DDU-SU President Office
3.15K subscribers
721 photos
12 videos
6 files
72 links
Download Telegram
ዉድ የድሬ ዳዋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንኳን ለእሬቻ በዐል በሰላም አደረሳችሁ!

#IRREECHAA_እሬቻ
የሰላም፣ የይቅር ባይነት እና አንድነት በዓል - ኢሬቻ
በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው ገዳ ስርዓት አንዱ እሴት የሆነው ኢሬቻ የሰላምና የምስጋና በዓል ነው።
በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርብበትና የሚፈልገውን ፈጣሪ እንዲፈጽምለት የሚጠይቅበት ነው::
ኢሬቻ በሁለት የተለያዩ ጊዜ እና ስፍራ ይከበራል። አንዱ ኢሬቻ መልካ ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ኢሬቻ ቱሉ ነው።
የጭለማ፣ ጭጋጋማ እና ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ወንዞች ጎድለው የውሃ ሙላት ካለፈ በኋላ መሬቱ ጠገግ ሲል የሚከበረው ኢሬቻ መልካ ክረምት እና የውሃ ሙላት የለያያቸው ሰዎች መገናኘት የሚጀምሩበት ነው፡፡
ክረምቱን በእርሻ ስራ የደከመ ሰው የሚያርፍበት እና የላቡን ተስፋ በሰብሉ ማበብ ማየት በሚጀምርበት ወቅት የሚከበረው ኢሬቻ መልካ በመስከረም ወር መጨረሻ ውሃ በሚገኝበት ስፍራ ሲከበር ለፈጣሪ ምስጋና ይቀርባል።
ኢሬቻ ቱሉ ዝናብ ሲርቅ፣ ወንዞች ሲደርቁ፣ መሬት ለከብቶች ሳር ስትነሳ፣ ድርቅ እና ረሃብ በሰውና በእንስሳት ላይ ሲያይል ዝናብ እንዲጥል ወደ ተራራ በመውጣት ለፈጣሪ ልመና የሚቀርብበት ነው።
በየዓመቱ መስከረም ወር መጨረሻ በአዲስ አበባ ሆረ ፊንፊኔ፣ በቢሾፍቱ ሆረ ሃርሰዴ፣ በቡራዩ ሆረ አቴቴ፣ በሰበታ መልካ ሰበታ እንዲሁም በየአካባቢው በዚሁ ጊዜ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል፥ ከገዳ ስርዓት ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለ
ምሁራን የናገራሉ:: ኢሬቻ መልካ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች፣ ቄሮ እና ቀሬዎች ተሰባስበው በአባገዳዎችና በአባመልካዎች መሪነት በታላላቅ ወንዞች ወይም ሐይቆች ዳር በመሄድ “አንተ ደግ ፈጣሪ ዋቃ ሆይ ውሃውን የፈጠርክ፣ ክረምቱን በሰላም ስላሳለፍከን፣ ወደ ብርሃን፣ አበባና ተስፋ ወዳየንበት ወደ ብራው ወቅት ስላሻገርከን እናመሰግናለን፤ ለአበባው ፍሬ ሰጥተህ ጎተራችን እና በረታችን ሙሉ ይሁንልን፤ የጥጋብ ዓመት ያድርግልን” እያሉ ምስጋና እና ፀሎት ያቀርባሉ።
በወርሃ መስከረም በሚከበረው የኢሬቻ በዓል፥ የተፈጥሮ ህግ ሳይዛባ ለመቆየቱ ወደፊትም ሚዛኑ እንዲጠበቅ ለአንድ ፈጣሪ ለምለም ሳር ተይዞ ምስጋና ይቀርብበታል።
የተጣላ ታርቆ፣ ቂሙን ትቶ የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ከሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭ የሚመጣ ታዳሚ በሙሉ በንጹህ ልቦና ፈጣሪ ንጹህ ወዳደረገው የውሃ አካል ይሄዳል።
ታዳሚው እርጥብ ሳር ወይም አበባ በእጁ በመያዝ ወንዝ ዳር ቆሞ፥ “ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያጸደቅከው ነው፤ አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሀለን” በማለት ምስጋናው ያቀርባል።
በዚህም የኦሮሞ ህዝብ በክረምት ወራት ዝናብ ለሰጠው ፈጣሪው ምስጋናውን ያቀርባል፤ በቀጣይም ቡቃያው ከየትኛውም የተፈጥሮ አደጋ ተጠብቆ በሰላም ወደ ጎተራው እንዲገባ ይማጸንበታል።
የኦሮሞ ሕዝብ ለሰላም የሚሰጠው ስፍራ ጉልህ በመሆኑ ምስጋናውን ለማድረስ የኢሬቻ በዓልን ሲያከብር፥ ኢሬቻ የእርቅና የሰላም ምንጭ እንደሆነ ያምናል።
በመሆኑም ኢሬቻ የሚያከብሩ ቂም ይዘው ማክበር ስለማይችሉ አባመልካው ስርዓቱን በምርቃት ከማስጀመራቸው አስቀድመው መታረቅና ይቅር መባባል፤ ቂምን መሻር ግዴታቸው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
ይቅርታ ያላደረገ እና ያልተቀበለ፣ ቂም በሆዱ ያሳደረ እና ያኮረፈ የሚያቀርበው ምስጋና ዋጋ አይኖረውም።
ይህ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ለዘመናት ሲከበር የቆየውን የኢሬቻ በዓል፥ እሴቱ ተጠብቆ ሊቆይ ቺሉዋል።
ኢሬቻ የሀይማኖት፣ የፖለቲካ እና የአመለካከት ልዩነቶች ሳይፈጠሩ ህዝቡ በአንድነት የሚገናኝበትና ፈጣሪ ፊት የሚቀርብበት አሰባሳቢ በዓል ነው።

