ኤፌሶን~፩
650 subscribers
75 photos
1 video
23 links
Download Telegram
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #ለታላቁ_አባት ለተመሰገኑ አባት አርባ ዓመት ሙሉ የሴቶች ፊት ሳያይ ለኖረ #ለአቡነ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል፣ በአባ መቃርስ ገዳም በአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ለሆነ ለከበረ አባት #ለአቡነ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል፣ ከመኰንኑ ከአርያኖስ የጭፍሮቹ ታላላቆች #ለቅዱሳን_ለኮርዮንና_ፊልሞና ከእናርሳቸው ጋር ካሉ #ከአርባ_ወታደሮች ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ተጋድይ ለሆነ #ለአባ_ዘካርያስ ዕረፍትና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦ ሄሮድስ ከገደላቸው #ከከበሩና_ከነጹ_ሕፃናት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️
1🙏1
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #ለሊቀ_ዲያቆናት_ለቀዳሜ_ሰማዕት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ_ለልደቱና_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ከሶርያ_አገር_ለሆነ በከሀዲው መክስምኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተበቀበለ #ለቅዱስ_ለውንድዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስልሳ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_መቃርስ ዕረፍት፣ #ከከበሩ_ከአክሚም_ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ከፈጸሙ ስማቸው #ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ ዕረፍት፣ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ቊጥራቸው #ከካህናት_ስምትት_መቶ#ከዲያቆናት_መቶ_ሠላሳ_ከመምህራን_ኃምሳ#ከሦስት_ከቤተ_ክርስቲያን_ሹማምንት_ከሰማንያ_መሳፍንት_ከሠላሳ_ሁለት_ንፍቅ_ዲያቆናትና_ከመቶ_ኃምሳ_ሕዝባውያን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️
ጥር ፬ /4/

የተመሰገነ ዮሐንስም ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ሰዓት እንደ ቀረበ በአወቀ ጊዜ ሕዝቡን ጠራቸው ጸሎትንም ጸለየና ኅብስቱን ባርኮ ቆረሰ ይህም የጌታችን ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ባረካቸው አጽናናቸውም ።

ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለትን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ ። ከኤፌሶንም ከተማ ውጭ ወጣ ጕድጓድ እንዲቆፍሩም አዘዘ ከውስጥዋም ወርዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ ከአንድ የበፍታ ቀሚስ በቀር አላስቀረም ። እጆቹንም አንሥቶ ጸለየና ወደ ከተማ ይመለሱ ዘንድ አሰናበታቸው በክርስቶስም ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝቡ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዛቸው በጎ ሥራዎችንም ይሠሩ ዘንድ ጌታችን ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፈለው ዘንድ አለውና ።

ይህንንም በተናገረ ጊዜ አለቀሱ እጆቹንና እግሮቹን ስመው በጒድጓዱ ውስጥ ትተውት ወደ መንገድ ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለሰዎች ነገሩዋቸው ሁሉም ደንግጠው መጡ ግን ልብስና ጫማ እንጂ መቃብሩን አላገኙም እጅግም አደነቁ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስን በዚህ በጎ ዕረፍት ያሳረፈው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦  መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻

በዚች ቀን

✨️️️️️️🌻✨️️️️️️
#የክብር_ባለቤት_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ #በሥጋው_ወደ_ቤተ_ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ

✨️️️️️️🌻✨️️️️️️
ልሳነ ዕረፍት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ" ብሎ እንደተናገረ።

✨️️️️️️🌻✨️️️️️️
ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር እነርሱ እንዳሰቡት ሁኖ ቢሆን ኑሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን የሚያገኙ በሆኑ ነበር

✨️️️️️️🌻✨️️️️️️
ጌታችን ግን ግዝረትን ሕግ ፈጸመ ለእኛ በግዝረት ፈንታ የክርስትና ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ በላ በእርሱም ፈንታ ሥጋውንና ደሙን ሰጠን።

ተጨማሪ ያንብ

✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻✨️️️️️️🌻
1
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #ለአጋዕዝተ_ዓለም_ለቅድስት_ሥላሴ የሰናዖር (የባቢሎንን) ቋንቋቸው ለደባለቁበትና የሠሩት ግንብ ላፈረሱበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል (ታሪኩ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ዘፍ11፥1-9)፣ ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀት ላጠመቀው ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳስ ለከበረ አባት #ለአቡነ_ሶል_ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለታላቁ አባት #ለቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ ለመታሰቢያው  በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከሰሎሞን#ከጎርጎርዮስ_ከማርቆስ_ከአትያኖስ_ከሉያ#ከመልይን_ከሱስዮስና_ከማርትይ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴


እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቀ_ነቢያት አንዱ ለሆነው #ለቅዱስ_ሚክያስ ለመታሰቢያ በዓል፣ #የአባ_መቃርስ_ቤተ_ክርስቲያን በከበረና በተመሰገነ በእስክድርያው ሊቀ ጳጳሳት #በአባ_ብንያሚን እጅ ለከበረችበትና ለእስክድርያ ሠላሳ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ብንያሚን_ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ  በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ ፦ከእስክንድርያ  ሠላሳ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_እንድራኒቆስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                       

@efeson_2

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴


እንኳን ለከበሩ አባት ጌታችን በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጦ በቤታቸው ጣራ ለገባላቸው #ለአባ_አብርሃም_ግብፃዊ  ዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ አባቶች #ከአባ_ጊዮርጊስ_ከአባ_ኖስሞስና ከሮሜ ሰው #ዲዮስቅርስ ዕረፍት፣ #ከአባ_ኪናፎርያ_ከበጥሪቃና_ከጥምያኒ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️
💫💦💫💦💫💦💫💦💫💦💫💦💫💦💫💦💫💫💦💫💦💫💦💫💦💫💦💫

@efeson_2

ከተራ መቼ ተጀመረ? ሃይማኖታዊ ትርጉሙስ ምንድነው?


ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ




የጥምቀት አከባበር በሀገራችን ኢትዮጵያ ታቦት ተሸክሞ ወንዝ ወርዶ የክርስቶስን በዓለ ጥምቀት ማክበር የተጀመረው በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ሲሆን ይበልጥ ተጠናክሮ በሜዳና በውኃ ዳር ማክበር የተጀመረው በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (ከ፭፻፭ - ፭፸፩ ዓ.ም) እንደ ሆነ ይነገራል። ይኸውም ከማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድ (፭፻፭ - ፭፻፸፪ ዓ.ም) ዜማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ታቦታቱ በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን ጠዋት ወደ ወንዝ ወርደው ማታ ወደ መንበረ ክብራቸው እንዲመለሱ ይደረግ ነበር።               

ተጨማሪ ያንብቡ              

@efeson_2

💫💦💫💦💫💦
🙏 ከአንዱ ወዳጄ🙏 መልክት 🥹

ሁለት ጊዜ ቀላል (Minor surgery) እንዲሆም ህመሙ በነዚህ ሁለት ቀዶ ጥገና ሊፈታ ባለመቻሉ በቅርቡ ከባድ ቀዶ ጥገና(major surgery)  ተደርጎለት ነበር።እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ደህና ሆኗል፣ ክብር ለመድኃኔዓለም ይሁን! 🥹

ነገር ግን ይህ የጤና መታመም ከፍተኛ የገንዘብ ጫና ፈጥሮበታል።ቤተሰቦቹ ለህክምና ወጪዎች ሲሉ ያለውን ሁሉ አውጥተዋል፣ እሱም ምንም አልያዘም። በአሁኑ ወቅት አካውንቱ ላይ ያለው ገንዘብ የገንዘብ መጠን በጣም ትንሽ ነው። 😢 ቤተሰቡም ለዛ ሕክምና ወጪ ያወጡት ተበደረው ነውና እሱን በትምህርቱ ለሚያስፈልገው ነገር እገዛ ማድረግ እጅጉን ከባድ ሆኖባቸዋል::

አሁን ደግሞ ዩኒቨርሲቲ ገብቷል።የመጀመሪያ ሳምንት ለሚያስፈልገው ሰርተፍኬት ፕሪንት ለማድረግ ከነበረችው 200 ብር ላይ አውጥቶ አሁን 100 ብር ብቻ ነው የቀረው።እንደ ማንኛውም ተማሪ ፕሪንት እንኳ ማድረግ አልቻለም።

"ይህ ሁሉ የኃጢአቴ ውጤት ነው፣ እሄ ሲያንሰኝ ነውና ጸልዩልኝ" በማለት የመንፈስ ጭንቀቱንና ትህትናውን አሳይቷል።ስመ ክርስትናውም ኃይለኢየሱስ ይባላል በፀሎት በቆምን ሰዓት ሁሉ በፀሎት እንድናስበው ጠይቆናል 🙏🙏🙏::"ለሰው መድኃኒቱ ሰው ይባል የለ፣ አደራችሁን" በማለት ከእኛ እርዳታን ይፈልጋል።

