ኤፌሶን~፩
650 subscribers
75 photos
1 video
23 links
Download Telegram
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን #በታላቁ_በቈስጠንጢኖስ_ዘመን ለነበረ ለከበረ አባት ለአንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በዓለም ለመላ ቁጥሩ #ከሠለስቱ_ምዕት ለሆነ #ለታላቁ_አባት_ለአባ_አንስጣስዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከቸሩ_መድኃኔዓለም_ከስቅለቱ መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
📣📣ዜና ዕረፍት

ለበርካታ ዓመታት ከገጠር እስከ ከተማ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገራት ቅዱሱን ሕያው ወንጌል በታማኝነትና በትጋት ያለዕረፍት ያገለገሉት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በትናንትናው ዕለት ከድካመ ሥጋ ዐረፉ።

ኦ እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ ገብርከ ወልደ ሰማዕት
ሀገረ ሕይወት መንግስተ ሰማያት ያውርስልን፤ በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ ዕቅፍ ያኑርልን፤
ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

📣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት

@efeson_2

📣📣📣📣📣📣
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ጻድቅ በአጤ (ዐፄ) #ሱሱንዮስ አንገቷን ተሰይፈ ሰማዕት ከሆነች በኋላ #ቅዱስ_ሚካኤል ገነትንና ሲኦልን አሳይቶ 14ቀን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ከተቀመጠች በኋላ እንደገና እንደተኛ ወይም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ከሞት ተነስታ ብዙ ገዳማትን (ታላቁን ገዳም ራማ ኪዳነ ምሕረትን) ላቀናች #ለታላቋ_ለጻድቅ_ወሰማዕት_ለቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ለዕረፍቷ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
1
መጋቢት ፫ /3/


በዚች ቀን በእስክንድርያ ለተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት ሃምሣ ስምንተኛ የሆነው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አባ ቆዝሞስ አረፈ።

ይህም አባት እውነተኛና ንጹሕ የዋህ ርኅራኄው የበዛ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍትና ትርጓሜያቸውን የሚያውቅ ነበር።

እግዚአብሔርም በወንጌላዊው ማርቆስ መንበር ላይ ለሊቀ ጵጵስና ሹመት መረጠው የግብጽ ንጉሥ መቅትር በነገሠ በአሥራ ስምንት ዓመት ሊቀጳጳሳት ሁኖ ተሾመ። ጴጥሮስ የሚባል ጳጳስን ለኢትዮጵያ አገር ሹሞ ነበር ። አባ ጴጥሮስም ወደ ኢትዮጵያ በደረሰ ጊዜ ጥቂት ዘመን በሰላም ኖረ።

በዚያም ሳለ ሰይጣን ያደረባቸው ከሶርያ የመጡ ሁለት መነኮሳት አባ ቆዝሞስ በሾመው በአባ ጴጥሮስ ላይ ሴራ ሰርው በእርሱ ፈንታ እነርሱ ተሾሙ። ከግዜም በኋላ በእግዚአብሔር ቸርነት ሴራቸው ታወቀ የኢትዮጲያ ንጉስም አባ ጴጥሮስን ያመጡት ዘንድ አዘዘ ነገር ግን ሙቶ አገኙት ይሕንንም አባ ቆዝሞስ ሲሰማ በጣም አዘነ። በዚህም ምክንያት ለሰማንያ አራት ዓመታት ያህል ለኢትዮጵያ ሰዎች ጳጳስ ተሹሞ አልተላከላቸውም።

አባ ቆዝሞስም እጅግ ሸመገለ የሹመቱም ዘመን ደኀንነትንና ሰላምን የተመላ ነበር። በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም አሥራ ሁለት ዓመት ኖረ በሰላምም አረፈ እግዚአብሔርበጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
መጋቢት ፬ /4/


በዚህችም ቀን የከበረና የተመሰገነ መኰንን ሐኑልዮስ ከጵንፍልያ አውራጃ ብርግያ በምትባል ከተማ በሰማዕትነት አረፈ።

ይህንንም ቅዱስ ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ መውደዱና እርሱንም ስለ ማምለኩ ከዲዮቅልጥያኖስ ተልኮ የመጣ ብርይንኮስ የተባለ መኰንን ያዘው።

በመኰንኑም ፊት በቆመ ጊዜ ምስጋና ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ከፍ ከፍ ባሉ ቃላት አብራርቶ ገለጠ። ብዙ ምስጋናዎችንም ለእግዚአብሔር አቀረበ የረከሱ ጣዖታትንም ረገማቸው።

መኰንኑም በዕንጨት መስቀል ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ስለ ከበረ ስሙም ምስክር ይሆን ዘንድ ስለ አደለው ምስጋና ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው። ከዚያም ምስጋና ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
1
በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ

የማቴዎስ ወንጌል ፲፮᎓፪
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።"

(ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)
1🥰1
"ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።" — ሉቃ 1:14
🥰2