ደብረ ብርሃን ዩ/የቀን ግቢ ጒባኤ
1.28K subscribers
390 photos
36 videos
45 files
49 links
ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ደ/ብ ማዕከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቀን ግቢ ጒባኤ ይፋዊ የቴሌግራም መገናኛ ነው።
Download Telegram
ሰላም ወንድም እህቶች እንኮን አደረሳችው !!!የምታሳዩት እንቅስቃሴ በጣም ደስ ይላል አይዞችው በእግዚአብሔር አጋዥነት እናሳካዋለን የምስረታ በእላችንን በእዲሶ ሞንታርቦና በአዲስ አዳራሽ ወለል እናካብራለን!!!የመጽሐፍ ስማቸውን ለኛም አድርሱን ምህላ ስላለን
👍1
ሀ/ገብርኤል ከባች ክፍል
የgroup አችን ሃሳብ መስጫ ተከፍቷል ለተመራቂ እህት ወንድሞቻችን ደስታችሁን ማጋራት ትችላላችሁ 👇👇👇👇
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን አደረሰን እንኳን አደረሳችሁ!

''ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ።(መዝ 122፥1-2)

እኔሆ በጉጉት ስጠበቅ የነበረው
የደብረብርሃን ዩንቨርስቲ
የቀን ግብ ጉባኤ
18ኛ ዓመት
የምሥረታ በዓል
ደረሰ
ይሄውም
ከመጋቢት 19-21/07/ 2017 ዓ.ም
መምህራነ ወንጌል
እንድሁም ዘማሪያን
የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂ ተማሪዎች
በዩኒቨርስቲያችን የምገኙ ሠራተኞች
አሁን ላይ በግቢው የምገኙ ተማሪዎችን ጨምሮ
በአንድነት በታላቅ ድምቀት ይከበራል

ስለሆነም ከመጋቢት 19-21/07/2017 ዓ.ም
በደብረብርሃን ዩንቨርስቲ የቀን ግቢ ጉባኤ አዳራሽ በመገኘት ይህንን ታላቅ በዓል እንድታከብሩ ስትል እናት ግቢ ጉባኤ ጥሪዋን ታስተላልፋለች!

ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን !

የደብረብርሃን ዩንቨርስቲ የቀን ግቢ ጉባኤ
👍118🕊3

መፃጉዕ
የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል (፭፥፪-፱) መፃጉዕ የተባለ አንድ በሽተኛ ለሠላሳ ስምንት ዓመት በደዌ ተይዞ በአልጋ ቁራኝነት የኖረ ሰው በአምላካችን ድንቅ ተአምር እንዴት ፈውስ እንዳገኘ ይተርካል፡፡ የዐቢይ ጾም አራተኛው ሳምንትም ይህን ታሪክ በማውሳት “መፃጉዕ” ተብሎ ይጠራል፡፡ 
ጌታችንም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ በበጎች በር አጠገብ በነበረች መጠመቂያ ቦታ ስሟም በዕብራይስጥ ቋንቋ ‹‹ቤተ ሳይዳ›› ወደ ምትባል ቦታ ደርሶ በዚያ ያሉ ዕውራኖችና አንካሶች፣ ሰውነታቸውም የሰለለ ድውያን ተኝተው የውኃውን መናወጥ ሲጠባበቁ አገኛቸው፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ወደ መጠመቂያው ወርዶ ውኃውን በሚያናውጠው ጊዜ፥ ከውኃው መናወጥ በኋላ በመጀመሪያ ወርዶ የሚጠመቅ ካለበት ደዌ ይፈወስ ነበርና፡፡ በመካከላቸውም ከበሽታው ጽናት የተነሣ ስሙ እንኳን ጠፍቶ በበሽታው ስም “መፃጉዕ” የተባለውን ሰው ጌታችን ተመከተውና ወደ እርሱም ቀርቦ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ በሽተኛውን ጠየቀው፡፡ መጠየቁ ሰውየው መዳን እንደሚፈልግ ሳያውቅ ቀርቶ ሳይሆን ‹‹በዕለተ ዓርብ ፈውሰኝ ሳልል ፈውሶኛል›› ብሎ የሚመሰክርበት ነውና አስፈቅዶ ለማዳን ጠየቀው፡፡ አንድም በድኅነት ውስጥ ሰው የራሱ ሱታፌ እንዳለው ለማስተማር ነው፡፡
ድውዩም ‹‹ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም፤ ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል›› ብሎ መለሰለት። ቸሩ አምላካችንም ‹‹ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ›› አለው። መፃዕጉም ጉልበቱ ጸንቶ ተነሣ፤ አልጋውንም ተሸክሞ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ ፈሪሳውያን ግን ‹‹በሰንበት አልጋህን ተሸክመህ መሄድ እትችልም፤ ፈውስም በሰንበት መሆን የለበትም›› ብለው ተቆጡ፡፡ (ዮሐ.፭፥ ፩-፱)
አይሁድም ‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለህ ሰውዬው ማነው?›› ብለው ጠየቁት፡፡ ያ የተፈወሰው ግን ያዳነው ማን እንደ ሆነ አላወቀም፤ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ቦታ በነበሩት ብዙ ሰዎች መካከል ተሠውሮ ነበርና፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ያን የዳነውን ሰው በቤተ መቅደስ አገኘውና፥ ‹‹እነሆ፥ ድነሃል፤ ግን ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ዳግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ›› አለው፡፡ ያም ሰው ሄዶ ያዳነው ጌታችን ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገራቸው፡፡ ስለዚህም አይሁድ ጌታችን ኢየሱስን ያሳድዱትና ሊገድሉትም ይሹ ነበር፤ በሰንበት እንዲህ ያደርግ ነበርና፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥ ‹‹አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል፤ እኔም እሠራለሁ›› አላቸው፡፡ ስለዚህም አይሁድ ‹‹ሰንበትን የሚሽር ነው፤ እግዚአብሔርን አባቴ ነው ይላል፤ ራሱንም ከእግዚአብሔር ጋር ያስተካክላል›› በማለት ሊገድሉት በጣም ይፈልጉ ነበር፡፡
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹እውነት እውነት እላችኋለሁ፣ ወልድ ከራሱ ብቻ ምንም ሊያደርግ አይችልም፤ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ፤ ወልድም አብ የሚሠራውን ያንኑ እንዲሁ ይሠራል፡፡ አብ ልጁን ይወዳልና የሚሠራውንም ሥራ ሁሉ ያሳየዋል፤ እናንተም ታደንቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ሥራን ያሳየዋል፡፡ አብ ሙታንን እንደሚያስነሣቸው÷ ሕይወትንም እንደሚሰጣቸው እንዲሁ ወልድም ለሚወድዳቸው ሕይወትን ይሰጣል፡፡ አብ ከቶ በማንም አይፈርድም፤ ፍርዱን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ፡፡ ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩ ወልድን ያከብሩ ዘንድ፤ ወልድን የማያከብር ግን የላከውን አብን አያከብርም፡፡›› (ዮሐ.፭፥ ፩-፳፬)
አምላካችንን እግዚአብሔር በመፍራት፣ በማከበር፣ እርሱን በማመን መኖርና ለእርሱ መታመን እንዳለብን እዚህ ላይ እንረዳለን፡፡ አለበለዚያ ግን ፈውሰ ሥጋን ካገኘን፣ ከሕመማችን ከተፈወስንና ከሥቃያችን ከተላቀቅን በኋላ እንደ መፃጉዕ መልሰን አምላካችንን መርሳት አልያም መካድ ይሆናልና በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በእምነት ጸንተን እንኑር!
አምላካችን እግዚአብሔር በቸርነቱ ጸሎታችንን፣ ጾማችንና ንስሐችንን ይቀበለን፤ አሜን!     
ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን!
ኢትዮጵያን በጽኑ ሰላም ይጠብቅልን!!
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
 ደ/ብ/ዩ ቀን ግ/ጉ/ ት/ት እና ሐ/አ/ክ 
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
👍7
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!
የደብረብርሃን ዩንቨርስቲ የቀን ግቢ ጉባኤ 18ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በያዝነው ወር ማለትም መጋቢት 19-21/07/2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
ይህንን የእናት ግቢ ጉባኤ ጥሪ ድምፅ ላልሰሙት በማሰማት የበኩልዎን ድርሻ ይወጡ!
በሰላም ለዚያች ቀን ያድርሰን!
13👍2🕊2
Forwarded from Ďâňĩ Ÿé ďĩňĝĩl21❤
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
11👍2
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ      ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!

      👉 5 ቀን ብቻ ቀረው👈
🌲 "መጋቢት 14 የህይወት ቀን"🌳
እንኳን ለተወደደችው እና ለተመረጠችው የሕይወት ቀን በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
ለመሆኑ የህይወት ቀን ምንድነው????
እስኪ ሁላችንም ይችን ጽሁፍ በማስተዋል እናንብብ👇👇👇👇👇👇👇👇👇
✍️የሕይወት ቀን በግቢ ጉባኤያችን ከሚታወጀው ንስሓ ሳምንት በኋላ የክርስቶስን ስጋ እና ደም በጋራ ሆነን ነጭ ለብሰን እንደመላዕክቱ ደምቀን የምንቀበልበት ቀን ነው ።🙏🙏🙏🙏
👉ጌታችን በቅዱስ ቃሉ ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ›› በማለት እንደተናገረ በህብረት የተቀበልነው ቅዱስ ቁርባን የሕያው አምላክ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም ነውና የዘላለም ሕይወት ባለቤት መሆናችንን ያረጋግጣል፡፡
👉ዳግመኛም ቅርንጫፍ ከግንዱ እስካልተለየ ድረስ ልምላሜ፣ ጽጌና ፍሬ ሕይወት ለዘላለም እንዲኖረው ሁሉ ክርስቲያኖችም ጉንደ ሐረገ ወይን ከሆነው ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አለመለየታችንና በሕይወት መኖራችንን ቅዱስ ቁርባን ስንቀበል እናረጋግጣለን፡፡ (ዮሐ 6፡53፣ ሮሜ 11፡21-24) ሕያዋን የሚያደርጉንም በውስጣችን ያደረው (የተዋሐደን) ሥጋ ክርስቶስና ደመ ክርስቶስ ናቸው።
   ቊርባን  ምን ማለት ነው?

