በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተከበረ
---------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን “ ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት“ በሚል መሪ ቃል ህዳር 21 ቀን 2016 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ ተማሪዎችን እና ሰራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት እና የጥያቄና መልስ ዉድድር በማድረግ አከበሩ፡፡
የፓናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታዴዎስ ሜንታ እንደተናገሩት ይህ በዐል በዋናነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲከበር የባህል ትዉዉቅ ከመፍጠሩም በላይ የሕዝቦችን ወንድማማችነት በማጠናከር ሕብረ ብሔራዊ አንድት ለማጎልበት ትልቅ ሚና እንደሚኖረዉ በመግለጽ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች እርስ በእርስ ከመተዋወቃቸዉ ባሻገር የእርስ በእርስ መቀራረብ የሚፈጠርበት ትልቅ ኩነት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ ሀገራችን በርካታ መገለጫዎች ያሏቸው ከ80 በላይ ብሄሮች ብሄረሰቦች ያሉባት ሀገር እንደመሆኗ የህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓት በጠንካራ ሂደት መገንባት ለሀገር እድገት እና ሰላም ግንባታ የማይተካ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የፌደራሊዝም ጥናት ትምክርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ግሩም ክንፈሚካኤል ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ በጽሁፋቸው ኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ የተገበረቻቸዉን የመንግስት አወቃቀር በመዳሰስ በአሁን ወቅት እየከተለቸዉ ያለዉን የሕብረ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓት አብራርተዋል፡፡ በቀረበው የመነሻ ፅሁፍ ላይ አሰተያየቶችና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች በመቅረብ ውይይት ተደርጓል፡፡ በማስከተልም በፊደራሊዝም የሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች መካከል የጥያቄና ምልስ ዉድድር ተካሂዷል፡፡
በዓሉን አስመልክቶ ቀደም ሲል በተከናወኑ መርሀ- ግብሮችም በህዳር 14 ቀን 2016 ዓም በጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን ማዕከል የአልባሳት ልገሳ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ በክረምት መርሀ ግብር በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራ ተከናውኗል፡፡
---------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን “ ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት“ በሚል መሪ ቃል ህዳር 21 ቀን 2016 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ ተማሪዎችን እና ሰራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት እና የጥያቄና መልስ ዉድድር በማድረግ አከበሩ፡፡
የፓናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታዴዎስ ሜንታ እንደተናገሩት ይህ በዐል በዋናነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲከበር የባህል ትዉዉቅ ከመፍጠሩም በላይ የሕዝቦችን ወንድማማችነት በማጠናከር ሕብረ ብሔራዊ አንድት ለማጎልበት ትልቅ ሚና እንደሚኖረዉ በመግለጽ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች እርስ በእርስ ከመተዋወቃቸዉ ባሻገር የእርስ በእርስ መቀራረብ የሚፈጠርበት ትልቅ ኩነት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ ሀገራችን በርካታ መገለጫዎች ያሏቸው ከ80 በላይ ብሄሮች ብሄረሰቦች ያሉባት ሀገር እንደመሆኗ የህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓት በጠንካራ ሂደት መገንባት ለሀገር እድገት እና ሰላም ግንባታ የማይተካ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የፌደራሊዝም ጥናት ትምክርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ግሩም ክንፈሚካኤል ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ በጽሁፋቸው ኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ የተገበረቻቸዉን የመንግስት አወቃቀር በመዳሰስ በአሁን ወቅት እየከተለቸዉ ያለዉን የሕብረ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓት አብራርተዋል፡፡ በቀረበው የመነሻ ፅሁፍ ላይ አሰተያየቶችና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች በመቅረብ ውይይት ተደርጓል፡፡ በማስከተልም በፊደራሊዝም የሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች መካከል የጥያቄና ምልስ ዉድድር ተካሂዷል፡፡
