መስከረም ፱ /9/
በዚህች ቀን መጺል የምትባል አገር ኤጲስ ቆጶስ፤ ቅዱስ አባት አባ ቢሶራ በሰማዕትነት አረፈ።
በወቅቱ ዲዮቅልጥያኖስ የተባለ ክፉ ሰው ንጉስ የነበረበት ግዜ ነበር። በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሰይጣን ቀጥሎ እንደዚህ የከፋ ስም የለም። የዓለም ክርስቲያኖችን የጨፈጨፈ ሰው ነው። መከራውም እየገፋ ሲመጣ ቅዱሱ በመፍራት ፈንታ የሰማዕትነት ፍቅር አደረበት:: በክርስቶስ ስም ደሙን ያፈስ ዘንድ ወደደ።
ሕዝቡንም ሰብስቦ አቆማቸው፤ ሊጠብቁት የሚገባውን ለጽድቅ የሚያበቃቸውን ትዕዛዝ ሁሉ አዘዛቸው። ከዚህም በኋላ ለሰማዕትነት እንደተዘጋጀ ነገራቸው። ይህንንም በሰሙ ግዜ ሁሉም አለቀሱ። የሙት ልጆች እንሆን ዘንድ ለምን ትተወናለህ፤ እንድትሄድ አንለቅህም አሉት ሊይዙትም ቃጡ። ቅዱሱም ሰላምታ ሰጥቷቸው ከእነርሱ ዘንድ ወጥቶ ተጓዘ። አንዳንድ አባቶችም አብረን እንሞታለን ብለው አብረውት ሄዱ።
በኋላም መኰንኑ ጽኑ የሆነ መከራ አደረሰባቸው ፤አባቶች ግን በታላቅ ትዕግስት ጸኑ። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውንም በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ። በዚህች ዕለትም የሕይወት አክሊልን በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ።
በረከታቸው ይደርብን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@efeson_2
💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
🔥1
መስከረም ፲ /10/
በዚህች ዕለት ጼዴንያ በምትባል አገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል፤ ከሠሌዳዋም ቅባት የሚንጠፈጠፍባት የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ተዐምር ተገለጠ።
ይህችን ሥዕል የሳላት ቅዱስ ሉቃስ ነው። ወደ ጸዴንያ እንዴት መጣች ቢሉ፤ አንዲት ማርታ የምትባል ሴት ነበረች በቤቷም እንግዳ ትቀበል ነበር። ድንግል ማርያምንም አብዝታ ትወዳት ነበር። በአንዲት ቀንም ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል መነኩሴ በእንግድነት መጣ። በማግስቱ ስትሸኘው ወዴት ነህ ብላ ጠየቀችው። እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም እንደሆነ ነገራት። እርሷም ሲመለስ የእመቤታችንን ሥዕል አምጣልኝ አለችው።
ከዚህም በኋላ ከቦታው ደርሶ ሥዕሏን ሳይገዛ ተመለሰ፤ በመንገድም ሥዕሏን ለምን አልገዛህም? የሚል ድምጽ ሰምቶ ተመልሶ ገዛ። በጎዳናው እየተመለሰ ሳለም የሚያስፈሩ ወንበዴዎች፤ ኋላም አንበሳ ገጠመው፤ የያዛት ሥዕልም ቃል አውጥታ አዳነችው። አባ ቴዎድሮስም ይህን ድንቅ ተአምር ባየ ግዜ ሥዕሏን ወደ ሀገሩ ሊወስዳት ወደደ። በሌላ ከተማም አድርጎ ሊሄድ መርከብ ተሳፈረ።
በመርከቧ ሳለም ታላቅ ነፋስ ተነስቶ አቅጣጫውን አስቀይሮ ወደ ጸዴንያ ወሰደው። ኋላም ቢመሽበት ማርታ ቤት ሄደ እራሱን ግን አልገለጠም። በማግስቱም ተሰውሮ ከከተማው ሊወጣ ቢሞክር መውጫው ጠፍቶት ሲዞር ውሎ ተመለሰ። እንዲህም እያለ ሶስት ቀን ሆነው። ማርታም ይህን ተመልክታ ምን እንደሆነ ጠየቀችው። እርሱም ሁሉንም ነገራት።
በኋላም የመነኩሴውን እጅና እግር ስማ ሥዕሏን ተቀበለች። በታላቅ ክብርም አስቀመጠቻት። ያም መነኩሴ እስከሚሞትበት ቀን ድረስ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገለ ኖረ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
@efeson_2
💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
ሰላም ለሥዕልኪ ፥ ሶበ ጸለየት ማርታ
አጽነነት ርዕሳ ከመ_ትትመጠው ስእለታ
ምክሐ ታዴዎስ አንቲ ማርያም ፤ ወሞገሰ ቶማስ ስሙየ መንታ። አመ ኢታድኅን ፥ እም ወለታ ፤ ወአመ_ታገብእ ምድር ማኅፀንታ ፤ ኵንኒ_ለመዋቲ ሐገፋ ወወልታ።
◈◈_◈◈◈_◈◈◈◈_◈◈◈◈◈__◈◈
ስሙ ሁለት የሆነ ፥ የቶማስና ፥ የሐዋርያው የታዴዎስ ትምክህት ማርያም ሆይ ፥ (በጼዴንያ አገር የምትኖር) ቅድስት ማርታ ፥ በጸለየች ጊዜ ፥ ጸሎቷን ለመስማት ራሷን ዘለስ ፥ ለአደረገች ሥዕለ_አድኅኖሽ ሰላም እላለሁ። ምድር አደራዋን ስትመልስ ፣ እናትም ፥ ሴት ልጇን በማታድንበት ዕለት ፣ ያን ዕለት ለሟች ለእኔ መደገፊያና ጋሻ ሁኚኝ።