መልካም በዐል ይሁንልን።

ጎሳ ከበደ
የድሬ ዳዋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝደንት
👍116🔥1
DDU ተማረዎች ህብረት ICT ክለብ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ተጀመረ!
ትናንት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የDDU ICT ክለብን በይፋ አስጀመርን፤ ይህ ክለብ ለቴክኖሎጂ ወዳጆች፣ ለፈጣሪዎችና ለአዳዲስ ነገሮች ገንቢዎች አዲስ መናኸሪያ ይሆናል። የመክፈቻ ዝግጅቱ በአነቃቂ ንግግሮች፣ አሳታፊ ውይይቶች እና ወደፊት ስለምንሄድበት ጉዞ በጋራ በሚነበበው ጉጉት የተሞላ ነበር። ገና እየጀመርን ነው፣ እናም ከዚህ ማኅበረሰብ ምን ያህል አስደናቂ ፕሮጀክቶችና ሐሳቦች እንደሚፈልቁ ለማየት ጓጉተናል።


Gamtaa Barattootaa DDU ICT Kilabii Yuunivarsiitii Dirre Dhawaatti ifatti Eegalame!
Kaleessa Yuunivarsiitii Dirree Dhawaatti gumii DDU ICT ifatti eegalle; gumiin kun jaallattoota teeknooloojii, kalaqtootaafi hojii bu'uuraa haaraa hundeesseef bakka haaraa ta'a. Sagantaan baniinsaa haasawwan kaka'umsa kennan, mariiwwan hirmaachisoo fi fedhii waliinii imala gara fuulduraatti godhamuuf qabnuun kan guutame ture. , akkasumas gumii kana irraa pirojektiiwwan dinqisiisoo fi yaadoleen hedduun akka madduuf hawwiin eegganna.
🔥4👍1👏1
officially launched the DDU Student Union ICT Club yesterday a new home for tech lovers, innovators, and creators at Dire Dawa University! The opening event was filled with inspiring speeches, engaging discussions, and shared excitement about the journey ahead. We’re just getting started, and we can’t wait to see what amazing projects and ideas will rise from this community. Here’s a look back at the moments that kicked it all off!
👍4🔥1
በትላንትናው እለት የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት በካፍቴሪያ ዘርፍ አባላት ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት የሆነው ጎሳ ከበደ የተገኘ ሲሆን
ተማሪዎች በካፌ አገልግሎት ዙሪያ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በምን መልኩ መፍታት እንደሚቻል እና የተሻለ አገልግሎት እንዴት ማቅረብ እንደሚቻል መክረዋል
የዘርፉ ተጠሪ የሆነው ተማሪ ሸምሰዲን ለተማሪዎች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የበኩላችን እንወጣለን ሲል አክሏል።

