ደብረ ብርሃን ዩ/የቀን ግቢ ጒባኤ
1.28K subscribers
390 photos
36 videos
45 files
49 links
ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ደ/ብ ማዕከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቀን ግቢ ጒባኤ ይፋዊ የቴሌግራም መገናኛ ነው።
Download Telegram
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
<<እንበለ ደዌ ወህማም፣እንበለ ፃማ ወድካም፣አመ ከመ ዮም ፣ያብጽሀነ ያብፅህክሙ፣ለብርሃነ ትንሣኤ በፍስሀ ወበሰላም።
እንደምን አላችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች?
እንደምታወቀው ሰሞኑን የተጀመረ ትልቅ የበረከት ሥራ አለ ይሄውም የጌታችን፤የመድኀኒታችንና የፈጣሪያችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ መታሰቢያ በዓል ከአቅሜ ደካሞች ጋር አብረን በአንድነት ለማክበር ታቅዶ የበረከት ሥራ ላይ እንገኛለን።ስለሆነም ሁላችንም የግቢ ጉባኤ ልጆች ይህንን ታላቅ የበረከት በዓል በመሳተፍ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደምባል እኛ በሥጋችንም በነፍሳችን ተጠቅመን፤የምስራቹን ቃለ ወንጌል ሰምተን ያዘኑትንም አጽናንተን በዓሉን እንድናሳልፍ በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ:- ለዚህ ሥራ የተመደቡ አካላት በተመደቡበት ቦታ እየሄዱ ብር ይሰበስባሉ እና ግቢ ምታሳልፉ የተባለውን በማድረግ እንድትተባበሩ ወደ ቤተሰብ የምትሄዱ ደግሞ በረከቱ ለእናንተም እንድደርሳችሁ ያላችሁን እንድታበረክቱ እና በጎዳና ወድቀው የሰዎችን እጅ የምጠባበቁትን ለቀናቶች መመገብ ባንችልም እንኳን ለሰዓታት ከእኛ ጋር በትንሣኤው ብርሃን አብረውን እንድደሰቱ ስንል እናሳስባለን!

እየሰጣችሁ  ያላችሁም እግዚአብሔር ይስጥልን እናመሰግናለን🤲!
የደ/ብ/ዩ/ቀ/ግ/ጉ
3
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
ደብረ ብርሃን ዩ/የቀን ግቢ ጒባኤ
Photo
🍂 +  ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጉታላችሁ?  #ተነስቷል_እንጂ_በዚህ_የለም   + 🍂

†††   ክርስቶስ ተንስአ እሙታን!
¤      በዐቢይ ኃይል ወስልጣን!
†††  አሠሮ ለሰይጣን!
¤      አግዐዞ ለአዳም!
†††   ሰላም!
¤      እምይእዜሰ!
†††   ኮነ!
¤       ፍሥሐ ወሰላም


  የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥ እና ሊሰቀል #በሦስተኛውም_ቀን_ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ።
                    ( ሉቃ 24 ፥ 5 , 6 )

    🍀 " ትላንት ይሁዳ ሰረቀ
ዛሬ ደግሞ ጥበቃዎች መማለጃ (ጉቦ) ተቀበሉ ፤
የእውነት ጠላቶች ኪሶቻቸውን በጉቦ አቆሸሹ ፤
ግን እውነቱን መደበቅ አልተቻላቸውም ፤
ኃያሉ ጌታ ራሱን አሳልፎ ሰጠ ፤ደካማ ሰዎች ዙሪያውን ከበቡት  ነጻ ወጥቶ በእነርሱ ላይ በቀልን እንዳያደርግባቸው
ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር ፤ በመቃብር አድሮ ሳለ እንኳን ጠላቶቹን ማንቀጥቀጥ የሚችለው እርሱ ባያስፈራቸው ኖሮ ፤ ስለምን መቃብሩን ይጠብቁት ነበር።"
      ( ድርሳን ዘቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በእንተ ትንሣኤ )

             +    +    +

🌻 "ይእዜኒ ንትለዋ ለሰላም እስመ ተንስዓ ክርስቶስ ዮም በዛቲ ዕለት አክሊሎሙ ለሰማዕት ክብሮሙ ለመላዕክት ወልድ ተንስሥአ ቤዛነ ሥዒሮ ሞተ ወከይዶ ሲኦለ ንግበር በዓለ በትፍሥሕት ተዝካረ ትንሣኤሁ ለመድኃኒነ።"
    
