Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
በአብይ ሐይለ ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አጋእዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም
ለማስታወስ ያህል ነው እንጂ አልረሳቹትም ።
እንደምን ቆያችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች? ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ጸንቶ ይኑር አሜን!
ዛሬ እንደምታወቀው ሳምንታዊ የዓርብ ጸሎት ቀን ነው።ስለሆነም ሁላችንም በሰዓቱ ተቀሳቅሰን በመምጣት የእመቤታችንን ውዳሰዋን በሕብረት እናድርስ፥እረፍት እና ሰላም የምሆነንን ቃለ እግዚአብሔር እንማር!
እስከዛም ቸር ያቆየን🤲
ከቀኑ:-10:30 ጀምሮ።
ቦታ:- በግቢ ጉባኤው ዋና አዳራሽ።
❤2
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
በአብይ ሐይለ ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አጋእዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም
እንደምን ቆያችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች? ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ጸንቶ ይኑር አሜን!
እንደምታወቀው ዛሬ ማለትም ዕለተ ቅዳሜ 09/09/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ሳምንታዊ የክፍላት ውይይት ቀን ነው።ስለሆነም ሁላችንም በሰዓቱ ተቀሳቅሰን በመገኘት ለሕይወታችን እና ለኑሯችንም የምበጀንን ቃለ እግዚአብሔር እንማማር !
በየክፍላችሁ ልጆቻችሁን ቀስቅሱ
እስከዛም ቸር ያቆየን🤲
ከቀኑ:-10:00 ጀምሮ።
ቦታ:- በግቢ ጉባኤው ዋና አዳራሽ።
መጻፊያው ተከፍቷል። ሀሳብ ለመስጠት ይሄንን link ይጠቀሙ 👉https://t.me/dbugg21group
👍1
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
አስታወሳችሁ???
በቀን አንድ በዕለተ ዓርብ በእመቤታችን በልደቷ ቀን ነበር ዋና ዋና የክፍሉ ሰብሳቢዎች አጀንዳ የተረካከቡት እነሆ ዛሬ ደግሞ የየክፍሉ ምክትል ሰብሳቢዎች፤የክፍሉ ጸሐፊዎች፤እንዲሁም የየንዑስ ክፍሉ ሰብሳቢዎች፤ምክትል ሰብሳቢዎችና ጸሐፊዎችም ጭምር በዛሬው ዕለት አጀንዳ ተረካክበዋል።ነባር ወይም የ2017 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎች በነበራቸው የአገልግሎት ዘመን እጅግ ደስተኞች እንደነበሩና አሁን ወደ ኃላፊነት እግዚአብሔር የጠራቸውን የመንጋ ጠባቂ በመሆን በየደረጃቸው የተመደቡትን የ2018 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎችን በርትተውና ጠንክረው ያላቸውን ግዜ እንድጠቀሙና በቀናነት እግዚአብሔርን እና ሕዝቡን እንድያገለግሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ባላለቀ ስል ዓመቱ አለቀ
ባልመሸ ብዬ እየተመኘሁ በቃ ግን መሸ😥
በነበረን ግዜ በእውነት እጅግ በጣም ደስተኞች ነበርን እግዚአብሔርም በጎደለው እየሞላ፥በፈረሰው እየሰራ ፤ስበርደን እያሞቀ፤ስሞቀንም ውሃ ሁኖ እያቀዘቀዘ በቸርነት ጠብቆ ለዚህ አድርሶናል ወንድሞች ሆይ በድካማችሁ እግዚአብሔር ብርታት ፤ይሆናችኋልና በትጋት እንድታገለግሉ፤የተሰጣችሁን አደራ በቅንነትና በጨዋነት ከሁሉ በላይ መንፈሳዊነትን በተሞላ ስብእና እንድታገለግሉ ከእግዚአብሔር ጋርም ሕብረት እንድኖራችሁ ጽኑ ጠንክሩ ስትል እናት ግቢ ጉባኤ የደስታ ጥሪዋን ታስተላልፋለች። መጽሐፍ እንዳለ እጅጉን ተግታችሁ ከእግዚአብሔር ጋር ባሳለፍነው ዓመት የታየውን ክፍተት በመሙላት ፤ ችግሮችንም በመፍታት ከፍት ይልቅ አሁን ትጉ👉'' ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ።(2 ጴጥሮስ 1፥10)
በቀን አንድ በዕለተ ዓርብ በእመቤታችን በልደቷ ቀን ነበር ዋና ዋና የክፍሉ ሰብሳቢዎች አጀንዳ የተረካከቡት እነሆ ዛሬ ደግሞ የየክፍሉ ምክትል ሰብሳቢዎች፤የክፍሉ ጸሐፊዎች፤እንዲሁም የየንዑስ ክፍሉ ሰብሳቢዎች፤ምክትል ሰብሳቢዎችና ጸሐፊዎችም ጭምር በዛሬው ዕለት አጀንዳ ተረካክበዋል።ነባር ወይም የ2017 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎች በነበራቸው የአገልግሎት ዘመን እጅግ ደስተኞች እንደነበሩና አሁን ወደ ኃላፊነት እግዚአብሔር የጠራቸውን የመንጋ ጠባቂ በመሆን በየደረጃቸው የተመደቡትን የ2018 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎችን በርትተውና ጠንክረው ያላቸውን ግዜ እንድጠቀሙና በቀናነት እግዚአብሔርን እና ሕዝቡን እንድያገለግሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ባላለቀ ስል ዓመቱ አለቀ
ባልመሸ ብዬ እየተመኘሁ በቃ ግን መሸ😥
በነበረን ግዜ በእውነት እጅግ በጣም ደስተኞች ነበርን እግዚአብሔርም በጎደለው እየሞላ፥በፈረሰው እየሰራ ፤ስበርደን እያሞቀ፤ስሞቀንም ውሃ ሁኖ እያቀዘቀዘ በቸርነት ጠብቆ ለዚህ አድርሶናል ወንድሞች ሆይ በድካማችሁ እግዚአብሔር ብርታት ፤ይሆናችኋልና በትጋት እንድታገለግሉ፤የተሰጣችሁን አደራ በቅንነትና በጨዋነት ከሁሉ በላይ መንፈሳዊነትን በተሞላ ስብእና እንድታገለግሉ ከእግዚአብሔር ጋርም ሕብረት እንድኖራችሁ ጽኑ ጠንክሩ ስትል እናት ግቢ ጉባኤ የደስታ ጥሪዋን ታስተላልፋለች። መጽሐፍ እንዳለ እጅጉን ተግታችሁ ከእግዚአብሔር ጋር ባሳለፍነው ዓመት የታየውን ክፍተት በመሙላት ፤ ችግሮችንም በመፍታት ከፍት ይልቅ አሁን ትጉ👉'' ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ።(2 ጴጥሮስ 1፥10)
