Ethiopian Civil Service University
10K subscribers
330 photos
5 files
23 links
The first public service university in Ethiopia.
Download Telegram
ኢሲሰዩ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት የምርምር አስተችቶት አውደጥናት አካሄደ
________________
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የሁለት ቀናት የምርምር አስተችቶት አውደ-ጥናት ከጥር 23-24 /2015 ዓ.ም በአባይ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይም የተለያዩ የፌዴራል ፣ የክልልና የሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የሴክተር መስሪያ ቤት ሀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

ዶ/ር ተመስገን ቡርቃ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በአውደ ጥናቱ መክፍቻ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የማስተማር፣ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮ የሚያከናውኗቸው ተግባራት የሀገሪቱን ችግር የሚፈቱ መሆን እንዳለባቸው በመጠቆም የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲም ባለፉት ሃያ ስምንት ዓመታት በትምህርት በስልጠናና የማማከር አገልግሎት እንዲሁም በርካታ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችም ሲያከናውን መቆየቱን አመልክተዋለ፡፡ በአሁኑ ወቅትም ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዩኒቨርሲቲ ስር የተመደበ በመሆኑ ይህን ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን ማከናወኑን የበለጠ አስጠብቆ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ያወሱት ዶ/ር ተመስገን ከእነዚህ ችግሮች መካከል አንዱ የሙስና መንሰራፋት እንደሆነ ጠቁመው ዜጎች መብቶቻቸውን እና አገልግሎትን በገንዘብ ሊገዙ የሚገደዱባቸው እውነቶች መኖራቸው ጠቁመዋል፡፡ ሙሰኝነት መንግስት ሙሉ አቅሙን በልማትና በሀገር ግንባታ ላይ እንዳያደርግ ችግር እየፈጠረ ይገኛል፡፡ ይህ ችግር የሚፈታው ከመንግስት ቁርጠኝነት በተጨማሪ የመላው ህብረተሰብ ተሳትፎ ሲታከልበት ነው፡፡ ንቅዘት በሀገራችን አጠቃላይ ዕድገት ላይ እያደረሰ ያለው ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር በሀገር ሰላምና በዜጎች ህይወት ላይ ያለው ጫናም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ይህን አደጋ ለመቀልበስ ሳይንሳዊ የሆነ ጥናትና ምርምር መስራት አስፈላጊ በመሆኑ ምሁራንም ጥረት ማድረግ ይጠብቅባቸዋል፡፡ በመሆኑም የዛሬው መድረክ ዓላማና ግብ ንቅዘትን ከየአቅጣጫው በመመርምርና በመተንተን መገለጫዎችን ብቻ ሳይሆን ምክንያቶችንም ጭምር ማሳየት እና የመፍትሄ አቅጣጫንም የሚያመላክት ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ ዩኒቨርሲቲው እያከናወነ ያለው ስራ አበረታች ቢሆንም የበለጠ አጠናክሮ መሄድ ይገባዋል ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲውንና በጥናቱ ሂደት የተሳተፉትን አካላትም አመስግነዋል፡፡

ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ለአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ዩኒቨርሲቲው እንደማንኛውም ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የትምህርት ፣ የስልጠናና ማማከር አገልግሎት እንዲሁም የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ቢሆንም በዋናነት የሲቪል ሰርቪሱን ሰራተኞች በመቀበል የሚያሰለጥን መሆኑ ከሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተለየ ያደርገዋል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስም ከሃምሳ ሺህ በላይ ምሩቃንን ያፈራ እና እነዚህም ምሩቃን በሀገሪቱ የፌዴራልና የክልል ተቋማት እንዲሁም የከተማ መስተዳድሮች ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦን ያበረከቱ እና በማበርከት ላይ የሚገኙ ምሩቃንን አፍርቷል ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ባለው የሃያ ስምንት ዓመታት ዕድሜ ተጠሪነቱ ለተለያዩ ተቋማት ሲቀያየር የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በተደረገው አዲስ አደረጃጀት በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ስር መካተቱን የጠቀሱት ፕ/ር ፍቅሬ ዩኒቨርሲቲው አሁን ባለው ቁመናና ደረጃ አንጻር ከቀደምት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በምርምር ዩኒቨርሲቲነት መመደቡንና በማህበረሰቡ ዘንድም ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራው በመንግስት መስረያ ቤቶች ላይ በመሆኑ የምርምር የትኩረት መስኮቹም የሚነሱት ከመንግስት ነው፡፡ መንግስትም ሃላፊነቶችም የዜጎችን መሰረታዊ ፍላጎቶች ማሟላትና የሰላምና ደህንነት ፍትህን ማስከበር በመሆኑ የምርምር ስራዎቻችን በእነዚህና መሰል ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በምርምር ስራዎቻችንም በርካታ ሥራዎች የተሰሩ መሆናቸውን የጠቀሱት ፕ/ር ፍቅሬ በከተሞች ልማት፣ ሰላም፣ ፍትህ እናሌሎች ልዩ ልዩ ስራዎች መሰራታቸውን አመልክተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሙስናና የመልካም አሰተዳደር ችግሮች ላይ ዩኒቨረሲቲው ምርምር የሚያደርግ ሲሆን በዚህ አውደ ጥናት የሚቀርቡት በዚህ የምርምር ማዕቀፍ ስር የተሰሩት ጥናቶች የችግሩን ጥልቀትና ስፋት የሚያስረዱ በመሆናቸው ተሳታፊዎች በውይይቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪአቸውን አቅርበዋል፡፡