⛲መልክዓ_ስዕል
አጽነነት ርዕሳ ከመ_ትትመጠው ስእለታ
ምክሐ ታዴዎስ አንቲ ማርያም ፤ ወሞገሰ ቶማስ ስሙየ መንታ። አመ ኢታድኅን ፥ እም ወለታ ፤ ወአመ_ታገብእ ምድር ማኅፀንታ ፤ ኵንኒ_ለመዋቲ ሐገፋ ወወልታ።
◈◈_◈◈◈_◈◈◈◈_◈◈◈◈◈__◈◈
ስሙ ሁለት የሆነ ፥ የቶማስና ፥ የሐዋርያው የታዴዎስ ትምክህት ማርያም ሆይ ፥ (በጼዴንያ አገር የምትኖር) ቅድስት ማርታ ፥ በጸለየች ጊዜ ፥ ጸሎቷን ለመስማት ራሷን ዘለስ ፥ ለአደረገች ሥዕለ_አድኅኖሽ ሰላም እላለሁ። ምድር አደራዋን ስትመልስ ፣ እናትም ፥ ሴት ልጇን በማታድንበት ዕለት ፣ ያን ዕለት ለሟች ለእኔ መደገፊያና ጋሻ ሁኚኝ።
⛲መልክዓ_ስዕል
❤2
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ አራት በዚህች ቀን ቅዱስ አባት አባ አጋቶን ዘዓምድ አረፈ።
ይህም ቅዱስ ለግብጽ አገር ደቡብ ከሆነ ተንሳ ከሚባል መንደር የሆነ ነው፤ ወላጆቹም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ለድኆችና ለችግረኞች መመጽወትን የሚወዱ ደጎችና ቸሮች ነበሩ። የአባቱም ስም መጥራ የእናቱም ስም ማርያ ነው የምንኵስና ልብስን ይለብስ ዘንድ የሚተጋና በልቡም ሁል ጊዜ የሚያስብና የሚታወክ ሆነ። ዕድሜውም ሠላሳ አምስት ዓመት በሆነው ጊዜ ቅስና ተሾመ ከዚህ ዓለምም የሚወጣበትን መንገድ ይጠርግለት ዘንድ ወደ ገዳም ሒዶ በዚያ እንዲመነኵስ እግዚአብሔርን እየለመነው የከበረች ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል የተጠመደ ሆነ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምክንያት ሰጥቶት ከሀገሩ ወጣ መርዩጥ ወደሚባልም አገር ገባ ከዚያም ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ በመነኰስ አምሳል ከእርሱ ጋር በመጓዝ ወደ ቅዱስ አባ መቃርስ ገዳም እስከ አደረሰው ድረስ እየመራው ወደ እስቄጥስ ገዳም ሔደ። ለከበሩ አረጋውያንም ለአባ አብርሃምና ለአባ ገዐርጊ ደቀመዝሙር ሁኖ ከእሳቸው ጋር ሦስት ዓመት ያህል ኖረ። ከዚህም በኋላ በአባ ዮሐንስ ቤተ መቅደስ ፊት አቆሙት በምንኵስናው ልብስና በአስኬማው ላይ ሦስት ቀኖች ያህል ጸልየው አለበሱት ከዚያችም ቀን ወዲህ ተጋድሎውንና የእግዚአብሔርን አገልግሎት እጥፍ ድርብ አደረገ። ተጋድሎውም ሁል ጊዜ በቀንና በሌሊት በመጾም፥ በመጸለይ፥ የሥጋው ቆዳ ከዐጥንቱ እስኪጣበቅ ያለ ምንጣፍም በምድር ላይ በመተኛት ሆነ። ሁል ጊዜም የአባ ስምዖን ዘዓምድን ገድል ያነብ ነበረ መንፈሳዊ ቅናትንም ቀንቶ ራሱን በገድል እሥረኛ ሊያደርግ በልቡ አስቦ ለከበሩ አባቶች አማከራቸው እነርሱም ይህ ሀሳብ መልካም ነው አሉት በላዩም ጸለዩ ከእርሳቸውም በረከትን ተቀብሎ ከገዳም ወጣ ለዓለም ቅርብ ወደ ሆነ ስካ ወደሚባል አገር ሒዶ በአንዲት ትንሽ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተቀመጠ ምእመናንም ዓምድ ሠሩለት። በዚያ ላይም ወጥቶ እየተጋደለና እያገለገለ ሃምሳ ዓመት ያህል ቆመ። በዘመኑም ሰይጣን ያደረበት ሰው ተገለጠ ብዙ ወገኖችንም አሳታቸው እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚቀመጥ ሁኖ ትምህርቱን የሚሰሙ ሕዝቦች የዕንጨት ቅርንጫፎችን በመያዝ በዙሪያው ይቀመጣሉ አባ አጋቶንም ልኮ ወደእርሱ አስመጣው በላዩም ጸለየና በሰውዬው ላይ አድሮ ለሰዎች በመናገር የሚያስተውን ሰይጣን ከእርሱ አስወጣው። እንዲሁም ሰማዕት ሚናስ ያነጋግረኛል የምትል ሴት ተነሥታ በቅዱስ ሚናስ ስም የውኃ ጒድጓድ እንዲቆፍሩ በጠበሉ ውኃ ተጠምቀው ከደዌያቸው እንዲፈወሱ የአገርዋን ሰዎች አዘዘቻቸው ያቺንም ሴት ወደርሱ አስመጥቶ በላይዋ ጸለየ ርኵስ መንፈስንም ከእርሷ አስወጣው። ዳግመኛም ሌላ ሰው ተነሣ እርሱም ጋኔን ይዞ ያሳበዳቸውን ሰበሰባቸው ሲደበድባቸውም ለጥቂት ጊዜ ጋኔኑን ያስተዋቸዋል ብዙዎችም ጋኔን የያዛቸው ወደእርሱ ተሰበሰቡ ቅዱስ አባ አጋቶንም ወደእርሱ እንዲመጣ ወደ ሰውዬው ላከ ሰውዬውም ትእዛዙን ሰምቶ አልመጣም የስሕተት ሥራውንም አልተወም። የዚያችም አገር ገዥ ሲያልፍ የሰበሰባቸው እብዶች ሰደቡት ረገሙትም ስለዚህ ያን ሰው መኰንኑ ይዞ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየውና በሥቃዩ ውስጥ ሞተ። ሌላው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንድ ቄስ ነበረ እርሱም ከአንዲት ሴት ጋር በዝሙት ወደቀ የአካሉም እኩሌታ በደዌ ተበላሸ ተሸክመውም ወደ አባ አጋቶን አደረሱት እርሱም ጸልዮለት በእግዚአብሔር ስም አዳነው ያንንም ቄስ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ እንዲጠነቀቅና በክህነቱም እንዳያገለግል አዘዘው። ይህም ቅዱስ አባ አጋቶን ብዙ ተአምራትን አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
