COFFEE MAY ENTER THE U.S. DUTY-FREE? ☕️
ቡና ከቀረጥ ነፃ ወደ አሜሪካ ሊገባ ይችላል? ☕️
📢 የዩናይትድ ስቴትስ የንግድ ሚኒስትር ሃዋርድ ሉትኒክ ዋሽንግተን ከአምራች ሀገራት ጋር የንግድ ስምምነቶችን ከፈረመች በአገሯ ውስጥ ላልተመረቱ የግብርና ምርቶች ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል ።
📢 U.S. Commerce Secretary Howard Lutnick has revealed the possibility of duty-free imports for agricultural products not grown domestically – including coffee and cocoa – if Washington signs trade agreements with producing countries.
🔎 Speaking on CNBC’s “Squawk Box”, Lutnick stated:
“If a country produces a crop that the U.S. doesn’t grow, they could export it to the U.S. at a 0% tariff. Coffee and cocoa are perfect examples.”
📄 The new trade agreement between the U.S. and Indonesia has already laid the foundation for this policy, potentially allowing tropical products like coffee to be imported tariff-free in the future. However, countries without such agreements – like Brazil – still face a planned 50% tariff starting August 1.
📉 This could heavily impact Brazil, which currently supplies one-third of the U.S.’s coffee consumption, forcing farmers and exporters to find alternative markets to avoid oversupply and price drops.
🔥 What does this mean for Ethiopian coffee?
With the potential for duty-free access, Ethiopian could become a key supplier to the U.S. market.
source: https://www.reuters.com/.../coffee-cocoa-could-be-exempt.../
ቡና ከቀረጥ ነፃ ወደ አሜሪካ ሊገባ ይችላል? ☕️
📢 የዩናይትድ ስቴትስ የንግድ ሚኒስትር ሃዋርድ ሉትኒክ ዋሽንግተን ከአምራች ሀገራት ጋር የንግድ ስምምነቶችን ከፈረመች በአገሯ ውስጥ ላልተመረቱ የግብርና ምርቶች ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል ።
📢 U.S. Commerce Secretary Howard Lutnick has revealed the possibility of duty-free imports for agricultural products not grown domestically – including coffee and cocoa – if Washington signs trade agreements with producing countries.
🔎 Speaking on CNBC’s “Squawk Box”, Lutnick stated:
“If a country produces a crop that the U.S. doesn’t grow, they could export it to the U.S. at a 0% tariff. Coffee and cocoa are perfect examples.”
📄 The new trade agreement between the U.S. and Indonesia has already laid the foundation for this policy, potentially allowing tropical products like coffee to be imported tariff-free in the future. However, countries without such agreements – like Brazil – still face a planned 50% tariff starting August 1.
📉 This could heavily impact Brazil, which currently supplies one-third of the U.S.’s coffee consumption, forcing farmers and exporters to find alternative markets to avoid oversupply and price drops.
🔥 What does this mean for Ethiopian coffee?
With the potential for duty-free access, Ethiopian could become a key supplier to the U.S. market.
