ታሕሣሥ 27፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 5፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم
#የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስልምን ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ሙስሊም ማኀበረሰብ ላይ የሚፈጸመውን የእምነትና የሰብአዊ ጥሰት በፅናት በመቃወም ከትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጎን እንደሚሰለፍ መግለጫ አውጥቷል ።
የመግለጫው ሙሉ ቃል ከላይ ይመልከቱ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم
#የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስልምን ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ሙስሊም ማኀበረሰብ ላይ የሚፈጸመውን የእምነትና የሰብአዊ ጥሰት በፅናት በመቃወም ከትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጎን እንደሚሰለፍ መግለጫ አውጥቷል ።
የመግለጫው ሙሉ ቃል ከላይ ይመልከቱ
ታሕሣሥ 27፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 5፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ክቡር ፕሬዚደንቱ "ለሕዝበ ሙስሊሙ እና ለአገር የሚሠሩ ማኅበራት ሊበራከቱ ይገባል" አሉ።
• የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር መሥራች ጠቅላላ ጉባዔ አካሄደ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ ለሕዝበ ሙስሊሙ እና ከፍ ሲልም ለአገር የሚሠሩ ማኅበራት ሊበራከቱ ይገባል አሉ።
ክቡር ፕሬዚደንቱ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር ካለው 'የተቋማትና ማኅበራት አስተዳደር' ሕጋዊ ፈቃድ የወሰደው የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር በዛሬው ዕለት የምሥረታ ጠቅላላ ጉባዔውን በኤልያናሞል ያካሄደበትን መርኃግብር ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ነው።
በማኅበሩ የምሥረታ ጉባዔ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ አዲሱ አመራር ወደ ኃላፊነት የመጣው ሠርቶ ለማሠራት መኾኑን ጠቅሰው፣ "ከማኅበሩ ጋራ በመተባበር ለአገር እና ለማኅበረሰቡ ጠቀሜታ ባላቸው ጉዳዮች ላይ አብረን በመሥራት ትውልዳዊ ኃላፊነታችንን እንወጣለን" ብለዋል።
ክቡር ፕሬዚደንቱ አክለውም፣ "ሥራችን ኃላፊነት ያለበት፣ ከኩራት የራቀ እና የዑለማ ይሁንታ ያለው እንዲሆን አደራ!" ብለዋል።
የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር ምሁራዊ መሠረት ያለውና በተለያዩ ዘርፍ የሚገኙ ሙስሊም ባለሙያዎችን ያሰባሰበ ተቋም መሆኑ ከመድረኩ ተነግሯል።
ማኀበሩ ተጠናክሮ ማኅበረሰባዊ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ የሙስሊሙ ማኀበረሰብ ድጋፍ እንዳይለየው ጥሪ አቅርቧል።
በማኅበሩ የምሥረታ እና የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሸይኽ ሡልጣን አማን እና የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚደንት ዑስታዝ ሐይደር ከድር መልዕክት ያስተላለፉ ሲኾን፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሐጂ ከማል ሀሩን፣ የሥራ አመራር አባላት እና ዑስታዝ አህመዲን ጀበልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ምሁራን ታድመዋል።
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ክቡር ፕሬዚደንቱ "ለሕዝበ ሙስሊሙ እና ለአገር የሚሠሩ ማኅበራት ሊበራከቱ ይገባል" አሉ።
• የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር መሥራች ጠቅላላ ጉባዔ አካሄደ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ ለሕዝበ ሙስሊሙ እና ከፍ ሲልም ለአገር የሚሠሩ ማኅበራት ሊበራከቱ ይገባል አሉ።
ክቡር ፕሬዚደንቱ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር ካለው 'የተቋማትና ማኅበራት አስተዳደር' ሕጋዊ ፈቃድ የወሰደው የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር በዛሬው ዕለት የምሥረታ ጠቅላላ ጉባዔውን በኤልያናሞል ያካሄደበትን መርኃግብር ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ነው።
በማኅበሩ የምሥረታ ጉባዔ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ አዲሱ አመራር ወደ ኃላፊነት የመጣው ሠርቶ ለማሠራት መኾኑን ጠቅሰው፣ "ከማኅበሩ ጋራ በመተባበር ለአገር እና ለማኅበረሰቡ ጠቀሜታ ባላቸው ጉዳዮች ላይ አብረን በመሥራት ትውልዳዊ ኃላፊነታችንን እንወጣለን" ብለዋል።
ክቡር ፕሬዚደንቱ አክለውም፣ "ሥራችን ኃላፊነት ያለበት፣ ከኩራት የራቀ እና የዑለማ ይሁንታ ያለው እንዲሆን አደራ!" ብለዋል።
የሙስሊም ባለሙያዎች ማኅበር ምሁራዊ መሠረት ያለውና በተለያዩ ዘርፍ የሚገኙ ሙስሊም ባለሙያዎችን ያሰባሰበ ተቋም መሆኑ ከመድረኩ ተነግሯል።
ማኀበሩ ተጠናክሮ ማኅበረሰባዊ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ የሙስሊሙ ማኀበረሰብ ድጋፍ እንዳይለየው ጥሪ አቅርቧል።
በማኅበሩ የምሥረታ እና የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሸይኽ ሡልጣን አማን እና የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚደንት ዑስታዝ ሐይደር ከድር መልዕክት ያስተላለፉ ሲኾን፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሐጂ ከማል ሀሩን፣ የሥራ አመራር አባላት እና ዑስታዝ አህመዲን ጀበልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ምሁራን ታድመዋል።