በዓሉን አስመልክቶ ቀደም ሲል በተከናወኑ መርሀ- ግብሮችም በህዳር 14 ቀን 2016 ዓም በጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን ማዕከል የአልባሳት ልገሳ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ በክረምት መርሀ ግብር በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የጸረ ሙስና ቀን ተከበረ
---------------------
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀን ‘‘ሙስና ጠላታችን ነው ፤በጋራ እንታገለው’’ በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርስቲዉ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ/ም በፓናል ውይይት እና በተቋሙ በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት በማቅረብ ተከብሯል፡፡
የውይይቱን መድረክ የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በአስተላለፉት መልዕክት ‘‘ ሙስና ግዑዝ ነገር አይደለም ፤ሀብት በአግባቡ ለታለመለት ጉዳይ አለማዋል ማለት ነዉ ፡፡በዚህም አመራሮች የመወሰን ስልጣን ያለን የመንግስት ሀብት በአግባቡ እየተጠቀምን ነዉ ወይ የሚለዉን መጠየቅ ፣ተቋማችንን እያየን በመገምገም አቅጣጫ እያስቀመጥን የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የጸረ ሙስና ትግል አካል ሆነን እነደ ዜጋ ድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል ፡፡’’
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ በስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሰላማዊት ተ/ሚካኤል ‘’የሙስና ምንነትና የሚያስከትለው ጉዳት’’ በሚል ርዕስ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት ቀርቧል፡፡ በውይይቱም የሙስና ምንነት ፤ መንስኤዎችና መገለጫዎቹ፤ ሙስና የሚያስከትለው ጉዳት እንዲሁም ሙስናን በጋራ ለመከላከል የባለ ደርሻ አካላት ሚና ምን መሆን እንዳለበት ለተሳታፊዎች በዝርዝር ቀርቧል ፡፡
በእለቱም በየዘርፉ ያሉ ኃላፊዎች የሙስና ተጋላጭነት እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚታገሉት የዘረጉት አሰራር ጭምር አብራርተዉ ለሙስና ሂደት በር የሚከፍቱ አሰራሮች እንዴት እንደሚከታተሉ አስተያየታቸዉን በመስጠት የዘርፋቸዉን ሂደት ገምገመዋል፡፡በተለይ ከፍተኛ ፋይናንስ የሚያንቀሳቅሱ እና የሰው ሀብትን የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ከመታገል አኳያ እራሳቸውን እንዲፈትሹ በቀረበው የውይይት ርዕስ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአንዳንድ ስራ አስፈጻሚዎች በተጨባጭ የተሰራው ስራ እና የታየው የፀረ ሙስና ትግል ቁርጠኝነት ለሁሉም ስራ አስፈጻሚዎች በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማጠቃላያዉም ላይ ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት ይህ መድረክ የምንማማርበት ግንዛቤ የምንጨብጥበት መድረክ እንደመሆኑ ሁላችንም በተሰማራንበት እና አመራር በምንሰጥበት ዘርፍ ስራዎች በአግባቡ መሰራቱን የማረጋገጥ ትልቅ ሀላፊነት እንዳለብን ከዚህ ባለፈም ለምንስራቸዉ ማንኛዉም ስህተቶች ከተጠያቂነት እንደማናመልጥ መገንዘብ ማንኛዉም ስራዎች በህግ እና በህግ አግባባብ ብቻ መስራት አስፈላጊ ነዉ ብለዋል፡፡
---------------------
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀን ‘‘ሙስና ጠላታችን ነው ፤በጋራ እንታገለው’’ በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርስቲዉ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ/ም በፓናል ውይይት እና በተቋሙ በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት በማቅረብ ተከብሯል፡፡