@efeson_2
ከዚህም በኋላ በመላእክት አምሳል በመልካም ዝማሬ በመዘመር እያመሰገኑት ሰይጣናት ተገለጡለት እርሱ ግን የክብር ባለቤት ክርስቶስ በሰጠው ጸጋ ሽንገላቸውን አውቆ አዳኝ በሆነ በመስቀል ምልክት አማተበባቸው ፈጥነውም ከፊቱ ተበተኑ። ክብር ይግባውና እግዚአብሔርም ከዚህ ዓለም ድካም ሊያሳርፈው በወደደ ጊዜ ጥቂት ታሞ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ አስረከበ። ከዚህም በፊት ሕዝቡ ወደእርሱ ይሰበሰቡና የእግዚአብሔርን መንገድ ያስተምራቸውና በጸሎቱም ከበሽታቸው ይፈውሳቸው ስለነበር አሁን በአረፈበት ላይ በአገኙት ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሱ እነርሱ የሚያጽናናቸውን አባታቸውን በማጣት ከእርሱ ከቅዱስ አባት በመለየት የሙት ልጆች ሁነዋልና።
መላው የሕይወቱ ዘመንም መቶ ዓመት ሆነ ከርሱም ሠላሳ አምስቱን በዓለም ውስጥ ኖረ። ዐሥራ አምስቱን ዓመት በገዳም ኖረ አምሳውን በዓምድ ላይ ቁሞ ኖረ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛ ንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከ ቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን ቀሲስ ዴግና አረፈ። ደግሞ የሰማዕት መቃራ፥ የበርተሎሜዎስ፥ የአውዳራና የናሶን መታሰቢያቸው ነው። እግዚ አብሔርም በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
@efeson_2
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን ደግሞ የፃና መምህራን ለሆኑ አባቶች ዐሥራ አንደኛ የሆነ የፃና መምህር ቅዱስ አባት አባ ጴጥሮስ አረፈ።
ይህም በሥራው ሁሉ እውነተኛና ንጹሕ በቀንና በሌሊትም በጾምና በጸሎት የተጠመደ ሆነ። ሕዝቡም በጎ ሥራውንና ቅድስናውን በአዩ ጊዜ ለመምህርነት መርጠው ሾሙትና በሹመቱ ወንበር አርባ ስምንት ዓመት በሰማዕት ገላውዴዎስ መቅደስ ኖረ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
🙏አሜን።🙏
@efeson_2
🍀🍀🍀🍀✨✨✨✨🍀🍀🍀🍀
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ አራት በዚህች ቀን ቅዱስ አባት አባ አጋቶን ዘዓምድ አረፈ።
ይህም ቅዱስ ለግብጽ አገር ደቡብ ከሆነ ተንሳ ከሚባል መንደር የሆነ ነው፤ ወላጆቹም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ለድኆችና ለችግረኞች መመጽወትን የሚወዱ ደጎችና ቸሮች ነበሩ። የአባቱም ስም መጥራ የእናቱም ስም ማርያ ነው የምንኵስና ልብስን ይለብስ ዘንድ የሚተጋና በልቡም ሁል ጊዜ የሚያስብና የሚታወክ ሆነ። ዕድሜውም ሠላሳ አምስት ዓመት በሆነው ጊዜ ቅስና ተሾመ ከዚህ ዓለምም የሚወጣበትን መንገድ ይጠርግለት ዘንድ ወደ ገዳም ሒዶ በዚያ እንዲመነኵስ እግዚአብሔርን እየለመነው የከበረች ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል የተጠመደ ሆነ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምክንያት ሰጥቶት ከሀገሩ ወጣ መርዩጥ ወደሚባልም አገር ገባ ከዚያም ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ በመነኰስ አምሳል ከእርሱ ጋር በመጓዝ ወደ ቅዱስ አባ መቃርስ ገዳም እስከ አደረሰው ድረስ እየመራው ወደ እስቄጥስ ገዳም ሔደ። ለከበሩ አረጋውያንም ለአባ አብርሃምና ለአባ ገዐርጊ ደቀመዝሙር ሁኖ ከእሳቸው ጋር ሦስት ዓመት ያህል ኖረ። ከዚህም በኋላ በአባ ዮሐንስ ቤተ መቅደስ ፊት አቆሙት በምንኵስናው ልብስና በአስኬማው ላይ ሦስት ቀኖች ያህል ጸልየው አለበሱት ከዚያችም ቀን ወዲህ ተጋድሎውንና የእግዚአብሔርን አገልግሎት እጥፍ ድርብ አደረገ። ተጋድሎውም ሁል ጊዜ በቀንና በሌሊት በመጾም፥ በመጸለይ፥ የሥጋው ቆዳ ከዐጥንቱ እስኪጣበቅ ያለ ምንጣፍም በምድር ላይ በመተኛት ሆነ። ሁል ጊዜም የአባ ስምዖን