❤1
†
🕊 💖 ቅዱስ ያሬድ 💖 🕊
[ ግንቦት ፲፩ [ 11 ] የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል ]
♥ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ [ ይሥሐቅ ] እናቱ ክርስቲና [ ታውክልያ ] ሲባሉ የተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. በአክሱም ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላረፈ፤ እናቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምረው ለአባ ጌዴዎን ሰጠችው፡፡
❤ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዴዎን ይቈጣው ነበርና ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ ፤ ከዐዘኑም ብዛት የተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሽ ትል ከዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጨረሻም በጭንቅ ከዛፉ ላይ ሲወጣ በማየቱ እግዚአብሔር በዚኽች ታናሽ ፍጥረት እንዳስተማረው በመረዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡
♥ ❝ ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህረ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ❞ ይላል ከዚኽ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኾኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጨረስ ዲቁናን ተሾመ ፤ እስከ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በከፍተኛ ድምፅ የመዝሙር ማሕሌት አልነበረም ፤ እግዚአብሔርም ለዚኽ አባት የመላእክትን ዝማሬ ሊያሳየው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ የኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን የምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡
♥ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደረሰ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ፦ ❝ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ❞
[ ለአብ ምስጋና ይገባል ፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል ፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም ለሙሴ የድንኳኑን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ አሳየው ] ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ከሰማይ መላእክት አገኘኹት ፣ በማለት "አርያም" በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡
♥ ይኽነኑ ድርሳነ ዜማ የጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብረ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስከትል መኳንንቱ ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተከትለው እየተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኼድ በተመስጦ ሲሰሙት ውለዋል፡፡
♥ ቅዱስ ያሬድ ዐምስት የዜማ መጻሕፍትን የደረሰ ሲኾን እነርሱም ፦
፩ኛ ] ድጓ
፪ኛ ] ጾመ ድጓ
፫ኛ ] ምዕራፍ
፬ኛ ] ዝማሬ
፭ኛ ] መዋሥዕት ናቸው፡፡
♥ እነዚኽንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሦስት የዜማ ስልቶች ማለት በግእዝ ፣ በዕዝል ፣ በአራራይ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ ❝ ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብረ መስቀል ወእንዘ ያጸምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተከለ በትረ ኀጺን ውስተ መከየደ እግሩ ለያሬድ❞ ይላል ፤ ከዕለታት ባንዳቸው ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብረ መስቀል ሳያውቁት ልባቸው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ የብረት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታል፤ ከእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስከሚፈጽም ድረስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡
♥ ንጉሡም የደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጦ ቅዱስ ያሬድን ❝ የደምኽ ዋጋ የፈለግኸውን ንገረኝ ❞ አለው ፤ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኼድ እንደኾነ ነገረው ፤ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡
♥ ❝ ወእምዝ ቦአ ያሬድ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቦተ ጽዮን ❞ ይላል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት በመቆም የአንቀጸ ብርሃንን ምስጋና ከመዠመሪያው እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኽል ከምድር ከፍ ከፍ አለ።