የውይይቱን መድረክ የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በአስተላለፉት መልዕክት ‘‘ ሙስና ግዑዝ ነገር አይደለም ፤ሀብት በአግባቡ ለታለመለት ጉዳይ አለማዋል ማለት ነዉ ፡፡በዚህም አመራሮች የመወሰን ስልጣን ያለን የመንግስት ሀብት በአግባቡ እየተጠቀምን ነዉ ወይ የሚለዉን መጠየቅ ፣ተቋማችንን እያየን በመገምገም አቅጣጫ እያስቀመጥን የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የጸረ ሙስና ትግል አካል ሆነን እነደ ዜጋ ድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል ፡፡’’
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ በስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሰላማዊት ተ/ሚካኤል ‘’የሙስና ምንነትና የሚያስከትለው ጉዳት’’ በሚል ርዕስ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት ቀርቧል፡፡ በውይይቱም የሙስና ምንነት ፤ መንስኤዎችና መገለጫዎቹ፤ ሙስና የሚያስከትለው ጉዳት እንዲሁም ሙስናን በጋራ ለመከላከል የባለ ደርሻ አካላት ሚና ምን መሆን እንዳለበት ለተሳታፊዎች በዝርዝር ቀርቧል ፡፡
በእለቱም በየዘርፉ ያሉ ኃላፊዎች የሙስና ተጋላጭነት እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚታገሉት የዘረጉት አሰራር ጭምር አብራርተዉ ለሙስና ሂደት በር የሚከፍቱ አሰራሮች እንዴት እንደሚከታተሉ አስተያየታቸዉን በመስጠት የዘርፋቸዉን ሂደት ገምገመዋል፡፡በተለይ ከፍተኛ ፋይናንስ የሚያንቀሳቅሱ እና የሰው ሀብትን የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ከመታገል አኳያ እራሳቸውን እንዲፈትሹ በቀረበው የውይይት ርዕስ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአንዳንድ ስራ አስፈጻሚዎች በተጨባጭ የተሰራው ስራ እና የታየው የፀረ ሙስና ትግል ቁርጠኝነት ለሁሉም ስራ አስፈጻሚዎች በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማጠቃላያዉም ላይ ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት ይህ መድረክ የምንማማርበት ግንዛቤ የምንጨብጥበት መድረክ እንደመሆኑ ሁላችንም በተሰማራንበት እና አመራር በምንሰጥበት ዘርፍ ስራዎች በአግባቡ መሰራቱን የማረጋገጥ ትልቅ ሀላፊነት እንዳለብን ከዚህ ባለፈም ለምንስራቸዉ ማንኛዉም ስህተቶች ከተጠያቂነት እንደማናመልጥ መገንዘብ ማንኛዉም ስራዎች በህግ እና በህግ አግባባብ ብቻ መስራት አስፈላጊ ነዉ ብለዋል፡፡
G+7 የስልጠና ማዕከል ግንባታ ዉል ስምምነተ ተደረገ
------------------------------------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) ዘመናዊ የስልጠና ማዕከል የግንባታ ዉል ስምምነት ከ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ 19/4/2016 ዓ.ም አደረገ፡፡ተቋራጭ ድርጅቱ ግንባታዉን በ2 ዓመት ዉስት ገንብቶ ለዩኒቨርስቲዉ እንደሚያስረክብ ገልጿል፡፡
በዉል ስምምነቱ ወቅት የኢሲሰዩ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደተናገሩት ይህ ፕሮጀክት በ2 ዓመት የግዜ ገደብ የሚጠናቀቅ ሲሆን በተለይ ዩኒቨርሲቲዉ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ለሚያደርገዉ የሽግግር ሂደት ትልቁን ድርሻ ይይዛል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ በዉስጡ የተለያዩ ዘመኑን የዋጁ ማሰልጠኛ ክፍሎች፣ሙዚየሞች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ስልጠና ማዕከል የሚያስልጉ ክፍሎች ከተሟሉ ግብአቶች ጋር የሚይዝ ሲሆን ተቋሙን አሁን ካለዉ የስልጠና መዕከል ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረዉ ነዉ ብለዋል፡፡
የፕሮጀክት አሸናፊ አሴፍ ኢንጂነሪንግ ይህን ግንባታ ሲያከናዉን አደራ ጭምር የምንሰጠዉ የፕሮጀክቱ አሸናፊ ድርጅት ብቻ ሳይሆን እንደ ዜጋ ሀላፊነቱን በመወጣት ለትዉልድ የሚተላለፍ ግንባታ በመገንባት አሻራዉን ማሳረፍ አለበት ብለዋል፡፡ዩኒቨርስቲዉ የሚገነባዉ ህንጻ ለትዉልድ ተሸጋሪ እንዲሆን ከጅማሪዉ ጀምሮ ትልቅ ትኩረት አድርጎ የሰራ መሆኑን በመግለጽ ይህ ፕሮጀክት እዚህ ደረጃ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሂደት በተመለከት የኢሲሰዩ የምህንድስናና ጥገና አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለሙ ሲሳይ እንደገለጹት የስልጠና ማዕከሉ ለመገንባት ግልጽ ጨረታ የወጣ ሲሆን 36 ተወዳዳሪዎች ተወዳድረዉ 6 ተወዳዳሪዎች የተቀመጠዉን መስፈርት ያሟሉ ሲሆን ከእነዚህ ዉስጥም አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮንሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) እንዳሸነፈ አብራርተዋል፡፡
የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አስራት ኤፍሬም እንደገለጹት ከዩኒቨርስቲዉ ጋር ለመስራት እድሉን ስላገኙ ደስተኛ መሆናቸዉን በመግለጽ ማዕከሉን በጥሩ ሁኔታ መርተን በተቀመጠለት የግዜ ገደብ በማጠናቀቅ እናስረክባለን ብለዋል፡፡ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ1994 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመስራት ብዙ ልምድ ያለዉ ዉጤታማ ስራ የሰራ መሆኑን ገልጸዉ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት የምንሰራዉ ስራ ምስክር እንዲሆን አድርገን እንገነባዋለን ብለዋል፡፡
------------------------------------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) ዘመናዊ የስልጠና ማዕከል የግንባታ ዉል ስምምነት ከ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ 19/4/2016 ዓ.ም አደረገ፡፡ተቋራጭ ድርጅቱ ግንባታዉን በ2 ዓመት ዉስት ገንብቶ ለዩኒቨርስቲዉ እንደሚያስረክብ ገልጿል፡፡
በዉል ስምምነቱ ወቅት የኢሲሰዩ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደተናገሩት ይህ ፕሮጀክት በ2 ዓመት የግዜ ገደብ የሚጠናቀቅ ሲሆን በተለይ ዩኒቨርሲቲዉ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ለሚያደርገዉ የሽግግር ሂደት ትልቁን ድርሻ ይይዛል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ በዉስጡ የተለያዩ ዘመኑን የዋጁ ማሰልጠኛ ክፍሎች፣ሙዚየሞች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ስልጠና ማዕከል የሚያስልጉ ክፍሎች ከተሟሉ ግብአቶች ጋር የሚይዝ ሲሆን ተቋሙን አሁን ካለዉ የስልጠና መዕከል ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረዉ ነዉ ብለዋል፡፡
የፕሮጀክት አሸናፊ አሴፍ ኢንጂነሪንግ ይህን ግንባታ ሲያከናዉን አደራ ጭምር የምንሰጠዉ የፕሮጀክቱ አሸናፊ ድርጅት ብቻ ሳይሆን እንደ ዜጋ ሀላፊነቱን በመወጣት ለትዉልድ የሚተላለፍ ግንባታ በመገንባት አሻራዉን ማሳረፍ አለበት ብለዋል፡፡ዩኒቨርስቲዉ የሚገነባዉ ህንጻ ለትዉልድ ተሸጋሪ እንዲሆን ከጅማሪዉ ጀምሮ ትልቅ ትኩረት አድርጎ የሰራ መሆኑን በመግለጽ ይህ ፕሮጀክት እዚህ ደረጃ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሂደት በተመለከት የኢሲሰዩ የምህንድስናና ጥገና አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለሙ ሲሳይ እንደገለጹት የስልጠና ማዕከሉ ለመገንባት ግልጽ ጨረታ የወጣ ሲሆን 36 ተወዳዳሪዎች ተወዳድረዉ 6 ተወዳዳሪዎች የተቀመጠዉን መስፈርት ያሟሉ ሲሆን ከእነዚህ ዉስጥም አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮንሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) እንዳሸነፈ አብራርተዋል፡፡
የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አስራት ኤፍሬም እንደገለጹት ከዩኒቨርስቲዉ ጋር ለመስራት እድሉን ስላገኙ ደስተኛ መሆናቸዉን በመግለጽ ማዕከሉን በጥሩ ሁኔታ መርተን በተቀመጠለት የግዜ ገደብ በማጠናቀቅ እናስረክባለን ብለዋል፡፡ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ1994 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመስራት ብዙ ልምድ ያለዉ ዉጤታማ ስራ የሰራ መሆኑን ገልጸዉ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት የምንሰራዉ ስራ ምስክር እንዲሆን አድርገን እንገነባዋለን ብለዋል፡፡
𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗣𝗿𝗲𝘀𝗶𝗱𝗲𝗻𝘁 𝗗𝗶𝘀𝗰𝘂𝘀𝘀𝗲𝘀 𝘄𝗶𝘁𝗵 𝗗𝗲𝗽𝘂𝘁𝘆 𝗛𝗲𝗮𝗱 𝗼𝗳 𝗘𝗨 𝘁𝗼 𝗔𝗨
Professor Fikre Dessalegne, Ethiopian Civil Service President, discussed with H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of Delegation European Union to the African Union on further strengthening the bilateral relations of ECSU and Kehl University in Germany on January19, 2024 at Hidasse Hall.