ዘዓምድን ገድል ያነብ ነበረ መንፈሳዊ ቅናትንም ቀንቶ ራሱን በገድል እሥረኛ ሊያደርግ በልቡ አስቦ ለከበሩ አባቶች አማከራቸው እነርሱም ይህ ሀሳብ መልካም ነው አሉት በላዩም ጸለዩ ከእርሳቸውም በረከትን ተቀብሎ ከገዳም ወጣ ለዓለም ቅርብ ወደ ሆነ ስካ ወደሚባል አገር ሒዶ በአንዲት ትንሽ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተቀመጠ ምእመናንም ዓምድ ሠሩለት። በዚያ ላይም ወጥቶ እየተጋደለና እያገለገለ ሃምሳ ዓመት ያህል ቆመ። በዘመኑም ሰይጣን ያደረበት ሰው ተገለጠ ብዙ ወገኖችንም አሳታቸው እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚቀመጥ ሁኖ ትምህርቱን የሚሰሙ ሕዝቦች የዕንጨት ቅርንጫፎችን በመያዝ በዙሪያው ይቀመጣሉ አባ አጋቶንም ልኮ ወደእርሱ አስመጣው በላዩም ጸለየና በሰውዬው ላይ አድሮ ለሰዎች በመናገር የሚያስተውን ሰይጣን ከእርሱ አስወጣው። እንዲሁም ሰማዕት ሚናስ ያነጋግረኛል የምትል ሴት ተነሥታ በቅዱስ ሚናስ ስም የውኃ ጒድጓድ እንዲቆፍሩ በጠበሉ ውኃ ተጠምቀው ከደዌያቸው እንዲፈወሱ የአገርዋን ሰዎች አዘዘቻቸው ያቺንም ሴት ወደርሱ አስመጥቶ በላይዋ ጸለየ ርኵስ መንፈስንም ከእርሷ አስወጣው። ዳግመኛም ሌላ ሰው ተነሣ እርሱም ጋኔን ይዞ ያሳበዳቸውን ሰበሰባቸው ሲደበድባቸውም ለጥቂት ጊዜ ጋኔኑን ያስተዋቸዋል ብዙዎችም ጋኔን የያዛቸው ወደእርሱ ተሰበሰቡ ቅዱስ አባ አጋቶንም ወደእርሱ እንዲመጣ ወደ ሰውዬው ላከ ሰውዬውም ትእዛዙን ሰምቶ አልመጣም የስሕተት ሥራውንም አልተወም። የዚያችም አገር ገዥ ሲያልፍ የሰበሰባቸው እብዶች ሰደቡት ረገሙትም ስለዚህ ያን ሰው መኰንኑ ይዞ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየውና በሥቃዩ ውስጥ ሞተ። ሌላው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንድ ቄስ ነበረ እርሱም ከአንዲት ሴት ጋር በዝሙት ወደቀ የአካሉም እኩሌታ በደዌ ተበላሸ ተሸክመውም ወደ አባ አጋቶን አደረሱት እርሱም ጸልዮለት በእግዚአብሔር ስም አዳነው ያንንም ቄስ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ እንዲጠነቀቅና በክህነቱም እንዳያገለግል አዘዘው። ይህም ቅዱስ አባ አጋቶን ብዙ ተአምራትን አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
@efeson_2
ከዚህም በኋላ በመላእክት አምሳል በመልካም ዝማሬ በመዘመር እያመሰገኑት ሰይጣናት ተገለጡለት እርሱ ግን የክብር ባለቤት ክርስቶስ በሰጠው ጸጋ ሽንገላቸውን አውቆ አዳኝ በሆነ በመስቀል ምልክት አማተበባቸው ፈጥነውም ከፊቱ ተበተኑ። ክብር ይግባውና እግዚአብሔርም ከዚህ ዓለም ድካም ሊያሳርፈው በወደደ ጊዜ ጥቂት ታሞ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ አስረከበ። ከዚህም በፊት ሕዝቡ ወደእርሱ ይሰበሰቡና የእግዚአብሔርን መንገድ ያስተምራቸውና በጸሎቱም ከበሽታቸው ይፈውሳቸው ስለነበር አሁን በአረፈበት ላይ በአገኙት ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሱ እነርሱ የሚያጽናናቸውን አባታቸውን በማጣት ከእርሱ ከቅዱስ አባት በመለየት የሙት ልጆች ሁነዋልና።
መላው የሕይወቱ ዘመንም መቶ ዓመት ሆነ ከርሱም ሠላሳ አምስቱን በዓለም ውስጥ ኖረ። ዐሥራ አምስቱን ዓመት በገዳም ኖረ አምሳውን በዓምድ ላይ ቁሞ ኖረ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛ ንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከ ቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን ቀሲስ ዴግና አረፈ። ደግሞ የሰማዕት መቃራ፥ የበርተሎሜዎስ፥ የአውዳራና የናሶን መታሰቢያቸው ነው። እግዚ አብሔርም በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
@efeson_2
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን ደግሞ የፃና መምህራን ለሆኑ አባቶች ዐሥራ አንደኛ የሆነ የፃና መምህር ቅዱስ አባት አባ ጴጥሮስ አረፈ።
ይህም በሥራው ሁሉ እውነተኛና ንጹሕ በቀንና በሌሊትም በጾምና በጸሎት የተጠመደ ሆነ። ሕዝቡም በጎ ሥራውንና ቅድስናውን በአዩ ጊዜ ለመምህርነት መርጠው ሾሙትና በሹመቱ ወንበር አርባ ስምንት ዓመት በሰማዕት ገላውዴዎስ መቅደስ ኖረ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