🌹  ዛሬ በዚህች ቀን ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷልና ፤
ከዛሬ ጀምሮ ሰላምን እንከተላት ፤
የሰማዕታት አክሊላቸው ፣
የመላእክት ክብራቸው
ቤዛችን ወልድ ሞትን ሽሮ ሲኦልን ረግጦ ከሞት ተነሣ ፤ የመድኃኒታችን የትንሣኤውን መታሰቢያ
በደስታ በዓልን እናድርግ።
          ( ድጓ ዘፋሲካ )

💥 አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት
#በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል።
ሞት በሰው በኩል ስለመጣ
ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኗል።💥
     
          ( 1ኛ ቆሮ 15 ፥20 - 22 )

                      🙏

ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤

ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና።

ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን፤

ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቶ ወደ ፊት እንዳይሞት ሞትም ወደ ፊት እንዳይገዛው እናውቃለንና።

መሞትን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ለኃጢአት ሞቶአልና፤ በሕይወት መኖርን ግን ለእግዚአብሔር ይኖራል።

እንዲሁም እናንተ ደግሞ ለኃጢአት እንደ ሞታችሁ፥ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ሆናችሁ ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደ ሆናችሁ ራሳችሁን ቁጠሩ።

/ ሮሜ 6 - 5 -11 /

     🍂

    የትንሣኤውን ብርሃን እንድናይ ያደለን፤
ከሞት ወደ ሕይወት ፣ ከባርነት ወደ ነጻነት ፣ ከሲኦል ወደ ገነት                 #በፍቅሩ_ያሻገረን
ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ
                 ምስጋና ይሁን
                         🙏

+🍂 እንኳን  #ለብርሀነ_ትንሣኤው
በሰላም አደረሳችሁ 🍂
          
    +    +      +    +    +   +   +

  የደ/ብ/ዩ/ቀ/ግ/ጉ/
1👍1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን

በአብይ ሐይለ ወስልጣን           
አሰሮ ለሰይጣን

አጋእዞ ለአዳም                        
ሰላም

እምይዜሰ   

ኮነ

ፍስሐ ወሰላም

መልካም በዓል
የድንግል ማርያም ልጅ እየሱስ ክርስቶስ የበረከት የሰላም የጤና የአንድነት የአብሮነት በዓል ያድርግልን ።

እንኳን ለጌታችን፥ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
የደብረብርሃን ዩንቨርሲቲ የቀን ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አብዛኛው ቅዳሴ ቀሪዎቹ ደግሞ ካፌ ላይ የጾም መፍቻ የበረከት ሥራ ላይ ።
ፍቅር+ ጾም + መተሳሰብ + መከባበር +የበረከት ሥራ =ለትንሣኤ በዓል
እንኳን አደረሳችሁ
credited by dani
11👍4🕊1
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም''

''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ''

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም  በጤና አደረሳችሁ አደረሰን በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት ያርግልን።

text መጻፊያው ተከፍቷል መልካሙን ሰላምታ ተለዋወጡ!
👍21
ወደ ሀሳብ መስጫ ለመሄድ ይሄንን ይጠቀሙ
👉https://t.me/dbugg21group
1
ዛሬ የጥዋት መርሐ ግብር በግቢ ጉባኤ ዋና አዳራሽ
10👍2🏆2👏1🕊1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን

በአብይ ሐይለ ወስልጣን           
አሰሮ ለሰይጣን

አጋእዞ ለአዳም                        
ሰላም

እምይዜሰ   

ኮነ

ፍስሐ ወሰላም

መልካም በዓል
የድንግል ማርያም ልጅ እየሱስ ክርስቶስ የበረከት የሰላም የጤና የአንድነት የአብሮነት በዓል ያድርግልን ።

እንኳን ለጌታችን፥ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን🤲🤲🤲

የጥዋት መርሐ ግብ በአጭሩ
1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
''ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው፦ ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።(ሉቃስ24፥5)
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን

በአብይ ሐይለ ወስልጣን           
አሰሮ ለሰይጣን

አጋእዞ ለአዳም                        
ሰላም

እምይዜሰ   

ኮነ

ፍስሐ ወሰላም

የከሰዓት የምሳ program ካፌ
👍3
መርሐ ግብሩ ዛሬ 4:00 ላይ ይጀመራል።
2