❤ ከዚኽ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ገዳም ሲኼድ የአኲስም ጽዮን ካህናት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት ርሱም እጅግ ባማረ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ከፍ አድርጎ ❝ ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትረ ምስለ ኲልክሙ ❞ [ በኹሉ ላይ ጸንታ የምትኖር የእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ከኹላችኊ ጋር ትኑር ] ብሎ የስንብት መዝሙርን ዘመረ ፤ ካህናቱም ይኽነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡
♥ በትርጓሜ ቅዳሴ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቦታ ተሰውሮ ጸዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቤታችን ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬምን የብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኤፍሬም ውዳሴዬን ፤ ሕርያቆስ ቅዳሴዬን ነግራችኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድረስልኝ ብላ ነግረውት በዜማ ደርሶታል ፤ ይኽም ሊታወቅ ሥረይ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል፡፡
♥ ርሱም ጸዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማረ መላእክት ዘወትር እየጐበኙት በጾም በጸሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጸንቶ ኖረ፤ በመጨረሻም ጌታችንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጾለት ፦
❝ ኦ ፍቁርየ ቀዳሚኒ በከመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍከ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር ... ❞
[ ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኽ ይኽነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊልና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል። ] ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት ጌታ በክብር ዐረገ፡፡ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቦት ዐሥራ አንድ ነው፡፡
♥ ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ ፦
❝ ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጼ
እንተ አዕረገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ረዋጼ
ለትምህርተ መጽሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጼ
በብዙኅ ጻማ ዘአልቦ ሑጻጼ
መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ የዐርግ ዕጼ❞
[ የመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳረገ ለኾነ ፤ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶ፤ ኰብልሎ ከኼደበት መጻሕፍትን ለመማር የተመለሰ ለኾነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል። ] በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡
♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ ፦
❝ ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ ፤
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ
ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ፡፡ ❞
[ የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል ] ይለዋል፡፡
[ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ]
† † †
💖 🕊 💖
🕊 💖 ቅዱስ ያሬድ 💖 🕊
[ ግንቦት ፲፩ [ 11 ] የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል ]
♥ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ [ ይሥሐቅ ] እናቱ ክርስቲና [ ታውክልያ ] ሲባሉ የተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. በአክሱም ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላረፈ፤ እናቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምረው ለአባ ጌዴዎን ሰጠችው፡፡
❤ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዴዎን ይቈጣው ነበርና ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ ፤ ከዐዘኑም ብዛት የተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሽ ትል ከዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጨረሻም በጭንቅ ከዛፉ ላይ ሲወጣ በማየቱ እግዚአብሔር በዚኽች ታናሽ ፍጥረት እንዳስተማረው በመረዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡
♥ ❝ ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህረ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ❞ ይላል ከዚኽ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኾኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጨረስ ዲቁናን ተሾመ ፤ እስከ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በከፍተኛ ድምፅ የመዝሙር ማሕሌት አልነበረም ፤ እግዚአብሔርም ለዚኽ አባት የመላእክትን ዝማሬ ሊያሳየው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ የኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን የምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡
♥ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደረሰ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ፦ ❝ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ❞
[ ለአብ ምስጋና ይገባል ፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል ፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም ለሙሴ የድንኳኑን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ አሳየው ] ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ከሰማይ መላእክት አገኘኹት ፣ በማለት "አርያም" በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡
♥ ይኽነኑ ድርሳነ ዜማ የጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብረ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስከትል መኳንንቱ ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተከትለው እየተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኼድ በተመስጦ ሲሰሙት ውለዋል፡፡
♥ ቅዱስ ያሬድ ዐምስት የዜማ መጻሕፍትን የደረሰ ሲኾን እነርሱም ፦
፩ኛ ] ድጓ
፪ኛ ] ጾመ ድጓ
፫ኛ ] ምዕራፍ
፬ኛ ] ዝማሬ
፭ኛ ] መዋሥዕት ናቸው፡፡
♥ እነዚኽንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሦስት የዜማ ስልቶች ማለት በግእዝ ፣ በዕዝል ፣ በአራራይ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ ❝ ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብረ መስቀል ወእንዘ ያጸምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተከለ በትረ ኀጺን ውስተ መከየደ እግሩ ለያሬድ❞ ይላል ፤ ከዕለታት ባንዳቸው ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብረ መስቀል ሳያውቁት ልባቸው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ የብረት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታል፤ ከእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስከሚፈጽም ድረስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡
♥ ንጉሡም የደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጦ ቅዱስ ያሬድን ❝ የደምኽ ዋጋ የፈለግኸውን ንገረኝ ❞ አለው ፤ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኼድ እንደኾነ ነገረው ፤ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡
♥ ❝ ወእምዝ ቦአ ያሬድ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቦተ ጽዮን ❞ ይላል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት በመቆም የአንቀጸ ብርሃንን ምስጋና ከመዠመሪያው እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኽል ከምድር ከፍ ከፍ አለ።
❤ ከዚኽ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ገዳም ሲኼድ የአኲስም ጽዮን ካህናት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት ርሱም እጅግ ባማረ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ከፍ አድርጎ ❝ ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትረ ምስለ ኲልክሙ ❞ [ በኹሉ ላይ ጸንታ የምትኖር የእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ከኹላችኊ ጋር ትኑር ] ብሎ የስንብት መዝሙርን ዘመረ ፤ ካህናቱም ይኽነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡
♥ በትርጓሜ ቅዳሴ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቦታ ተሰውሮ ጸዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቤታችን ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬምን የብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኤፍሬም ውዳሴዬን ፤ ሕርያቆስ ቅዳሴዬን ነግራችኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድረስልኝ ብላ ነግረውት በዜማ ደርሶታል ፤ ይኽም ሊታወቅ ሥረይ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል፡፡