🙏አሜን።🙏
@efeson_2
🍀🍀🍀🍀✨✨✨✨🍀🍀🍀🍀
🔥1🥰1
መስከረም ፲፭ /15/
በዚችም ቀን ጠራው ከሚባል አገር ለከበረ ጻድቅ አባት አባ ጴጥሮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህም ቅዱስ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተሰጠ የስእለት ልጅ ነው። በአደገም ጊዜ ለታላቅ ተጋድሎ ከልቡ በቆራጥነት ተነሣ። በቀንና በሌሊትም በጾም በጸሎት ተወስኖ ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን የሚያገለግል ሆነ።
ሰው የሚመገበውንም ምንም አይመገብም በዱር ያገኘውን ጥቂት ሣርን ይመገባል እንጂ። ደገኛው ምግቡ ግን ክብር ይግባውና የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ማመስገን ነበረ። በዚህም ምግባቸው የእግዚአብሔር ምስጋና የሆነ መላእክትን መሰላቸው።
አሎን በሚባል የወንዝ ውኃ ላይም ይመላለስ ዘንድ ውሀ ውስጥ የገቡት እግሮቹ አይርሱም ነበር ሥጋ እንደሌለው መንፈስ እስከሚሆን በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ከችግር ብዛትና ከሚለብሰው የብረት ልብስ ክብደት የተነሣ ሥጋው እጅግ ደርቆ የረቀቀም ሁኖ ነበርና በእንዲህ ያለ ተጋድሎም እግዚአብሔርን ከአገለገለው በኋላ በዚህች ቀን በክብር አርፏል።
የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
@efeson_2
🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊
መስከረም ፲፮ የደመራ ክብረ በዓል
ጥንተ ጠላታችን ዲያቢሎስ የቅዱስ መስቀሉን ሀይል ስለሚያውቅ አጥብቆ ይቃወመዋል፤ ስለዚህም አይሁድን አነሳሥቶ ከ፫፻ ዓመታት በላይ ተቀብሮ እንዲቆይ አድርጓል፡፡
ቀራንዮም ለመስቀሉ መትከያነት የተመረጠችውም ቀዳሜ ፍጥረት አዳም የተቀበረው በዚያ ስለ ነበረ ነው፡፡ ቦታው ‹‹የራስ ቅል ሥፍራ›› /ማቴ.፳፯፥፴፪/ መባሉም የኹላችን ራስ አዳም ዓፅሙ በዚያ ስላረፈ ነው፡፡ መስቀሉ በአዳማውያን ፍጥረታት አእምሮ ውስጥ እንጂ ከዚያ ውጪ የሚኖር ባለመኾኑ ተቀብሮ በቆየባቸው ዓመታት ውስጥም ፍቅሩ ከሰው ልጆች ልቡና አልወጣም፡፡
ጠላት በሠራው ተንኮል ተቀብሮ እንዳይቀር መስቀሉን እንድታወጣ መንፈስ ቅዱስ ንግሥት ዕሌኒን አስነሣት፡፡
ንግሥት ዕሌኒም የመስቀሉን ነገር ታስብ፤ ብርሃነ መስቀሉም ዘወትር በልቧ ያንጸባርቅ ነበር፡፡ ሐሳቧን እንዲያሳካላት የለመነችው አምላክም ኪራኮስ የተባለውን አይሁዳዊ ሽማግሌ ልኮ አቅጣጫውን አመላከታት፤ ኪራኮስ የጀመረውን ምሥጢርም መልአኩ ‹‹ደመራ ደምረሽ፣ ሰንድሮስ የሚባል ነጭ ዕጣን ጨምረሽ አቃጥዪው›› ብሎ ተረጐመላት፡፡ እርሷም መልአኩ እንደ ነገራት መስከረም ፲፮ በዕኩለ ሌሊት ደመራን ብታደርግ ጢሱ ሰማይ ደርሶ ወደ ምድር ተመልሶ መስቀሉ ወደሚገኝበት ተራራ ሰገደ፡፡ በጢሱ ምልክትነት መስከረም ፲፯ ቀን የተጀመረው ቍፋሮ መጋቢት ፲ ቀን አልቆ ዕሌኒ መስቀሉን ከልበ ምድር ለማውጣት ችላለች።
✝✝ መልካም በዓል ያድርግልን።✝✝
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
@efeson_2
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
🔥1
መስከረም ፳ /20/
በዚህች ቀን ለሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባት አትናቴዎስ አረፈ።
ይህም አባት አስቀድሞ የእስክንድርያ አገር ቤተክርስቲያን መጋቢ ነበር፤ ከእርሱም በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ይህን አባት ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ሁሉም ኤጲስቆጶሳት መኳንንቱና ሊቃውንቱ ሕዝቡም በአንድ ምክር ተስማሙ።
በእግዚአብሔር ሕግ በመጽናት ያደረገው መልካም ተጋድሎውና ቅድስናው ስለእርሱ ስለተነገረ መንፈስ ቅዱስም እንደ አደረበት ስለ ተረዱ ያለ ፈቃዱም ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በምክሩ፣ በትምህርቱ፣ በጸሎቱ ከዲያብሎስ ተኵላዎች በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው እኒህም ሃይማኖትን የሚለውጡ መናፍቃን ናቸው። በሊቀ ጵጵስናውም ፯ ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።