source: https://www.reuters.com/.../coffee-cocoa-could-be-exempt.../
በስርዓተ ጾታ እና በአየር ንብረት ላይ በተዘጋጀው የትግበራ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ
ሐምሌ 29/2017
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የስርዓተ ጾታና አየር ንብረት ላይ በተዘጋጀ የትግበራ ዕቅድ ላይ የተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላትን በመጋበዝ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም ባለስልጣኑን ጨምሮ የሲቪል ማኅበራት ድርጅት፣ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የምርምር ተቋማት ተሳትፈውበታል፡፡
የውይይቱን መድረክ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሠፊሳ አባቡ በንግግር ከፍተዋል፡፡ በንግግራቸውም የተዘጋጀው ሰነድ ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነና ዓለማቀፍ የስርዓተ ጾታና የአየር ንብረት ነባራዊ ሁኔታዎችን በዳሰሰ መልኩ እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡ ሰነዱ ቢዘጋጅም ለተግባራዊነቱ በቂ ዝግጅት ማድረግ ስለሚገባ ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለማግኘት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ለማድረግ መድረኩ እንደተጠራ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለታቀደው እቅድ በተፈለገው መጠን፣ ጥራትና ጊዜ መተግበር የተለያዩ የሚመለከታቸው ፕሮጀክቶች ትብብር እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል፡፡ የስርዓተ ጾታና አየር ንብረት ሁኔታ ለባለስልጣን መስሪያቤቱ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ገልጸው በዚህም መሠረት ባለስልጣኑ ለዕቅዱ መፈጸም ስኬት እንደሚተጋ ተናግረዋል፡፡ በስተመጨረሻም የታዳሚው በተለይ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲኖር አሳስበዋል፡፡
ዕቅዱን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የስርዓተ ጾታና እንክብካቤ ተመራማሪ የሆኑት ወ/ሮ ለምለም አበበ አቅርበዋል፡፡ በመንደርደሪያቸውም ዕቅዱ ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተዘጋጀው ሰነድ ግቦችና ዓላማዎችን ሲገልጹም የጾታ እኩልነትን፣ የአየር ንብረት መላመድ፣ የረጅም ጊዜ የከባቢያዊ ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ ቀጣይነትን በማሻሻል የኢትዮጵያ የቡና ሴክተር ችግሮችን ተቋቋሞ የማለፍ አቅምን የማጎልበት ግብን ያነገበ እንደሆነ ካቀረቡት ሰነድ ማወቅ ተችሏል፡፡ ዝርዝር ዓላማውንም ሲያቀርቡ ከጾታ እኩልነት፣ ከአየር ንብረት መቋቋም፣ ከአቅም ግንባታ፣ ከእሴት ሰንሰለት ልማት፣ ከኑሮ ገቢ ልማት፣ ከተቋማት መጠናከር ጋር በተያየዘ በርካታ ዝርዝር ዓላማዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡
በቦታው ተገኝተን እንደተገነዘብነውም ዕቅዱ በይዘት የጾታ ሃላፊነት መወጣት አቅም ማዳበር፣ አየር ንብረትን የሚቋቋሙ የግብርና ልምዶች፣ የሀብትና አገልግሎት ተደራሽነት ማሳደግ፣ የፋይናንስ አገልግሎት አካታችነት ማሻሻል፣ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቡና ልማት፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ተቋማትን ማጠናከርና የፖሊሲ ሁኔታ፣ ምርምሮችን ማካሄድና ዕውቀት ማዳበር፣ ማኅበረሰብን መሠረት ያደረገ የዕለት ገቢና ችግሮችን ተቋቁሞ ማለፍ ላይ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት፣ የአየር ንብረት መረጃና ቅድመ መከላከል ማስጠንቀቂያ ስርዓቶች፣የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ትብብር እና የዕውቀት ሽግግር፣ ቁጥጥር ክትትል እና የመማማር ማዕቀፈ ማዘጋጀት፣ የሚጠበቁ ውጤቶች፣ ለተፈጻሚነቱ ባለድርሻ አካላቱ እነማን እንደሆኑና ሚናቸው፣ ለዕቅዱ መፈጸም የሚጠይቀው ወጪ ያካተተ እንደሆነ ለመረዳት ችለናል፡፡
የትግበራ ዕቅዱ ከቀረበም በኋላ በቡድን ውይይት ሀሳቦች መንጭተው ውይይት ተካሂዶባቸው የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
ዕቅዱ በስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን የገንዘብ ድጋፍ ኦስሪያ በተባለ ድርጅት ለቡናና ሻይ ባለስልጣን ግብአትነት የተዘጋጀ እንደሆነ ከመድረኩ አዘጋጅ ክፍል ለማወቅ ተችሏል፡
ሐምሌ 29/2017
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የስርዓተ ጾታና አየር ንብረት ላይ በተዘጋጀ የትግበራ ዕቅድ ላይ የተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላትን በመጋበዝ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም ባለስልጣኑን ጨምሮ የሲቪል ማኅበራት ድርጅት፣ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የምርምር ተቋማት ተሳትፈውበታል፡፡
የውይይቱን መድረክ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሠፊሳ አባቡ በንግግር ከፍተዋል፡፡ በንግግራቸውም የተዘጋጀው ሰነድ ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነና ዓለማቀፍ የስርዓተ ጾታና የአየር ንብረት ነባራዊ ሁኔታዎችን በዳሰሰ መልኩ እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡ ሰነዱ ቢዘጋጅም ለተግባራዊነቱ በቂ ዝግጅት ማድረግ ስለሚገባ ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለማግኘት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ለማድረግ መድረኩ እንደተጠራ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለታቀደው እቅድ በተፈለገው መጠን፣ ጥራትና ጊዜ መተግበር የተለያዩ የሚመለከታቸው ፕሮጀክቶች ትብብር እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል፡፡ የስርዓተ ጾታና አየር ንብረት ሁኔታ ለባለስልጣን መስሪያቤቱ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ገልጸው በዚህም መሠረት ባለስልጣኑ ለዕቅዱ መፈጸም ስኬት እንደሚተጋ ተናግረዋል፡፡ በስተመጨረሻም የታዳሚው በተለይ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲኖር አሳስበዋል፡፡
