰላም፣ ነጻነት፣ ይቅርታ፣ ብርሃንና ፍቅር ዋጋ የተከፈለበት ጸጋ የወረስንበት በመሆኑ ዘወትር በድንቅ ፍቅሩ የሚታደገን አምላካችን እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ እስከ መጨረሻው ድረስ ጸንተን እንድንኖር ክብራችንንና ጸጋችንን አስተውለን ከኃጢአት ርቀን በንሰሐ ታጥበን እራሳችንን ለክርስቶስ የተወደደ መስዋዕት አድርገን እንድናቀርብ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት አይለየን።
አሜን።
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
@embtee
@embtee
ዳግም ልደት
በአዳም በደል ምክንያት አጥተነው የነበረው ልጅነታችንን ክርስቶስ በልደቱ ዳግመኛ እንደመለሰልን ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው።” ዮሐ 1፥12 በማለት ገልጾታል።
ሰላም
በጌታችን ልደት ለዓለም ሁሉ የሚሆን ዘላለማዊ ሰላም ተገኝቷል። ይህም “ክብር እግዚአብሔር በሰማያት ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጐ ፈቃድ” እያሉ ቅዱሳን መላእክት በመዘመራቸው ተረጋግጧል። ሉቃ 2፥14። ስለዚህ በክርስቶስ ያገኘነው እውነተኛ ሰላም በእኛ ጸንቶ እንዲኖር ዘወትር በጾምና በጸሎት እየተጋን ስለሰላም የምንማፀን ሆነን ልንገኝ ይገባል። ሰላም የክርስትና መታወቂያ አርማ ነውና።
ብርሃን
“በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃንን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።” ኢሳ 9፥2። ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ያህል በዲያብሎስ ቁራኝነት ተይዞ የነበረው አዳም ወደሚደነቀው ብርሃን የተሸጋገረው በክርስቶስ ልደት ነው። እኛም በልደቱ ያገኘነውን የጽድቅ ብርሃን ጠብቀን ለመኖር (ብርሃነ ወንጌልን) ፈጽመን ከኃጢአት ርቀን በጽድቅ ሥራ ተወስነን ብርሃን ሆነን ልንኖር ይገባል።
ነጻነት
“በነጻነት እንኖር ዘንድ ክርስቶስ ነጻ አወጣን። ከእንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደገና በባርነት ቀንበር አትያዙ”። ገላ 5፥1። የሰው ልጅ እግዚአብሔርን በነጻነት እያመሰገነ ይኖር ዘንድ ተፈጥሯልና። ኃጢአት በመሥራት የዲያብሎስ ባርያ ሳንሆን በተሰጠን ነጻነት በመጠቀም የጽድቅ አገልጋዮች ሆነን ልንመላለስ ይገባል።
ይቅርታ
በአዳም በደል ምክንያት ከአብራኩ የተከፈሉ በሙሉ በደለኛ ሆነው የነበሩበትን ዘመን ለውጦ አዳምንና የልጅ ልጆቹን በደል ደምስሶ ፍቅርን ይመሰርት ዘንድ ጌታ ተወለደ። በምድርና በሰማይ ላሉት ፍቅርን መሠረተ። እርሱ የሰው ልጆችን በደል ሳይቆጥር ሁሉን ይቅር እንዳለ ክርስቲያንም የበደሉትን ሁሉ ይቅር ይል ዘንድ የፈጣሪው ትዕዛዝ ነውና ዘወትር ሊፈጽማት የምትገባ ከእግዚአብሔር ጸጋ የምታስደምር የልደቱን ብርሃን ለማየት እንደበቁ በዚህም ደስ እንደተሰኙ እንደ ቅዱሳን መላእክት ለእውነተኛ ምስጋና የምታደርስ የጽድቅ መሠረት የበረከት በር ናት። ማቴ 18፥21-23፣ ማቴ 5፥23-25። መባህን ትተህ ሂድ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ የሚለው አምላካዊ ቃል ይቅርታ የክርስትና ሕይወት መመሪያ መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልንፈጽማት ይገባል።
ፍቅር
ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተናገረው እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጅን በደል ሳይቆጥር በዙፋኑ ሆኖ ምሬሃለሁ ማለት ሲችል ፍቅሩን ይገለጽ ዘንድ በከብቶች በረት ተወለደ። እውነተኛ ፍቅሩ ለክርስትናችን መሠረት ለጽድቃችን ፋና እንደሆነ መጻሕፍት ያረጋግጣሉ።
እንግዲህ በልደቱ ያገኘነውን ሰላም፣ ነጻነት፣ ይቅርታ፣ ብርሃንና ፍቅር ዋጋ የተከፈለበት ጸጋ የወረስንበት በመሆኑ ዘወትር በድንቅ ፍቅሩ የሚታደገን አምላካችን እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ እስከ መጨረሻው ድረስ ጸንተን እንድንኖር ክብራችንንና ጸጋችንን አስተውለን ከኃጢአት ርቀን በንሰሐ ታጥበን እራሳችንን ለክርስቶስ የተወደደ መስዋዕት አድርገን እንድናቀርብ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት አይለየን።
አሜን።
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
🌺🌺🌺
@embtee
@embtee