ደብረ ብርሃን ዩ/የቀን ግቢ ጒባኤ
1.28K subscribers
390 photos
36 videos
45 files
49 links
ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ደ/ብ ማዕከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቀን ግቢ ጒባኤ ይፋዊ የቴሌግራም መገናኛ ነው።
Download Telegram
ዛሬ ማለትም ዕለተ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት 21/07/2017 ዓ.ም የደ/ብ/ዩ/ቀ/ግ/ጉ/ አስራ ስምንተኛ (18ኛ) ዓመት የግቢ ጉባኤ የምሥረታ በዓል ዛሬ ሦስተኛውን ቀን የያዘ ሲሆን ፤በዚህ ታላቅ ክብረ በዓል ላይ ተጋባዥ መምህራን እና ዘማሪያን፤የደብረብርሃን ማዕከል ማህበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።
በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲሁም በተደረገው ቅስቀሳ መሠረት ከአንድ መቶ ሐምሳ ሦስት በላይ (153) የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂዎችም  ተገኝተዋል።
ዛሬ ላይ የነበሩን መርሐ ግብራቶች :
1,በጸሎት መክፈት
2,ዝማሬ
3,ስነ ጽሑፍ
4,በየክፍላቶች ከቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ጋር የልምድ ልውውጥ እና ምክክር
5,ማጠቃለያ በማህበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈፃሚ እና የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪ በሆኑት በዲ/ን ዘውዱ ተሰጥቶ
በመጨረሻም በጸሎት ተዘግቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።
አነሳስቶ ያስጀመረን አስጀምሮም ያስፈጸመን የአባቶቻችን አምላክ አምላከ ቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይሁን።
       ለከርሞ እንዲሁ በቸርነቱ ጠብቆ ቸር ያገናኘን።
11👍6🕊1🏆1