ኤፌሶን~፩
650 subscribers
75 photos
1 video
23 links
Download Telegram
🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️

"ጸሎት በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ ማእበል ለሚያንገላታቸው መልሕቅ የድሃው ሐብት የባለጸጋው ደህንነት የታማሚው መዳኛ ወይም ጤና ማግኛ ነው ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል።"

                              🍁️ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው። አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደኅንነት በሚሰማህ አሳቻ ሰዓት ሳታውቀው ይዘርፈሀል፤ ይገድልህማል። "

                             🍁️ቅዱስ ጎርጎርዮስ

"ብርሃን ወደ አንድ ቤት ውስጥ ሲገባ ጨለማን እንደሚያስወግድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን መፍራት ወደ አንድ ሰው ልብ ሲገባም አለማወቅን (በኃጢአት የሚወድቅባትን) ያስወግዳል።"

                           🍁️አባ እንጦንስ

"ካህኑን እንደ መንፈሳዊ አባትነቱ እየው፤ ልክ በሽተኛ የተሸፈኑ ቁስሎችን ለሐኪም እንደሚያሳይና እንደሚፈውስ ምስጢሮችህን በግልጽ ንገረው”

                         🍁️ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ።


"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"

                          🍁️ ቅዱስ ባስልዮስ


"ጥላቻን በልቡ ውስጥ የሚሸሽግ ሰው እባብን በጭኑ ላይ የሚያስቀምጥን ሰውን ይመስላል።
ጭስ ንቦችን እንደሚያባርር ሁሉ ጥላቻም በልብ ውስጥ የተቀመጠን እውቀት ያጠፋል፡፡"

                        🍁️ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ


ሰው ሆይ! ጻድቅ መሆንን ትወዳለህን? አዎን ትለኝ እንደሆነ፥ እንግዲያውስ ለራስህ ንፉግ ለሌላው ግን ቸር ሁን፡፡

                     🍁️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


@efeson_2

🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን #ለኢትዮጵያውያን_ጻድቅ ውኃ ከዓለት ድንጋይ ላይ እያፈለቁ አሕዛብን ሁሉ እያስተማሩ ያጠምቁ ለነበረ፤ ኅብስትም ከሰማይ እየወረደላቸው ሕዝቡን ያቆርቡ ለነበረ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ክፍለ_ማርያም_ዘድባጋ ከዚህ ዓለም እንደነ #ቅዱሳን_ሄኖክና_ኤልያስ ከሞት ለተሰወሩበት በዓልና #ለአባ_ገብረ_መርዓዊ_ዘአግዶ_ገዳም ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
የካቲት ፳፩ /21/


በዚችም ዕለት የከበረ የሐዋርያው የጳውሎስ ደቀ መዝሙር የሆነ ቅዱስ አናሲሞስ በሰማዕትነት አረፈ።

ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ፊልሞና ለሚባል ለሮሜ ሰው አገልጋይ ነበር። ሰይጣን  የአናሲሞስን ልቡ ለወጠና የጌታውን ገንዘብ ሰርቆ  ወደ ሮሜ ሔደ።

በእግዚአብሔርም ፈቃድ ወደከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ሔደ ትምህርቱንም ሰምቶ በክብርባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ለቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙሩ ሆነ። ነገር ግን የጌታውን ገንዘብ በመስረቁ በአናሲሞስ ልብ ጽኑ ሀዘን አደረ ለሐዋርያ ጳውሎስም የሠራውን ሁሉ ነገረው ሐዋርያ ጳውሎስም አትፍራ ልብህም አይዘን አለው የቀድሞ ጌታው በሰላም እንዲቀበለው ወደ ፊልሞናም መልእክትን ጻፈለት ይቺም ስለ አናሲሞስ የጻፋት ከመልእክቶቹ አንዲቱ ናት።

ይህ የከበረ አናሲሞስም ወደ ፊልሞና ወደ ጌታው በደረሰ ጊዜ በማመኑና በመጸጸቱ ደስ አለው ሐዋርያው እንዳዘዘውም ተቀበለው። ከዚህም በኋላ ሸኙትና ወደ ሮሜ አገር ተመለሰ በሰማዕትነት እስከ ሚሞትበት ጊዜ ሐዋርያ ጳውሎስን የሚያገለግልው ሆነ።

ከሐዋርያው ጳውሎስም የምስክርነት ሞት በኋላ የንጉሥ ጭፍራ ይህን ቅዱስ ይዞ ወደ አንዲት ደሴት ሰደደው በዚያም ያሉትን አስተምሮ አጠመቃቸው። ያ ጭፍራም ይህን በሰማ ግዜ በብዙ አሰቃይቶት በዚች ቀን ምስክርነቱንም ፈጸመ። የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን ለከበሩ #በቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት ላመኑ #ለቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞ፣ ለድንግል #ቅድስት_ሉቅያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለከበረ #ሐዲስ_አባ_እንጦኒ ይህም ረውሕ ለሚባለው ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ ለሆነ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት ቆሞ ሳይቀመጥ ለጸለየ #ለአባ_አቡፋ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር #ከዲያቆን_ቶና ከአገረ ቊስ #ሚናስ_ከጋዛ_ይልማድዮስ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከደማይልናልና_ከርጊኖስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ  ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
የካቲት ፳፮ /26/


በዚች ዕለት ዖዝያ ይባል የነበረ ዕውነተኛ ነቢይ ሆሴዕ አረፈ። ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህም ዖዝያን፡ ኢዮአታም፡ አካዝ፡ ሕዝቅያስ ናቸው።