ቢያንስ ለመማሪያ የትምህርት ግብዓት ሚያሟላበት እና ለፕሪንት ለኮፒ ሚሆን ነገር ብናግዘው መልካም ነው።ወንድማችን "ማርያምን 50 ብር ቢሆን ለእኔ ትልቅ ነገር ነው!" ብሏል።
የቻልነውን ያህል በጸሎትም ሆነ በገንዘብ እንርዳው።እያንዳንዱ ትንሽ እርዳታ ትልቅ ለውጥ ያመጣለታል። 🙏

የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥሩ:
1000670545788
ስለ እናታችን ስለ እማምላክ ስለ ኪዳነምህረት ስንል ሁላችንም ከጉድለታችን ላይ ያቅማችንን እንርዳው እናግዘው በፀሎትም እናስበው::
ጥር ፳፫ /23/


በዚች ዕለት የጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነ ሐዋርያው ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። የዚህም ቅዱስ ልደቱና እድገቱ ልስጥራን ከሚባል አገር ነው አባቱም ከዋክብትን የሚያመልክ ዮናናዊ ነው እናቱ ግን በኦሪት ሕግ ጥላ ሥር ያለች ናት።

የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም በልስጥራን ሀገር በሰበከ ጊዜ ይህ ጢሞቴዎስ ስብከቱንና ትምህርቱን ሰማ እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያደርጋቸውን ድንቆች ተአምራቶችን አይቶ እሊህም ተአምራቶች አስተዋዮችና ጥበበኞች የሚደነግጡባቸው ናቸው ስለዚህም ወደ ሐዋርያ ጳውሎስ ሒዶ በእርሱ ትምህርት በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቆ የሐዋርያ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ ሆነ ወደ ብዙ አገሮችም ተከትሎት በመሔድ ከእርሱ ጋር ደከመ ታላቅ መከራና ብዙ ኀዘንም ደርሶበታል ሐዋርያው ጳውሎስም በኤፌሶን ውስጥ በአንዲት አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው።

በዚያንም ጊዜ ወደርሷ ገብቶ ለሰዎቿ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ብዙዎችንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ከዚህም በኋላ በዙሪያዋ ወዳሉ ብዙዎች አገሮች በርቀትም ለሚገኙ አገሮችም የከበረ ወንጌልን ሰበከላቸው።

በትምህርቱም አይሁድንና ዮናናውያንን ይገሥጻቸውና ይዘልፋቸው ነበር እነርሱም ቀንተውበት ሁሉም በጠላትነት ተነሡበት ተሰብስበውም ገደሉት ምእመናንም ሥጋውን አንሥተው ቀበሩት ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከ ነገሠ በዚያው ኖረ እርሱም ስለ ሥጋው አስቦ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ በጥር ወር በሃያ ሰባት ቀን አፈለሰው በዚያችም ቀን በዓል አደረገለት።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
ጥር ፳፯ /27/


በዚችም ዕለት የአዳም ልጅ ኄኖክን መላእክት ይዘው አሳረጉት።

ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ትእዛዝ ጸሐፊ ተባለ።

በደብር ቅዱስ ለነበሩ ለኃጢአት ለሚተጉ ለሴት ልጆች ይዘልፋቸው ዘንድ ቃል እንደጠራውና እንዳሳየው ተናገረ።  በእሳት ቅጽርም የተሠራ በክብር ከሁሉ የሚበልጥ በውስጡም ከፍ ያለ የእግዚአብሔርን ዙፋን አየሁ መልኩም እንደ ውርጭ ነው አጎበሩም እንደሚያበራ ፀሐይ ነው። ከዙፋኑም በታች የኪሩቤል ድምፅ ይሰማል።

በሰማይ ገጽ ስለሚመላለሱ ብርሃናት እንዲህ አለ አንዱም አንዱ በየወገናቸው በሠለጠኑበትና በተሠየሙበት ጸንተው ይኖራሉ ስለ ነፋሳትም መውጫዎች እንዲህ ብሎ ተናገረ ሦስቱ በሰማይ ገጽ ሦስቱ በምድር ገጽ ሦስቱ በቀኝ ሦስቱ በግራ ናቸው። ስለ አዳምም እንዲህ አለ እነሆ በሬ ከምድር ወጣ ፀዓዳም ሆነ ስለ ሔዋንም ደግሞ ሴት እምቦሳ ከርሱ ወጣች አለ።