በረከታቸው ይደርብን! አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
@efeson_2
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
በዚህች ቀን ለሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባት አትናቴዎስ አረፈ።
ይህም አባት አስቀድሞ የእስክንድርያ አገር ቤተክርስቲያን መጋቢ ነበር፤ ከእርሱም በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ይህን አባት ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ሁሉም ኤጲስቆጶሳት መኳንንቱና ሊቃውንቱ ሕዝቡም በአንድ ምክር ተስማሙ።
በእግዚአብሔር ሕግ በመጽናት ያደረገው መልካም ተጋድሎውና ቅድስናው ስለእርሱ ስለተነገረ መንፈስ ቅዱስም እንደ አደረበት ስለ ተረዱ ያለ ፈቃዱም ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በምክሩ፣ በትምህርቱ፣ በጸሎቱ ከዲያብሎስ ተኵላዎች በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው እኒህም ሃይማኖትን የሚለውጡ መናፍቃን ናቸው። በሊቀ ጵጵስናውም ፯ ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።
በረከታቸው ይደርብን! አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
@efeson_2
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
🔥1
ውድ ወንድሜ ሰውን በስብከት ማገልገል የግድ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይደለም፣ ትልቁና ዋነኛው ሰውን በራስ ሕይወት መለወጥ ነው፡፡ ስለዚህ በሕይወትህ ለብዙዎች አብነት እንድትሆን እንጂ የግድ ስብከት አዘጋጅተህ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይጠበቅብህም፡፡ እንዲህ አይነት ሰው ከሆንክ ሰዎች ፊትህን ባዩት ጊዜ የዋህነትን፣ ሩህሩህነትን ይማራሉ፣ ንግግርህንም በሰሙ ጊዜ መንፈሰ ጠንካራነት፣ ታማኝነት፣ ፍፁምነትና ፍቅርን ያገኛሉ፡፡
(ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ - ከመንፈስ ነፃነት የተወሰደ)
@efeson_2
💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
(ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ - ከመንፈስ ነፃነት የተወሰደ)
@efeson_2
💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
እንኳን #የእናታች_የእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም (ለብዙኃን ማርያም)፣ #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል #በግሸን_በመስቀለኛው_ተራራ ላይ ገብቶ ለተቀመጠበት፣ #ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ሃይማኖታዊ_ውሳኔ ለመወሰን፤ #በኒቅያ_ጉባኤ_አርዮስን_ለማውገዝ ከሩቅ #ለተሰባሰቡበት_ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
እንኳን #የእናታች_የእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም (ለብዙኃን ማርያም)፣ #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል #በግሸን_በመስቀለኛው_ተራራ ላይ ገብቶ ለተቀመጠበት፣ #ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ሃይማኖታዊ_ውሳኔ ለመወሰን፤ #በኒቅያ_ጉባኤ_አርዮስን_ለማውገዝ ከሩቅ #ለተሰባሰቡበት_ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
እንኳን #ለቅዱሳን_ጻድቃን መነኰሳት #አውናብዮስና_እንድርያኖስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና #ለሰማዕቱ_ቅዱስ_ኤዎስጣቴዎስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመርዓተ_ክርስቶስ (ከክርስቶስ ሙሽራ) #ከቅድስት_ድንግል_ቴክላ ለመታሰቢያ በዓል፣ #ከአርባ_አራት_ሰማዕታት፣ #ከመንክራዊ_ጎርጎርዮስ #ከእንጺናና_ከብሊናም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