በአውደ-ጥናቱ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር አለማየሁ ደበበ ለአውደጥናቱ ተሳታፊዎች ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሚሰጣቸው የትምህርት፣ የስልጠናና የማማከር እንዲሁም የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎቶች ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ የቆየ መሆኑን አስታውሰው ይህን ትብብርና በቅንጅት የመስራት ባህል የበለጠ ለማጠናከር ጥረት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የዚህ ጥረት አንዱ ማሳያ የሆነው ይህ ዓመታዊ የምርምር አስተችቶት አውደ ጥናት አንዱ ሲሆን በዚህ የምርምር አስተችቶት ላይም በሀገራችን ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም በእያንዳንዳችን የግል ህይወትም ጭምር ሳይቀር ትልቅና አሉታዊ የሆነ ተጽዕኖ በማሳደር ላይ የሚገኙትን ሁለት አደጋዎች ማለትም ሙስና ወይም ንቅዘትን እና ድለላን የዚህ አውደ ጥናት ዐብይ ትኩረት በማድረግና በምርምር በመዳሰስ ለመንግስት የፖሊሲ ግብዐት የሚሆን ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ በማሰብ የምርምር ስራዎቹ ቀርበዋል ብለዋል፡፡

ሙስናን በተመለከተ ዘጠኝ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አለማየሁ እነዚህ ጥናቶችም ትኩረታቸውን ያደረጉት በህዝብ ጤና አገልግሎት፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በፈቃድና ሰነድ ሰጪ አካላት፣ በትራንስፖርት ዘርፍ፣ በመንግስት ግዥ እና ህብረተሰቡ ሙስናን ከመዋጋት አንጻር ያለው ቁርጠኝነትና የመሳሰሉት ርዕሰ ጉዳዮች የተዳሰሱ ሲሆን ድለላን በተመለከተም የተካሄዱ አስር ጥናቶችም አሁን ያለው የድለላ ሥራ በግልና በማህበራዊ ህይወት ላይ “ምን አይነት ተጽዕኖ እያደረሰ ይገኛል?” የሚለው በጥልቀት የተዳደሱና ድለላ በከተማ ቤቶች ፣ ድለላ በግንባታ ፈቃድ አሰጣጥ ሂደት ውስጥ፣ በሰነድና ፈቃድ ሰጪ ተቋማት ውስጥ ያለ ድለላ፣ በብድር አቅርቦትና የፋይናንስ አገልግሎት ውስጥ ያለ ድለላን ወዘተ. ትኩረት ተሰጥቶባቸው የተጠኑ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም ሁለት ቀጥታ የውጪ ኢንቨስትመንት መሳብ ላይ የተሰሩ ጥናቶችም የአውደ ጥናቱ አካል ሲሆኑ በአጠቃላይ ጥናቶቹን ለማከናወንም ከ117 የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መረጃ የተሰበሰበ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በቀረቡት ጥናቶችም ላይ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች በንቃት በመሳተፍ ግብረ መልስ እንዲሰጡበትና ጥናቶቹ የተሻሉ ሆነው ለመንግስት የፖሊስ ግብዐትነት እንዲውሉ ለማስቻል ሁሉም የጉባኤው ተሳታፊዎች በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅረበዋል፡፡
ለአውደ ጥናቱ የተዘጋጁት ጥናቶችም በዩኒቨርሲቲው ምሁራን የተሰሩ ሲሆኑ በተዘጋጀው ትይዩ መድረክ አማካይነት ለተሳታፊዎች ቀርበው በተሳታፊዎች አስተያየት ተሰጥቶባችዋል፡፡
𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗗𝗶𝘀𝗰𝘂𝘀𝘀𝗲𝘀 𝗪𝗶𝘁𝗵 𝗗𝗲𝗹𝗲𝗴𝗮𝘁𝗶𝗼𝗻 𝗳𝗿𝗼𝗺 𝗨𝗦𝗔 𝗘𝗺𝗯𝗮𝘀𝘀𝘆
-------------------------------------------------------------
Ethiopian Civil Service University (ECSU) president Professor Fikre Dessalegn together with vice presidents held a discussion with a delegation from the Embassy of the USA to Ethiopia on different issues and collaboration areas on February 7, 2023 at ECSU Senate Hall.