ዕቅዱን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የስርዓተ ጾታና እንክብካቤ ተመራማሪ የሆኑት ወ/ሮ ለምለም አበበ አቅርበዋል፡፡ በመንደርደሪያቸውም ዕቅዱ ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተዘጋጀው ሰነድ ግቦችና ዓላማዎችን ሲገልጹም የጾታ እኩልነትን፣ የአየር ንብረት መላመድ፣ የረጅም ጊዜ የከባቢያዊ ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ ቀጣይነትን በማሻሻል የኢትዮጵያ የቡና ሴክተር ችግሮችን ተቋቋሞ የማለፍ አቅምን የማጎልበት ግብን ያነገበ እንደሆነ ካቀረቡት ሰነድ ማወቅ ተችሏል፡፡ ዝርዝር ዓላማውንም ሲያቀርቡ ከጾታ እኩልነት፣ ከአየር ንብረት መቋቋም፣ ከአቅም ግንባታ፣ ከእሴት ሰንሰለት ልማት፣ ከኑሮ ገቢ ልማት፣ ከተቋማት መጠናከር ጋር በተያየዘ በርካታ ዝርዝር ዓላማዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡
በቦታው ተገኝተን እንደተገነዘብነውም ዕቅዱ በይዘት የጾታ ሃላፊነት መወጣት አቅም ማዳበር፣ አየር ንብረትን የሚቋቋሙ የግብርና ልምዶች፣ የሀብትና አገልግሎት ተደራሽነት ማሳደግ፣ የፋይናንስ አገልግሎት አካታችነት ማሻሻል፣ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቡና ልማት፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ተቋማትን ማጠናከርና የፖሊሲ ሁኔታ፣ ምርምሮችን ማካሄድና ዕውቀት ማዳበር፣ ማኅበረሰብን መሠረት ያደረገ የዕለት ገቢና ችግሮችን ተቋቁሞ ማለፍ ላይ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት፣ የአየር ንብረት መረጃና ቅድመ መከላከል ማስጠንቀቂያ ስርዓቶች፣የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ትብብር እና የዕውቀት ሽግግር፣ ቁጥጥር ክትትል እና የመማማር ማዕቀፈ ማዘጋጀት፣ የሚጠበቁ ውጤቶች፣ ለተፈጻሚነቱ ባለድርሻ አካላቱ እነማን እንደሆኑና ሚናቸው፣ ለዕቅዱ መፈጸም የሚጠይቀው ወጪ ያካተተ እንደሆነ ለመረዳት ችለናል፡፡
የትግበራ ዕቅዱ ከቀረበም በኋላ በቡድን ውይይት ሀሳቦች መንጭተው ውይይት ተካሂዶባቸው የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
ዕቅዱ በስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን የገንዘብ ድጋፍ ኦስሪያ በተባለ ድርጅት ለቡናና ሻይ ባለስልጣን ግብአትነት የተዘጋጀ እንደሆነ ከመድረኩ አዘጋጅ ክፍል ለማወቅ ተችሏል፡
ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በተደረገባቸው ወረዳዎች የስኬታማነት መረጃዎች በሚዲያ ባለሙያዎች በመሰባሰብ ላይ ይገኛል
መቱ
ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም
የEU-Desira ፕሮጀክት ተግባራዊ በሆነባቸው ወረዳዎች በተጨባጭ በተገኙ ውጤቶችና የፕሮጀክቱን ስኬታማነት በተመለከተ በሚዲያ ባለሙያዎች በኩል መረጃዎች በመሰባሰብ ላይ ይገኛል ።
በህብረት ሀገራቱ የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግለት ይኽው ፕሮጀክት በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል በኢሉአባቦር እና በቡኖ በደሌ ዞኖች በስድስት ወረዳዎች ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ሲሆን በዋናነትም ዘላቂ የቡና ልማት ስራው እና የደን ስነምህዳራዊ ጥበቃው በተቀናጀ የመሬት ማኔጅመንትና የአየር ንብረት አጠባበቅ ስራዎች በአግባቡ መደገፍ ዋነኛው ትኩረቱ መሆኑን ክቡር አቶ ታጋይ ኑሩ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክ/ዋና ዳይሬክተር እና የልማት ዘርፍ ሀላፊ ጠቁመዋል ።