♥ ርሱም ጸዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማረ መላእክት ዘወትር እየጐበኙት በጾም በጸሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጸንቶ ኖረ፤ በመጨረሻም ጌታችንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጾለት ፦
❝ ኦ ፍቁርየ ቀዳሚኒ በከመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍከ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር ... ❞
[ ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኽ ይኽነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊልና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል። ] ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት ጌታ በክብር ዐረገ፡፡ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቦት ዐሥራ አንድ ነው፡፡
♥ ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ ፦
❝ ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጼ
እንተ አዕረገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ረዋጼ
ለትምህርተ መጽሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጼ
በብዙኅ ጻማ ዘአልቦ ሑጻጼ
መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ የዐርግ ዕጼ❞
[ የመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳረገ ለኾነ ፤ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶ፤ ኰብልሎ ከኼደበት መጻሕፍትን ለመማር የተመለሰ ለኾነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል። ] በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡
♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ ፦
❝ ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ ፤
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ
ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ፡፡ ❞
[ የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል ] ይለዋል፡፡
[ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ]
† † †
💖 🕊 💖
👍8❤1
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
● ጥዑመ ልሳን
● ንሕብ
● ሊቀ ሊቃውንት
● የሱራፌል አምሳያ
●የቤተ ክርስቲያን እንዚራ
●ካህነ ስብሐት
●መዘምር ዘበድርሳን
● ማኅሌታይ
● ልዑለ ስብከት ቅዱስ ያሬድ
ነገ ግንቦት ፲፩/11 እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
ይህንን በዓል ምክንያት በማድረግ በግቢ ጉባኤያችን የዝክረ ያሬድ መርሐ ግብር ስለተዘጋጀ ነገ ማለትም ዕለተ ሰኞ 11/09/2017/ ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ታላቅ የቃለ እግዚአብሔር ፤የዝማሬ እና እንዲሁም ለሎችም መርሐ ግብራቶች ተዘጋጅተዋል ። ስለሆነም ሁላችሁም በክፍላችሁ ፤ በንዑስ ክፍላችሁና በለሎችም ግሩፕ ላይ መልእክቱን በማስተላለፍ ተቀሳቅሳችሁ በሰዓቱ እንድትገኙ ስንል በቅዱስ ያሬድ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ከቀኑ 10:00 ጀምሮ።
ቦታ:- በግቢ ጉባኤው ዋና አዳራሽ።
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 ቅዱስ 🌻🌻️
🌻🌻 ያሬድ 🌻🌻
🌻🌻ግንቦት 11🌻🌻️
🌻️🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊
● ንሕብ
● ሊቀ ሊቃውንት
● የሱራፌል አምሳያ
●የቤተ ክርስቲያን እንዚራ
●ካህነ ስብሐት
●መዘምር ዘበድርሳን
● ማኅሌታይ
● ልዑለ ስብከት ቅዱስ ያሬድ
ነገ ግንቦት ፲፩/11 እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
ይህንን በዓል ምክንያት በማድረግ በግቢ ጉባኤያችን የዝክረ ያሬድ መርሐ ግብር ስለተዘጋጀ ነገ ማለትም ዕለተ ሰኞ 11/09/2017/ ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ታላቅ የቃለ እግዚአብሔር ፤የዝማሬ እና እንዲሁም ለሎችም መርሐ ግብራቶች ተዘጋጅተዋል ። ስለሆነም ሁላችሁም በክፍላችሁ ፤ በንዑስ ክፍላችሁና በለሎችም ግሩፕ ላይ መልእክቱን በማስተላለፍ ተቀሳቅሳችሁ በሰዓቱ እንድትገኙ ስንል በቅዱስ ያሬድ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ከቀኑ 10:00 ጀምሮ።
ቦታ:- በግቢ ጉባኤው ዋና አዳራሽ።
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 ቅዱስ 🌻🌻️
🌻🌻 ያሬድ 🌻🌻
🌻🌻ግንቦት 11🌻🌻️
🌻️🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊
❤1🕊1