ስለ ምኵራብም ያንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ። ስለ ቤተክርስቲያንም ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ እስቲሠራ ድረስ አየሁ ከቀድሞውም ቤት የበለጠ ነው በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሠማራሉ አለ ። ስለ ምእመናንም የእሊህም በጎች ፀጕራቸው ንጹሕ ነጭ ነው የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሠማራሉ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሆነዋልና።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር


@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
መድኃኔዓለም ሆይ አስቀድሞ ፈያታዊ ዘየማንን እንዳስብከው አቤቱ አዳኝ ቤዛ በሚሆን መስቀልህ አስበኝ፤ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ ቸር ጠባቂ ነህና እንደ ዓይን ብሌን ጠብቀኝ፤ አቤቱ እኔን መከረኛውን ሃዘንተኛውን በምስጋናህ የወይን ጠጅ አስደስተኝ አረጋጋኝ።
    
                "መልክአ መድኃኔዓለም"



@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን ጌታችን በአካል ተገልጦ በደሃ ሰው ተመስሎ ከማኅበረ ዴጔ ጋር በመካከላቸውም ተገኝቶ የጽዋ ማኅበር እየጠጣ ተራው ደርሶ ተዓምር አድርጎ  አምላክነቱ ለገለጠበት ቀን ለመታሰቢያ በዓል፣  የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በራእይ ለተገለጠላትና ከከበሩ ነገሥታት ወገን ለሆነችው ዓለምን ንቃ በመመንኰስ በምትተኛ ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ እየተኛችና ጥሬ ባቄላን ብቻ እየተመገበች በታላቅ ተጋድሎ ለኖረችው ለከበረች ቅድስት አክሳኒ ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ ተጋዳይ ለሆነ በበረሃ ውስጥ የሞተ ሰው ራስ ቅል አግኝተው የራስ ቅሉን ላነጋገሩና ሥራውን መርምረው ለተረዱ በኋላም አማልደውት ምሕረትን ላሰጡት አባ እስጢፍኖስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከድንግል እመቤታችን ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከተወለደበት ከልደቱ መታሰቢያ፣ ከመስተጋድል ከከበረ ሰማዕት ከሰርያኮስ ከመታሰቢያው፣ ከሮሜ ሰዎች ውስጥ ከንጹሐት ሴቶች ከመታሰቢያቸው፣ ከፊልንማ፣ ከኢያልኒ፣ ከሰረባሞኒና ከቃውት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
🔥1
ጥር ፴ /30/


በዚችም ዕለት ተገዳይ የሆነ መነኰስ የከበረ አክርስጥሮስ አረፈ።

ይህም አባት በዮርዳኖስ ገዳም የሚኖር ነበር ከመነኰሳቱም አንዱ እየሰገደ እንዲህ ብሎ ጠየቀው "አባቴ አክርስጥሮስ ሆይ ከእኔ ጋር ፍቅርን አደርግ እጠቀምበትም ዘንድ ሥራህን ሁሉ ንገረኝ" አለው።

ሽማግሌው አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት ልጄ ሆይ ጎልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እጸልይ ዘንድ በሌሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሔድ ነበር። ዐሥራ ሁሉት ደረጃዎችም አሏት በየአንዳንዱም ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶችን እሰግዳለሁ ደወልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት ከወንድሞች ጋርየማኅበሩን የጸሎት ሥርዓት እፈጽማለሁ እንዲሁም በማድረግ ዐሥር ዓመት ኖርኩ።

ከሌሊቶችም በአንዲቱ የተለመደ ጸሎቴን ከፈጸምኩ በኋላ ልቡናዬ በተመሥጦ ተማረከ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዞችን ሲያበሩ እኩሌቶቹ ሲበሩ እኩሌቶቹም ሲጠፉ አየሁ። እኔም ይህ ሥራ ምንድን ነው አልኳቸው እነዚያም አባቶች ባልንጀራውን የሚወድ መቅረዙ የበራለታል አሉኝ እኔም ደግሜ መቅረዜ የቱ ነው አልኋቸው እነርሱም ሒድ ከወንድሞችህ ጋር ተፋቀር እኛ እናበራልሃለን አሉኝ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም።