እንኳን #ለቅዱሳን_ጻድቃን መነኰሳት #አውናብዮስና_እንድርያኖስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና #ለሰማዕቱ_ቅዱስ_ኤዎስጣቴዎስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመርዓተ_ክርስቶስ (ከክርስቶስ ሙሽራ) #ከቅድስት_ድንግል_ቴክላ ለመታሰቢያ በዓል፣ #ከአርባ_አራት_ሰማዕታት፣ #ከመንክራዊ_ጎርጎርዮስ #ከእንጺናና_ከብሊናም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
🔥1
Forwarded from ነይ ነይ እምዬ ማርያም መዝሙሮች (𝕻𝖎𝖑𝖚𝕻ΔDΣR)
ወርኀ ጽጌ🥰
“በምሥራቀ ፀሐይ የምትመሰየሚው፤ እንደ መብረቅ ኃያል የሆነውን ጌታን የወለድሽ፣ ረቂቅ ምሥጢርን የምትችዪ፤ እንደ ፊደል ባለ ብዙ ዘር [ሆሄያት] የሆንሽ፣ ወንጌልን የወለድሽ፥ ነበልባለ እሳትን [ክርስቶስን] የተሸከምሽ ፤ በጽጌ ረዳ አምሳል የምትመሰየሚው ቅድስት ማርያም ሆይ! የዓለሙን እንግዳ ፈጣሪን የወለድሽ፤ ከፍዳ ሞት የምታድኚ፤ የወይን ሐረግ የወይን ዐፀድ [ተክል] አንቺ ነሽ።”
ሀሳብ አስተያየት ካለ @kingo08bot
“በምሥራቀ ፀሐይ የምትመሰየሚው፤ እንደ መብረቅ ኃያል የሆነውን ጌታን የወለድሽ፣ ረቂቅ ምሥጢርን የምትችዪ፤ እንደ ፊደል ባለ ብዙ ዘር [ሆሄያት] የሆንሽ፣ ወንጌልን የወለድሽ፥ ነበልባለ እሳትን [ክርስቶስን] የተሸከምሽ ፤ በጽጌ ረዳ አምሳል የምትመሰየሚው ቅድስት ማርያም ሆይ! የዓለሙን እንግዳ ፈጣሪን የወለድሽ፤ ከፍዳ ሞት የምታድኚ፤ የወይን ሐረግ የወይን ዐፀድ [ተክል] አንቺ ነሽ።”
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇
@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
ሀሳብ አስተያየት ካለ @kingo08bot
❤1
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
እንኳን #አስቀድሞ_በማንም_ላይ_ርኅራኄ የሌለው (ንፉግ) ለነበረ፤ በሕልሙ እግዚአብሔር በሳየው ራእይ ተመልሶ ስለ ምጽዋት ሲል ያለው ንብረት በሙሉ ከሰጠ በኋላ እራሱ ለሸጠ ለቀራጭች አለቃ ለነበረ #ለቅዱስ_አንጢላርዮስ_ለዕረፍት_በዓል መታሰቢያ፣ #በሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት አምና ለተጠመቀች ያለ ደም መፍሰሰ ሰማዕት ለሆነች #ለቅድስት_ጤቅላ (ቴክላ) ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ #ለቅዱስ_ኤዎስጣቴዎስ_ለሁለት_ልጆቹና_ለሚስቱም ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከመድኃኒታችን ከስቅለቱ #ከመድኃኔዓለም ከወራዊ ከመታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
እንኳን #አስቀድሞ_በማንም_ላይ_ርኅራኄ የሌለው (ንፉግ) ለነበረ፤ በሕልሙ እግዚአብሔር በሳየው ራእይ ተመልሶ ስለ ምጽዋት ሲል ያለው ንብረት በሙሉ ከሰጠ በኋላ እራሱ ለሸጠ ለቀራጭች አለቃ ለነበረ #ለቅዱስ_አንጢላርዮስ_ለዕረፍት_በዓል መታሰቢያ፣ #በሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት አምና ለተጠመቀች ያለ ደም መፍሰሰ ሰማዕት ለሆነች #ለቅድስት_ጤቅላ (ቴክላ) ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ #ለቅዱስ_ኤዎስጣቴዎስ_ለሁለት_ልጆቹና_ለሚስቱም ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከመድኃኒታችን ከስቅለቱ #ከመድኃኔዓለም ከወራዊ ከመታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
መስከረም ፳፯ (27)
በዚህችም ቀን ያለ ደም ማፍሰስ ሰማዕት የሆነች ቅድስት ጤቅላ አረፈች።
የዚህች ቅድስት ወላጆቿ ከመቄዶንያ ሰዎች ውስጥ ባለጸጎች ናቸው እርሷንም እንደ ሀገራቸው ባህል በተግሣጽ በምክር አሳደጓት እነርሱ ጣዖትን የሚያመልኩ ናቸውና። ሐዋርያ ጳውሎስም ወደዚህች አገር በደረሰ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አምስትን ሊአስተምር ጀመረ ዐውቀው ድኆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት ለእነርሱ ናትና።
ይህንንና ይህን የመሰለውን በሰማች ጊዜ ያለ መብልና መጠጥ ሦስት ቀን ኖረች። ከዚህም በኋላ ወደ ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ ሔደች። እርሱም በደስታ ተቀብሎ የክርስቶስን ሃይማኖት አስተማራት።
