ዛሬ ማለትም ዕለተ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት 21/07/2017 ዓ.ም የደ/ብ/ዩ/ቀ/ግ/ጉ/ አስራ ስምንተኛ (18ኛ) ዓመት የግቢ ጉባኤ የምሥረታ በዓል ዛሬ ሦስተኛውን ቀን የያዘ ሲሆን ፤በዚህ ታላቅ ክብረ በዓል ላይ ተጋባዥ መምህራን እና ዘማሪያን፤የደብረብርሃን ማዕከል ማህበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።
በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲሁም በተደረገው ቅስቀሳ መሠረት ከአንድ መቶ ሐምሳ ሦስት በላይ (153) የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂዎችም ተገኝተዋል።
ዛሬ ላይ የነበሩን መርሐ ግብራቶች :
1,በጸሎት መክፈት
2,ዝማሬ
3,ስነ ጽሑፍ
4,በየክፍላቶች ከቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ጋር የልምድ ልውውጥ እና ምክክር
5,ማጠቃለያ በማህበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈፃሚ እና የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪ በሆኑት በዲ/ን ዘውዱ ተሰጥቶ
በመጨረሻም በጸሎት ተዘግቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።
አነሳስቶ ያስጀመረን አስጀምሮም ያስፈጸመን የአባቶቻችን አምላክ አምላከ ቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይሁን።
ለከርሞ እንዲሁ በቸርነቱ ጠብቆ ቸር ያገናኘን።
በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲሁም በተደረገው ቅስቀሳ መሠረት ከአንድ መቶ ሐምሳ ሦስት በላይ (153) የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂዎችም ተገኝተዋል።
ዛሬ ላይ የነበሩን መርሐ ግብራቶች :
1,በጸሎት መክፈት
2,ዝማሬ
3,ስነ ጽሑፍ
4,በየክፍላቶች ከቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ጋር የልምድ ልውውጥ እና ምክክር
5,ማጠቃለያ በማህበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈፃሚ እና የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪ በሆኑት በዲ/ን ዘውዱ ተሰጥቶ
በመጨረሻም በጸሎት ተዘግቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።
አነሳስቶ ያስጀመረን አስጀምሮም ያስፈጸመን የአባቶቻችን አምላክ አምላከ ቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይሁን።
ለከርሞ እንዲሁ በቸርነቱ ጠብቆ ቸር ያገናኘን።
❤11👍6🕊1🏆1
text መጻፊያ ተከፍቷል መልካም ምኞታችሁን ተለዋወጡ ለዓመቱ በሰላም በጠና ያድርሰን❤❤❤❤
ወደ text መጻፊያ ለመሄድ 👉https://t.me/dbugg21group
ወደ text መጻፊያ ለመሄድ 👉https://t.me/dbugg21group
❤3🏆1
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤
ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡
ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡
ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"
/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/
ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡
ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡
ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"
/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/
👍11❤1🕊1