ከዚህም በኋላ አባ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሒዶ በዚያ እየተጋደለ ኀምሳ ዓመት ኖረ ወደርሱም እንዲህ የሚለው ቃል መጣ ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ ከዚህም በኋላ በተመለሰ ጊዜ በሰላም አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
1
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን #ጌታችንን_ሽቱ_ለቀባችው_ለማርያም_እንተ ዕፍረት ለዕለፍቷ መታሰቢያ በዓል፣ ለዓለሙ ሁሉ መምህር ለሆነ ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_አቡሊዲስ ሥጋው ከባሕር ለወጣበት በዓልና #ለከበሩ_ቅዱሳን_አቡቂርና_ዮሐንስ ለሦስቱ ደናግላን #ለቅድሳት_ቴዎድራ_ቴዎፍና_ቴዎዶክስያና ለእናታቸው #ለቅድስት_አትናስያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ  ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
የካቲት ፲ /10/


በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የዕልፍዮስ ልጅ የከበረ ሐዋርያ ያዕቆብ በሰማዕትነት ሞተ።

ይህም ሐዋርያ በብዙ ሀገሮች ውስጥ ከሰበከ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ወደ ምኵራብም ገብቶ የክብር ባለቤት የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት በግልጥ አስተማረ።

አይሁድም ደሙ በእኛ ላይ ይሁን ብለው ከሕዝብ መካከል ነጥቀው ወሰዱት ለሮም ንጉሥ እንደራሴ ለንጉሥ ቀላውዴዎስም አቀረቡትና ይህ ሰው ስለ ቄሣር ሳይሆን ስለ ሌላ ንጉሥ ይሰብካል ብለው ወነጀሉት ንጉሡም በሰማ ጊዜ በደንጊያ እንዲወግሩት አዘዘ አይሁድም ፈጥነው ወገሩት ነፍሱንም በጌታችን እጅ ሰጠ ምእመናንም ሥጋውን ገንዘው ቀበሩት።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ ያዕቆብ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
የካቲት ፲፩ /11/


በዚች ቀን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት በላትያኖስ በሰማዕትነት ሞተ።

ይህም ቅዱስ ብልህና አዋቂ የሆነ ታላቅ ተጋድሎን የሚጋደል ነው በሮሜ ሀገርም ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ በቅዱስ ጴጥሮስ ወንበር ላይ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሰላም ኖረ። ሕዝቡን የቀናች ሃይማኖትን እያስተማራቸው ሳለ መኰንኑ ፊሊጶስ በንጉሥ ቀላውዴዎስ ላይ ተነሥቶ በገደለው ጊዜ በርሱ ፈንታ ነገሠ በምእመናንም ላይ ታላቅ መከራን አመጣ በዚህ በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ብዙዎች በሰማዕትነት ሞቱ።

በዘመኑም ሰባት ሰዎች ከእርሱ ሸሹ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመት ተኝተው ነቁ እርሱም በኤፌሶን ከተማ መስጊድ ሠርቶ በውስጡ ጣዖታትን አኖረ ሰዎችን ሁሉ ለጣዖታት እንዲሠዉ አስገደዳቸው ለጣዖታት ያልሠዉትንም ገደላቸው።

ይህ የከበረ በላትያኖስም የጣዖታት አምልኮን እንደሚቃወም ሕዝቡም በክብር ባለቤት በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ እንደሚያስተምር ንጉሥ በሰማ ጊዜ ወደ ሮሜ አገርልኮ ወደ ኤፌሶን ከተማ አስመጣውና ለጣዖታት እንዲሠዋ ለመነው።

እርሱ ግን ቃሉን አልሰማም ተሣለቀበት አማልክቶቹንም ረገመ እንጂ። ንጉሡም ተቆጣ አንዲት ዓመት ያህልም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ በሰይፍ ራሱን ቆረጠው የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
1
የካቲት ፲፫ /13/


በዚች ዕለት የከበረ አባት የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ጢሞቴዎስ አረፈ።

እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሁለተኛ ነው ይህንንም አባት ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ መከራና ችግር ደርሶበታል እንዲህም ሆነ በዚያን ወራት የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ ወደ ግብጽ አገር መጣ እርሱም ከዚህ አባት ጢሞቴዎስ ጋር ምእመናንን እያጽናና ከሀገር ወደ ሀገር ከገዳም ወደ ገዳም ከቦታ ወደ ቦታ የሚዘዋወር ሆነ።