የመሬት መራቆት እና የጫካ ምንጣሮ የአፈር መሸርሸርን ከማስከተሉም በተጨማሪ የአካባቢያዊ ጥበቃ ስራን እንደሚጎዳ እና ዘላቂነት የሌለው የጫካ ቡና ልማት እንዲፈጠር ምክንያት ይሆናል ያሉት ምክ/ዋና ዳይሬክተሩ፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ በስፋት የሚገኘው የጫካ ቡና በአለም አቀፍ ደረጃ በተመዘገበው የያዮ ጥብቅ ደን ውስጥ የሚለማ በመሆኑ የአካባቢው ማህበረሰብ ከጫካውም ሆነ ከቡና ልማቱ ማግኘት ያለበትን ጥቅም በአግባቡ ማግኘት እንዲችል ከፍተኛ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል ።
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ እና በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፈቃዱ ደፈረስ በኩላቸው ባለስልጣን መ/ቤቱ በፕሮጀክቱ በኩል
በርካታ ድጋፎች እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸው ስለ ፕሮጀክቱ የበለጠ ግንዛቤ ለመፍጠር እና በተጨባጭ ስለተገኙ ስኬታማ ስራዎች ከሚዲያ አካላት ጋር በመሆን መረጃዎችን በማሰባሰብ ለህዝብ እና ባለድርሻ አካላት ተደራሽ የማድረግ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል ።
በተለያየ ሁኔታ የቡናውን ዘርፍ የሚደግፉ በርካታ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የገለፁት አቶ ፍቃዱ የEU-Desira ፕሮጀክት ከባለስልጣን መ/ቤቱ ጋር በመቀናጀት አነስተኛ ደረጃ አርሶአደሮችን፣ሴቶችን እና ወጣቶችን በመደገፍ ባስገኘው ለውጥ እና ለቡናው ሴክተር ውጤታማነት በአበረከተው አስተዋጽኦ ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ስራ እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ቡድን በቦታው ተገኝቶ ዘግቧል።
መቱ
ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም
የEU-Desira ፕሮጀክት ተግባራዊ በሆነባቸው ወረዳዎች በተጨባጭ በተገኙ ውጤቶችና የፕሮጀክቱን ስኬታማነት በተመለከተ በሚዲያ ባለሙያዎች በኩል መረጃዎች በመሰባሰብ ላይ ይገኛል ።
በህብረት ሀገራቱ የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግለት ይኽው ፕሮጀክት በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል በኢሉአባቦር እና በቡኖ በደሌ ዞኖች በስድስት ወረዳዎች ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ሲሆን በዋናነትም ዘላቂ የቡና ልማት ስራው እና የደን ስነምህዳራዊ ጥበቃው በተቀናጀ የመሬት ማኔጅመንትና የአየር ንብረት አጠባበቅ ስራዎች በአግባቡ መደገፍ ዋነኛው ትኩረቱ መሆኑን ክቡር አቶ ታጋይ ኑሩ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክ/ዋና ዳይሬክተር እና የልማት ዘርፍ ሀላፊ ጠቁመዋል ።
የመሬት መራቆት እና የጫካ ምንጣሮ የአፈር መሸርሸርን ከማስከተሉም በተጨማሪ የአካባቢያዊ ጥበቃ ስራን እንደሚጎዳ እና ዘላቂነት የሌለው የጫካ ቡና ልማት እንዲፈጠር ምክንያት ይሆናል ያሉት ምክ/ዋና ዳይሬክተሩ፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ በስፋት የሚገኘው የጫካ ቡና በአለም አቀፍ ደረጃ በተመዘገበው የያዮ ጥብቅ ደን ውስጥ የሚለማ በመሆኑ የአካባቢው ማህበረሰብ ከጫካውም ሆነ ከቡና ልማቱ ማግኘት ያለበትን ጥቅም በአግባቡ ማግኘት እንዲችል ከፍተኛ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል ።
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ እና በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፈቃዱ ደፈረስ በኩላቸው ባለስልጣን መ/ቤቱ በፕሮጀክቱ በኩል