በማግሥቱም እናቷ ከቅዱስ ጳውሎስ ዘንድ አብራ ተቀምጣ አገኘቻት ከዚያም ወደ መኰንን ሒዳ ልጇን ክርስቲያን እንደሆነች ከሰሰቻት። መኰንኑም ከቅዱስ ጳውሎስ ጋራ እንዲያመጧት አዘዘ አስቀድመው ቅዱስ ጳውሎስን ወደ እሳት እንዲወረውሩት አዘዘ እግዚአብሔርም አዳነው።
መኰንኑም ቅድስት ጤቅላን ወደ እሳት እንዲወረውሩዋት አዘዘ። በዚያን ጊዜ በክርስቶስ ማዕተብ ራሷን አማትባ ራስዋን በራስዋ ወደ እሳት ወረወረች ማንም ያያት ሳይኖር ከእሳት ውስጥ ወጥታ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሔደች የራስዋን ጠጒር ቆርጣ ወገቧንም ታጥቃ ቅዱስ ጳውሎስን ተከተለችው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ አንበሳና ድብ ከሚያድርበት ጨመራት እነርሱም ሰገዱላትና የእግሮቿን ትቢያ ላሱ። መኰንኑና ወገኖቹ ይህን አይተው በእግዙአብሔእ አመኑ ቅድስት ጤቅላም ቅዱስ ጳውሎስን አገልግላ በሰላም አረፈች።
በረከታቸው ይደርብን! አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@efeson_2
🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋
መስከረም ፳፰ /28/
በዚች ቀን ቅድስት ሶስና አረፈች
ይህችውም ቅድስት የባዕለ ጸጋ ኢዮአቄም ሚስት የኾነች፣ የቅዱስ ሙሴን ሕግ የተማረችና ደጋግ የኾኑን አባትና እናቷም በመልካም ያሳደጓት፣ የኦሪትንም ሕግ ያስተማሯት አስተዋይ ቅድስት ናት።
በዚያም በባልዋ ቤት ብዙ እስራኤላውያን ይመጡ ነበርና የዚያም፡ቤት ቤተኛ ከኾኑት ኹለት የአይሁድ ረበናት ይገኙበታል። እኒህም ኹለት ግብዞች ደጋግመው ሶስናን አዩአት በዚህም ጸላኤ ሰናያት በልቡናቸው አደረና ዐይናቸው ኹሉ ግልብጥብጥ ብሎ በክፉ ሥራ ፈቀዷት።
አንድ እለት ከአትክልት ሥፍራ ዘግታ ስትታጠብ አገልጋዮቿን መልእክት ልካቸው እንደወጡ እኒህ ኹለት ክፉዎች ከተደበቁበት ወጥተው ፈቃዳችንን ፈጽሚ ካልፈጸምሽ ስታመነዝር ይዘናታል ብለን እንከስሻለን አሏት። እርሷም ከእጃቸው ማምለጥ አትችልምና ወደ ሰማይ አንጋጣ ቸሩን አምላክ በጽኑዕ ያድናት ዘንድ ተማጸነች።
እርሷም ፈቃዳቸውን ብፈጽምም ኾነ ባልፈጽም እሞታለሁ፣ ከፈጸምኹ ግን ከነርኲሰት ነውና የምሞተው ብላ አስባ እንደማትፈጽም ነገረቻቸው። ሦስቱም ሲጮኹ ሕዝብ ሲሰበሰብ ስታመነዝር አገኘናት አሉና ከሰሷት። እርሷም እንዲህ ያለ ነውር ተሰምቶባት አይታወቅምና ዘመዶቿ አፈሩ። በኋላም ለፍርድ በአደባባይ አቀረቧትና አየን ያሉትን ተናገሩ።
ሊወግሯትም ብለው ሲኼዱ ታላቁ ነብይ ቅዱስ ዳንኤል ቆይ እኔ ልመርምራቸው ብሎ አራርቆ ቢመረምራቸው አንዱ ከኮክ ዛፍ ሥር ነው ያየኋት፣ አንዱ ደግሞ ከሮማን ዛፍ ሥር ነው አለ። በዚህም ተለያይተዋልና ሕዝቡ እኒህን ኹለት ግብዝ ክፉ ሰዎች ገደሏቸው፣ ቅድስት ሶስናም በቸሩ አምላክ ታላቅ ነቢይ እርዳታ ዳነች።
በረከታቸው ይደርብን! አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@efeson_2
🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋
❤1🔥1
🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር ለተሻገሩት ለታላቁ ጻድቅ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ደቀ መዝሙር ለሆኑ #በኤራትራና_በኢትዮጵያ_ገዳም ለመሰረቱ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አቡሳዲ_ለዕረፍታቸው በዓልና #ከተሰዓቱ_ቅዱሳን አንዱ ለሆኑት #ለአቡነ_ይስሐቅ_ተአምር_ሰረተው #አቡነ_ገሪማ ተብለው እንዳጠሩ ላተረጉበት ቀን መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር ለተሻገሩት ለታላቁ ጻድቅ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ደቀ መዝሙር ለሆኑ #በኤራትራና_በኢትዮጵያ_ገዳም ለመሰረቱ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አቡሳዲ_ለዕረፍታቸው በዓልና #ከተሰዓቱ_ቅዱሳን አንዱ ለሆኑት #ለአቡነ_ይስሐቅ_ተአምር_ሰረተው #አቡነ_ገሪማ ተብለው እንዳጠሩ ላተረጉበት ቀን መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
@efeson_2
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
🔥2