በዚህም አባት ጢሞቴዎስ ዘመን ከቊስጥንጥንያ የመጡ ክፉዎች ሰዎች በግብጽ አገርተገለጡ እነርሱም የክርስቶስን ተዋሕዶ ምትሐት በሚያደርግ መከራውንና ትንሣኤውንም በሚክድ በረከሰ በአውጣኪ ትምህርት የሚያምኑ ናቸው ይህም አባት አውግዞ ከግብጽ አገር አሳደዳቸው።

ዳግመኛም በዘመኑ ምእመን ንጉሥ አንስጣስዮስ አረፈና በርሱ ፈንታ ኬልቄዶናዊ መናፍቅ ዮስጣትያኖስ ነገሠ እርሱም በአባ ጢሞቴዎስ ፈንታ ሊናርዮስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው ሃይማኖታቸው የቀና ምእመናንን ሁሉ በኬልቄዶን ግባኤ ወደተወሰነ ሃይማኖት ሊመልሳቸው ወዶ በቍስጥንጥኒያ ጉባኤ ሰብስቦ የአንጾኪያውን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስን ከኤጲስቆጶሳቶቹ ጋር አስመጣው።

በኬልቄዶን ጉባኤ በተወሰነች በተበላሸች ሃይማኖቱ ያምኑ ዘንድ አስገደዳቸው እነርሱ ግን አልተቀበሉትም ትእዛዙንም አልሰሙም ስለዚህም ሃይማኖታቸው በቀና ምእመናን ሁሉ ታላቅ መከራ አደረሰባቸው። ይህም አባት ጢሞቴዎስ በመንበረ ሢመቱ ዐሥራ ሰባት ዓመት ኑሮ በሰላም አረፈ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@efeson_2

💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
1
🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️

"ጸሎት በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ ማእበል ለሚያንገላታቸው መልሕቅ የድሃው ሐብት የባለጸጋው ደህንነት የታማሚው መዳኛ ወይም ጤና ማግኛ ነው ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል።"

                              🍁️ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው። አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደኅንነት በሚሰማህ አሳቻ ሰዓት ሳታውቀው ይዘርፈሀል፤ ይገድልህማል። "

                             🍁️ቅዱስ ጎርጎርዮስ

"ብርሃን ወደ አንድ ቤት ውስጥ ሲገባ ጨለማን እንደሚያስወግድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን መፍራት ወደ አንድ ሰው ልብ ሲገባም አለማወቅን (በኃጢአት የሚወድቅባትን) ያስወግዳል።"

                           🍁️አባ እንጦንስ

"ካህኑን እንደ መንፈሳዊ አባትነቱ እየው፤ ልክ በሽተኛ የተሸፈኑ ቁስሎችን ለሐኪም እንደሚያሳይና እንደሚፈውስ ምስጢሮችህን በግልጽ ንገረው”

                         🍁️ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ።


"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"

                          🍁️ ቅዱስ ባስልዮስ


"ጥላቻን በልቡ ውስጥ የሚሸሽግ ሰው እባብን በጭኑ ላይ የሚያስቀምጥን ሰውን ይመስላል።
ጭስ ንቦችን እንደሚያባርር ሁሉ ጥላቻም በልብ ውስጥ የተቀመጠን እውቀት ያጠፋል፡፡"

                        🍁️ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ


ሰው ሆይ! ጻድቅ መሆንን ትወዳለህን? አዎን ትለኝ እንደሆነ፥ እንግዲያውስ ለራስህ ንፉግ ለሌላው ግን ቸር ሁን፡፡

                     🍁️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


@efeson_2

🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️🍁️
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን #ለኢትዮጵያውያን_ጻድቅ ውኃ ከዓለት ድንጋይ ላይ እያፈለቁ አሕዛብን ሁሉ እያስተማሩ ያጠምቁ ለነበረ፤ ኅብስትም ከሰማይ እየወረደላቸው ሕዝቡን ያቆርቡ ለነበረ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ክፍለ_ማርያም_ዘድባጋ ከዚህ ዓለም እንደነ #ቅዱሳን_ሄኖክና_ኤልያስ ከሞት ለተሰወሩበት በዓልና #ለአባ_ገብረ_መርዓዊ_ዘአግዶ_ገዳም ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።

@efeson_2

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