በርካታ ድጋፎች እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸው ስለ ፕሮጀክቱ የበለጠ ግንዛቤ ለመፍጠር እና በተጨባጭ ስለተገኙ ስኬታማ ስራዎች ከሚዲያ አካላት ጋር በመሆን መረጃዎችን በማሰባሰብ ለህዝብ እና ባለድርሻ አካላት ተደራሽ የማድረግ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል ።
በተለያየ ሁኔታ የቡናውን ዘርፍ የሚደግፉ በርካታ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የገለፁት አቶ ፍቃዱ የEU-Desira ፕሮጀክት ከባለስልጣን መ/ቤቱ ጋር በመቀናጀት አነስተኛ ደረጃ አርሶአደሮችን፣ሴቶችን እና ወጣቶችን በመደገፍ ባስገኘው ለውጥ እና ለቡናው ሴክተር ውጤታማነት በአበረከተው አስተዋጽኦ ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ስራ እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ቡድን በቦታው ተገኝቶ ዘግቧል።
በኪሎ 30 ሺህ 204 ዶላር የተሸጠው ቡና
https://www.upi.com/Top_News/World-News/
ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም
የፓናማ ምርጥ የሚል ስያሜ በተሰጠዉ የ2025 የአለም አቀፍ የፓናማ የቡና ጨረታ ላይ ምንጩ ከኢትዮጵያ የሆነው የጌሻ ቡና በኪሎ 30 ሺህ 204 ዶላር በመሸጥ አዲስ የአለም ክብረ ወሰን ሰብሯል።
የፓናማ ልዩ ቡና ማህበር የሚያዘጋጀው ጨረታ በፈረንጆቹ 1990 የተጀመረ ሲሆን በ2004 አለም አቀፍ እውቅናን በማግኘት በአሁኑ ሰዓት አለም አቀፍ ገዢዎችን በበይነ መረብ በማሳተፍ የሚካሄድ የፓናማ የቡና ጨረታ ሆኗል፡፡
ፓናማ የቡና ምርቶቿን ለማስተዋወቅ በምትጠቀምበት በዚህ ጨረታ ላይ በዚህ ዓመት ከቻይና፣ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ዱባይ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬት የተውጣጡ ተጫራጮች ተሳትፈዋል።
በጨረታውም ከሃሲዬንዳ ላ ኤስሜራልዳ እርሻ የተገኘው ‘የታጠበ ጌሻ’ የተባለው የቡና ዝርያ ለጨረታ ከቀረቡ 50 የቡና ዝርያዎች በኪሎ 30 ሺህ 204 ዶላር ለዱባይ ገዢ በመሸጥ ክብረ ወሰንን ይዟል።
ጌሻ ቡና ምንጩ ኢትዮጵያ የሆነው የአረቢካ ቡና ዝርያ መሆኑን ጠቅሶ የዘገበው ዩ ፒ አይ ነው።
https://www.upi.com/Top_News/World-News/
ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም
የፓናማ ምርጥ የሚል ስያሜ በተሰጠዉ የ2025 የአለም አቀፍ የፓናማ የቡና ጨረታ ላይ ምንጩ ከኢትዮጵያ የሆነው የጌሻ ቡና በኪሎ 30 ሺህ 204 ዶላር በመሸጥ አዲስ የአለም ክብረ ወሰን ሰብሯል።
የፓናማ ልዩ ቡና ማህበር የሚያዘጋጀው ጨረታ በፈረንጆቹ 1990 የተጀመረ ሲሆን በ2004 አለም አቀፍ እውቅናን በማግኘት በአሁኑ ሰዓት አለም አቀፍ ገዢዎችን በበይነ መረብ በማሳተፍ የሚካሄድ የፓናማ የቡና ጨረታ ሆኗል፡፡
ፓናማ የቡና ምርቶቿን ለማስተዋወቅ በምትጠቀምበት በዚህ ጨረታ ላይ በዚህ ዓመት ከቻይና፣ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ዱባይ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬት የተውጣጡ ተጫራጮች ተሳትፈዋል።
በጨረታውም ከሃሲዬንዳ ላ ኤስሜራልዳ እርሻ የተገኘው ‘የታጠበ ጌሻ’ የተባለው የቡና ዝርያ ለጨረታ ከቀረቡ 50 የቡና ዝርያዎች በኪሎ 30 ሺህ 204 ዶላር ለዱባይ ገዢ በመሸጥ ክብረ ወሰንን ይዟል።
ጌሻ ቡና ምንጩ ኢትዮጵያ የሆነው የአረቢካ ቡና ዝርያ መሆኑን ጠቅሶ የዘገበው ዩ ፒ አይ ነው።
ድንቅ እና የተለያየ አይነት የቡና ባህላችን!!