Professor Fikre Dessalegn, his introduction of the Ethiopian Civil Service University to the members of the delegate noted that ECSU has a unique mission of building the capacity of the public service and in its twenty eighty years old history insistently worked on human resource development of the country by providing specialized educational programs, short term training, research and community services. He also noted that the university has more than fifty thousand alumni who are serving the countries at different regional and federal offices including ministerial levels and now it becomes a university of choice by more than 2 million public servants.

Dr. Abrham Hagose, Director for Institutional Planning Directorate, presented a brief presentation about the establishment, major achievements and focus areas of the university. He also pointed out some identified collaboration areas with the US universities. According to him, some of the identified collaboration areas focus on technical assistance for the newly established English Language Learning Center, expansion of ECSU community Radio FM 100.5, senior professors who will teach and advice in post-graduate and PhD programs, and connecting ECSU with US universities. Professor Fikre also gave further elaboration on the identified collaboration areas.

Ruth Anne Stevens-Kliz, public Affairs Officer US Embassy and Margaret Henning, Senior Learning Advisor, USAID Ethiopia on their part expressed their pleasure in holding the discussion with ECSU and expressed their hope for further discussions and pave the way for establishing collaboration with US Embassy and US universities.
Notice
Extension and Weekend program for 2016 E.C
Click this link to download the Notice
http://www.ecsu.edu.et/notice/ma-letter-2016-ec-extension-and-weekend
ኢሲሰዩ የሰራተኞች ድልድል እያካሄደ ይገኛል
------------------------------------

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ሃያ ስምንት ዓመታት በትምህርት በስልጠናና የማማከር አገልግሎት እንዲሁም በርካታ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችም በማከናወን የሀገሪቱን የሲቪል ሰርቪስ ሴክተር አቅም የመገንባት ተልእኮን በብቃት ሲወጣ የቆየ ሲሆን በዚህም ከሃምሳ ሺህ በላይ በሀገሪቱ የፌዴራልና የክልል ተቋማት እንዲሁም የከተማ መስተዳድሮች ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦን ያበረከቱ እና በማበርከት ላይ የሚገኙ ምሩቃንን አፍርቷል፡፡

ይህን ሀላፊነቱም ከጠቅላይ ሚኒስተትር ጽ/ቤትን ጨምሮ ለተለያዩ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ተጠሪ በመሆን ሲያከናውን የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በተደረገው አዲስ አደረጃጀት ዩኒቨርሲቲው ተጠሪነቱ ለኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር እንዲሆን የተደረገ ሲሆን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ባካሄደው አዲስ የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ እና ምደባ ዩኒቨርሲቲው አሁን ባለው ቁመናና ደረጃ ተገምግሞ ከቀደምትና ከመጀመሪያው ትውልድ (First Generation) ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ምድብ ስር ተመድቧል፡፡

በዚህም መሰረት ዩኒቨርሲቲው የኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ለምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ባዘጋጀው አዲሱ መዋቅር መሰረትም በሶስት ዘርፎች ማለትም አስተዳደርና ልማት ዘርፍ፣ የአካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ እና የምርምርና ትብብር ዘርፍ የተዋቀረ ሲሆን ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ ለመወጣት የሚያስፈልገውን የመዋቅር ስራ አጥናቆ ከየካቲት 13 ቀን 2015ዓ.ም ጀምሮ ሰራተኞችን በመደልደል ላይ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ ክንውንም በአካዳሚክ ዘርፍ ውስጥ በሚገኙ የ69 የሀላፊነት መደቦች ብቃትን መሰረት ያደረገ (merit based ) ግልፅ ውድድር በማድረግ ሀላፊዎችን የመመደብ ስራ አጠናቋል፡፡

በአስተዳደርና የማኔጀመንት ድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ስር የሚገኙ የስራ ሀላፊዎችና የፈጻሚዎች ድልድልም ትልቅ ትኩረት በመስጠት ለሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ የግማሽ ቀን ገለፃ በማካሄድ ሰራተኛዉ ሙሉ በሙሉ በመመሪያ “859/2014 የፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች መዋቅራዊ አደረጃጀት ለዉጥ መሰረት የመንግስት ሠራተኞች የድልድል አፈጻጸም መመሪያ” ላይ ግንዛቤ እንዲኖረዉ ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮችም እንዲብራሩተደርጓል፡፡

በግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት ላይ የኢሲሰዩ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደገለጹት የአቅም ገንቢ ተቋም በመሆናችን ወደፊትም በተለይ የሰራተኞቻችን አቅም ለመገንባት በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የነጻ ትምህርት እድል አሁን ከሚሰጠዉ ቁጥር የበለጠ እንደሚሰጥ ዉጤቱም አሁን ላይ ሲታይ ከዚህ በፊት ትምህርታቸዉን ያጠናቀቁ ሰራተኞቻችን ለድልድሉ ዝግጁ መሆናቸዉ እንደ አንድ እምርታ ይታያል ብለዋል፡፡

በተቀመጠዉ የግዜ ሰሌዳ መሰረት አጠቃላይ የሰራተኞች ድልድል ግንቦት 15/2015 ድረስ ይጠናቀቃል፡፡