Guyyaa kaleessaa Yuunivarsiitii Dirree Dhawaatti Gamtaan Barattootaa miseensota Damee Kafeteeriyaa waliin marii gaggeesse.
Maricharratti Pirezidaantiin Gamtaa Barattootaa Gosaa Kabbadaa argameera.
Barattoonni rakkoolee tajaajila kafeteeriyaa irratti isaan mudatan akkamitti furuu akka danda'anfi akkamitti tajaajila fooyya'aa kennuu akka danda'an irratti mari'ataniiru.
Qindeessaan damechaa barataa Shamsaddin, tajaajila gaarii barattootaaf kennuuf gahee keenya ni baana jedheera.
😁43👍1🔥1🌭1
Yesterday, the Dire Dawa University Students' Union held a discussion with members of the Cafeteria Sector.
The discussion was attended by Gossa Kebede, President of the Students' Union.
Students discussed how to solve the problems they face regarding cafeteria services and how to provide better service.
Student Shemsedin, the head of the sector, added that they would do their part to provide better services to the students.
😁12👏54
ትላንት እና ዛሬ (በቀን 24_ 25 ) በሐረር ከተማ ሲካሄድ በቆየው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ላይ ከተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ ከሴቶች ዘርፍ፣ ከልዩ ፍላጎት እና ከህዝብ ግንኙነት ዘርፍ የዩኒቨርስቲ ወጣት ፣ሴት እና ልዩ ፍላጎት ወክለው በመገኘት ሀሳባቸውን አንፀባርቀዋል።


Kaleessaafi har'a (guyyaa 24-25) magaalaa Hararitti kan geggeeffame marii biyyaalessaa Itoophiyaa irratti, bakka bu'oonni Pirezidaantii Ittaanaa Gamtaa Barattootaa, Damee Dubartootaa, Fedhii Addaafi Damee Hariiroo Hawaasaa irraa kan walitti qabaman dargaggoonni, dubartoonniifi qaama miidhamtoonni Yuunivarsiitii, bakka bu'uun yaada isaanii ibsaniiru.


Yesterday and today (on the 24th and 25th), during the Ethiopian National Dialogue held in Harar city, representatives from the University's youth, women, and persons with disabilities, including the Vice President of the Students' Union, as well as those from the women's sector, special needs sector, and public relations sector, participated and expressed their views.
5👏3👍1
ማስታወቂያ ለድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ! 
.......................................................................................................................................................................................... 
የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት ጤና(health) ዘርፍ በ2018ዓ.ም እንደ አዲስ የዓባላት ምዝገባ ሰለሚያረግ መሳተፍ ለምትፈልጉ ከቀን 26/01/2018 እስከ27 /01/2018 በቢሯችን በ LTH7 ከ6:00 እስከ 8:00 ሰአት እና ከምሽቱ 2:30 እስከ 4:00 መታችው መመዝገብ የምትችሉ ይሆናል።

ለበለጠ መርጃ ቁጥር: 0991213797
ይደውሉልን። 
እናመሰግናለን።

————————

beeksisa Barattoota Yuunivarsiitii Diredawa hundaaf! 
.......................................................................................................................................................................................... 
Namoonni sektera Fayyaa Dirre Dawa Yuunivarsiitii keessatti hirmaachuu barbaaddan guyyas 27/01/2018 hanga 27/01/2018 biiroo LTH7 keessatti sa'atii 06:00 hanga 08:00 fi galgala sa'atii 02:30 hanga 04:00 irratti dhuftanii galmaawuu dandeessu.

Odeefanno dabalataaf: 
Lakk. bilb. 0991213797


————————

Notice to all Dire Dawa University students! 
.......................................................................................................................................................................................... 
For those who want to participate in the health sector of Dire Dawa University Students' Union in 2018 as a new member registration, you can register from 17/01/2018 to 19/01/2018 at our office at LTH7 from 6:00 AM to 8:00 AM and in the evening from 2:30 PM to 4:00 PM.

For more information: 0991213797 
7