ቀደም ሲል የጋምቤላ ክልል የቡና አፈላል ስነስርዓት መቃኘታችን ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ተወዳጅ እና ባህላዊ የሆነውን የቡና ስነስርዓት እንመልከት። የምታውቁትን አካፍሉን እናስተናግዳለን።
በቦረና - ተወዳጁ ቡነ ቀላ
***
ቦረናዎች የተቆላ ቡና ፍሬን ከትኩስ ወተት እና ቅቤ ጋር አዋህደው የሚያዘጋጁት ቡነ ቀላ የተሰኘ ተወዳጅ መጠጥ አላቸው፡፡
ቡነ ቀላ በኦሮሞ ባህል መሰረት ሰዎች የሚመራረቁበት ሲሆን፤ የቦረና የማንነት መገለጫ ከሆኑ ስርዓቶች መካከል አንደኛው
ነው፡፡
ሰዎች ሲጣሉ ለማስታረቅ እና እናቶች ሲወልዱ ቡነ ቀላ ተዘጋጅቶ የምርቃት ስነ-ስርዓት ይከወናል፡፡
ቡነ ቀላ በገዳ ስርዓት ወቅት፣ በባህላዊ ክንዋኔዎች ወቅት እንዲሁም በማንኛውም ጊዜ ተፈልቶ እንደሚጠጣ የአካባቢው ሽማግሌዎች ያስረዳሉ።
ቡነ ቀላ እንግዳም ሲመጣ የሚዘጋጅ ሲሆን፤ ቦረናዎች ቡነ ቀላን ለሚቀርብለት ሰው ያላቸውን አክብሮት የሚገልጹበትም ነው፡፡
በቦረና ባህል ቡና ትልቅ ክብር እንዳለውም ይነገራል፡፡
ረጅም ጉዞ የሚጓዝ ሰው ካለ የተዘጋቸውን ቡነ ቀላ ከመነሻው እስከመድረሻው ጉንጩ ላይ ይዞት እንዲሄድም ይደረጋል፤ ብርታት ይሰጣልና።
በቦረና ባህል መሰረት ቡነ ቀላ የቀረበለት ሰው የሚመልሰው ትንሽ አስተርፎ ነው። የቀረውም ቡነ ቀላ ለታታናሾች እና ለሕፃናትም እንደሚሰጥ የአካባቢው አባቶች ይናገራሉ።
ይህም መከባበርን እና ስርዓትን ለማስተማር እንደሚረዳ በርካቶች ያስረዳሉ።
ቀደም ሲል የጋምቤላ ክልል የቡና አፈላል ስነስርዓት መቃኘታችን ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ተወዳጅ እና ባህላዊ የሆነውን የቡና ስነስርዓት እንመልከት። የምታውቁትን አካፍሉን እናስተናግዳለን።
በቦረና - ተወዳጁ ቡነ ቀላ
***
ቦረናዎች የተቆላ ቡና ፍሬን ከትኩስ ወተት እና ቅቤ ጋር አዋህደው የሚያዘጋጁት ቡነ ቀላ የተሰኘ ተወዳጅ መጠጥ አላቸው፡፡
ቡነ ቀላ በኦሮሞ ባህል መሰረት ሰዎች የሚመራረቁበት ሲሆን፤ የቦረና የማንነት መገለጫ ከሆኑ ስርዓቶች መካከል አንደኛው
ነው፡፡
ሰዎች ሲጣሉ ለማስታረቅ እና እናቶች ሲወልዱ ቡነ ቀላ ተዘጋጅቶ የምርቃት ስነ-ስርዓት ይከወናል፡፡
ቡነ ቀላ በገዳ ስርዓት ወቅት፣ በባህላዊ ክንዋኔዎች ወቅት እንዲሁም በማንኛውም ጊዜ ተፈልቶ እንደሚጠጣ የአካባቢው ሽማግሌዎች ያስረዳሉ።
ቡነ ቀላ እንግዳም ሲመጣ የሚዘጋጅ ሲሆን፤ ቦረናዎች ቡነ ቀላን ለሚቀርብለት ሰው ያላቸውን አክብሮት የሚገልጹበትም ነው፡፡
በቦረና ባህል ቡና ትልቅ ክብር እንዳለውም ይነገራል፡፡
ረጅም ጉዞ የሚጓዝ ሰው ካለ የተዘጋቸውን ቡነ ቀላ ከመነሻው እስከመድረሻው ጉንጩ ላይ ይዞት እንዲሄድም ይደረጋል፤ ብርታት ይሰጣልና።
በቦረና ባህል መሰረት ቡነ ቀላ የቀረበለት ሰው የሚመልሰው ትንሽ አስተርፎ ነው። የቀረውም ቡነ ቀላ ለታታናሾች እና ለሕፃናትም እንደሚሰጥ የአካባቢው አባቶች ይናገራሉ።
ይህም መከባበርን እና ስርዓትን ለማስተማር እንደሚረዳ በርካቶች ያስረዳሉ።