በትንቢቱም ድንቆች ሥራዎችን ተናገረ የእስራኤልንም ልጆች ገሠጻቸው የአመንዝራ ልጆች ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቍጣውን ከእርሳቸው እንደማይመልስ አስረዳቸው። እንዲህም አለ የእስራኤል ልጆች ቍጥራቸው እንደማይሠፈርና እንደማይቈጠር የባሕር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም አለ። ስለ አሕዛብም በእግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኛል።

ዳግመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በከበረ ደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሣኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ። እሱ በመከራ ገርፎ ያድነናል እርሱም በመከራ አቍስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው በሦስተኛውም ቀን ድነን በሱ ፊት እንነሣለን እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ሥልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነው ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን #በታላቁ_በቈስጠንጢኖስ_ዘመን ለነበረ ለከበረ አባት ለአንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በዓለም ለመላ ቁጥሩ #ከሠለስቱ_ምዕት ለሆነ #ለታላቁ_አባት_ለአባ_አንስጣስዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከቸሩ_መድኃኔዓለም_ከስቅለቱ መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
📣📣ዜና ዕረፍት

ለበርካታ ዓመታት ከገጠር እስከ ከተማ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገራት ቅዱሱን ሕያው ወንጌል በታማኝነትና በትጋት ያለዕረፍት ያገለገሉት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በትናንትናው ዕለት ከድካመ ሥጋ ዐረፉ።

ኦ እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ ገብርከ ወልደ ሰማዕት
ሀገረ ሕይወት መንግስተ ሰማያት ያውርስልን፤ በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ ዕቅፍ ያኑርልን፤
ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

📣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት

@efeson_2

📣📣📣📣📣📣
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ጻድቅ በአጤ (ዐፄ) #ሱሱንዮስ አንገቷን ተሰይፈ ሰማዕት ከሆነች በኋላ #ቅዱስ_ሚካኤል ገነትንና ሲኦልን አሳይቶ 14ቀን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ከተቀመጠች በኋላ እንደገና እንደተኛ ወይም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ከሞት ተነስታ ብዙ ገዳማትን (ታላቁን ገዳም ራማ ኪዳነ ምሕረትን) ላቀናች #ለታላቋ_ለጻድቅ_ወሰማዕት_ለቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ለዕረፍቷ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
1
መጋቢት ፫ /3/


በዚች ቀን በእስክንድርያ ለተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት ሃምሣ ስምንተኛ የሆነው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አባ ቆዝሞስ አረፈ።

ይህም አባት እውነተኛና ንጹሕ የዋህ ርኅራኄው የበዛ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍትና ትርጓሜያቸውን የሚያውቅ ነበር።

እግዚአብሔርም በወንጌላዊው ማርቆስ መንበር ላይ ለሊቀ ጵጵስና ሹመት መረጠው የግብጽ ንጉሥ መቅትር በነገሠ በአሥራ ስምንት ዓመት ሊቀጳጳሳት ሁኖ ተሾመ። ጴጥሮስ የሚባል ጳጳስን ለኢትዮጵያ አገር ሹሞ ነበር ። አባ ጴጥሮስም ወደ ኢትዮጵያ በደረሰ ጊዜ ጥቂት ዘመን በሰላም ኖረ።

በዚያም ሳለ ሰይጣን ያደረባቸው ከሶርያ የመጡ ሁለት መነኮሳት አባ ቆዝሞስ በሾመው በአባ ጴጥሮስ ላይ ሴራ ሰርው በእርሱ ፈንታ እነርሱ ተሾሙ። ከግዜም በኋላ በእግዚአብሔር ቸርነት ሴራቸው ታወቀ የኢትዮጲያ ንጉስም አባ ጴጥሮስን ያመጡት ዘንድ አዘዘ ነገር ግን ሙቶ አገኙት ይሕንንም አባ ቆዝሞስ ሲሰማ በጣም አዘነ። በዚህም ምክንያት ለሰማንያ አራት ዓመታት ያህል ለኢትዮጵያ ሰዎች ጳጳስ ተሹሞ አልተላከላቸውም።

አባ ቆዝሞስም እጅግ ሸመገለ የሹመቱም ዘመን ደኀንነትንና ሰላምን የተመላ ነበር። በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም አሥራ ሁለት ዓመት ኖረ በሰላምም አረፈ እግዚአብሔርበጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
መጋቢት ፬ /4/


በዚህችም ቀን የከበረና የተመሰገነ መኰንን ሐኑልዮስ ከጵንፍልያ አውራጃ ብርግያ በምትባል ከተማ በሰማዕትነት አረፈ።

ይህንንም ቅዱስ ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ መውደዱና እርሱንም ስለ ማምለኩ ከዲዮቅልጥያኖስ ተልኮ የመጣ ብርይንኮስ የተባለ መኰንን ያዘው።

በመኰንኑም ፊት በቆመ ጊዜ ምስጋና ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ከፍ ከፍ ባሉ ቃላት አብራርቶ ገለጠ። ብዙ ምስጋናዎችንም ለእግዚአብሔር አቀረበ የረከሱ ጣዖታትንም ረገማቸው።

መኰንኑም በዕንጨት መስቀል ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ስለ ከበረ ስሙም ምስክር ይሆን ዘንድ ስለ አደለው ምስጋና ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው። ከዚያም ምስጋና ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
1
በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ

የማቴዎስ ወንጌል ፲፮᎓፪
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።"

(ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)
1🥰1