መጋቢት ፬ /4/
በዚህችም ቀን የከበረና የተመሰገነ መኰንን ሐኑልዮስ ከጵንፍልያ አውራጃ ብርግያ በምትባል ከተማ በሰማዕትነት አረፈ።
ይህንንም ቅዱስ ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ መውደዱና እርሱንም ስለ ማምለኩ ከዲዮቅልጥያኖስ ተልኮ የመጣ ብርይንኮስ የተባለ መኰንን ያዘው።
በመኰንኑም ፊት በቆመ ጊዜ ምስጋና ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ከፍ ከፍ ባሉ ቃላት አብራርቶ ገለጠ። ብዙ ምስጋናዎችንም ለእግዚአብሔር አቀረበ የረከሱ ጣዖታትንም ረገማቸው።
መኰንኑም በዕንጨት መስቀል ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ስለ ከበረ ስሙም ምስክር ይሆን ዘንድ ስለ አደለው ምስጋና ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው። ከዚያም ምስጋና ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
@efeson_2
💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
❤1
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።"
(ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)
(ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)