The President welcomed H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of EU Delegation to African Union and University Scholars and students from Kehl University, Germany. He added: ‘I am pleasured to see scholars from different background and different countries which is a valuable input for working together in the areas of public services. ‘’
The president said that as a higher Institution, one of ECSU strategic plan is partnership, internationalization and networking, so we have interest to further strengthening the tie with Kehl University. As we see, the progress of masters’ program in public Management in International relations which we started in collaboration with kehl University is one of the successes that has brought by collaborative effort he added. He also explained the overall strategic plan of ECSU on the Internationalization and partnership and the interest of working together in different areas with Kehl University.
Dr lemma Gudissa, ECSU Vice President for academic affairs, on his part, welcomed the Delegates and explained the strengthening of collaboration between the two institutions in different aspects in the future .He also noted that to further strength the masters’ program and open PhD program in collaboration with Kehl university .Besides, he briefly explained the University’s vision, mission, and values to the representatives and his discussion with kehl university Rector on the bilateral issues .
Dr. Joachim Beck, Rector of Kehl University, explained that how the international cooperation creates a learning environment and understand different system of government and practices in each country and opportunities to understand the different cultures in different countries. He also explained that in the collaborative masters’ program five universities from four countries are working together and ECSU is one of the partner institute.
He also briefed that the two institutions have the same vision which are working on Public service capacity building. So it possible to work together in administrative culture and developed the two years masters’ program to PhD project he underlined.
Onur Yel, Counselor of culture and Press representing Germen Embassy in Ethiopia thanked the hospitality of the Ethiopian and Civil Service University. He also emphasized developing cooperation among different institutions is very important and wished the students for the successful accomplishment of the program.
Finally, Students raised different questions for H.E. Riccardo Mosca and he respectively answered the questions raised by the students.
Professor Fikre Dessalegne, Ethiopian Civil Service President, discussed with H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of Delegation European Union to the African Union on further strengthening the bilateral relations of ECSU and Kehl University in Germany on January19, 2024 at Hidasse Hall.
The President welcomed H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of EU Delegation to African Union and University Scholars and students from Kehl University, Germany. He added: ‘I am pleasured to see scholars from different background and different countries which is a valuable input for working together in the areas of public services. ‘’
The president said that as a higher Institution, one of ECSU strategic plan is partnership, internationalization and networking, so we have interest to further strengthening the tie with Kehl University. As we see, the progress of masters’ program in public Management in International relations which we started in collaboration with kehl University is one of the successes that has brought by collaborative effort he added. He also explained the overall strategic plan of ECSU on the Internationalization and partnership and the interest of working together in different areas with Kehl University.
Dr lemma Gudissa, ECSU Vice President for academic affairs, on his part, welcomed the Delegates and explained the strengthening of collaboration between the two institutions in different aspects in the future .He also noted that to further strength the masters’ program and open PhD program in collaboration with Kehl university .Besides, he briefly explained the University’s vision, mission, and values to the representatives and his discussion with kehl university Rector on the bilateral issues .
Dr. Joachim Beck, Rector of Kehl University, explained that how the international cooperation creates a learning environment and understand different system of government and practices in each country and opportunities to understand the different cultures in different countries. He also explained that in the collaborative masters’ program five universities from four countries are working together and ECSU is one of the partner institute.
He also briefed that the two institutions have the same vision which are working on Public service capacity building. So it possible to work together in administrative culture and developed the two years masters’ program to PhD project he underlined.
Onur Yel, Counselor of culture and Press representing Germen Embassy in Ethiopia thanked the hospitality of the Ethiopian and Civil Service University. He also emphasized developing cooperation among different institutions is very important and wished the students for the successful accomplishment of the program.
Finally, Students raised different questions for H.E. Riccardo Mosca and he respectively answered the questions raised by the students.