ቊርባን ማለት ቃሉ ከሱርስት የተወሰደ ሲሆን፣ መስዋዕት ማለት ነው። እንዲሁም ቊርባን ሙሉ ትርጉሙ ለአምላክ የሚቀርብ መንፈሳዊ መባዕ ፣ ስጦታ፣ አምኃ፣ ማለት ነው። አንድም ሥጋውና ደሙ የተሰጠን በነፃ ያለ ዋጋ በችሮታ ነውና ቁርባን ስጦታ ይባላል።
ምሥጢረ ቁርባን ክርስቶስ ስለ እኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሥዋዕት ሆኖ በሥጋው በመሞቱ የዓለምን ኃጢአት ያስወገደበት፥ የዘላለም ሕይወትን ያስገኘበት የመዳናችን መሠረት፥ የጸጋችን ሁሉ ምንጭ የሆነውን የቅዱስ ሥጋውንና የክቡር ደሙን የማዳን ስራ የምንማርበት ታላቁ የሃይማኖታችን ትምህርት(ዶግማ) ነው "ለእኔስ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል።" መዝ፤73
🔸ምሥጢረ ቍርባን በብሉይ ኪዳን
👉ከአባታችን አዳም ጀምሮ የነበሩ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን በኃጢአታቸው ከእግዚአብሔር በተለዩ ጊዜ ሁሉ በግና ላምን የመሳሰሉ እንስሳትን በእምነት መስዋዕት አድርገው ያቀርቡ ነበር፤ እግዚአብሔርም መስዋዕታቸውን እየተቀበለ ይታረቃቸው ነበር፡፡ በሕገ ልቡናና በሕገ ኦሪት የነበሩት ሁሉ በዚህ ሥርዓት አልፈዋል፡፡ አበ ብዙሐን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ለመሰዋት ወደ ሞሪያ ተራራ በሚወስደው ሰዓት የክርስቶስ ምሳሌ የሆነ ይስሐቅ አባቱን አብርሃምን የጠየቀው ጥያቄና በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘው የአብርሃም ምላሽ በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን መስዋዕት መካከል ያለውን መሰረታዊ ልዩነት ያስረዳናል፡፡
🔸በዘመነ ብሉይ መስዋዕቱ ምድራዊ፣ አቅራቢውም ምድራዊ ነው፡፡ ይስሐቅ እንደተለመደው የመስዋዕት በግ እንዳልተያዘ ባየ ጊዜ “አባቴ ሆይ…እሳቱና እንጨቱ ይኸው…የመሥዋዕቱ በግ ግን ወዴት አለ?” በማለት ጠይቆት ነበር፡፡ በአብርሃም ህሊና የመሥዋዕቱ በግ ይስሐቅ ነበር፡፡ ይሁንና መንፈስ ቅዱስ እንዳቀበለው “ልጄ ሆይ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል፡፡” በማለት መለሰለት፡፡
🔸ሚሥጢረ ቁርባን በሐዲስ ኪዳን
  👉ምስጢረ ቁርባንን የመሠረተው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስ ‹‹ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራውን አንስቶ ባረከ፤ ቆርሶም ለደቀመዛሙርቱ ሰጠና እንካችሁ ብሎ ይህ ሥጋዬ ነው አለ፡፡ ጽዋውንም አንስቶ አመስግኖ ሰጣቸው፡፡ ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለብዙዎች የኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የሐዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው፡፡›› (ማቴ 26፡26) በማለት የምስጢረ ቁርባንን አመሠራረት ጽፎታል፡፡ አስቀድሞ በብሉይ ኪዳን ሲቀርቡ የነበሩ መስዋዕቶችን ሁሉ ምሳሌው አድርጎ በማሳለፍ የራሱን መስዋዕትነት ካቀረበ በኋላ ቀድሞ የነበሩትን ነፍሳት ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድርስ የሚመጡትን ሁሉ አንድ ጊዜ ባቀረበው መስዋዕት የሚያድን ስለሆነ ምስጢሩ ይፈጸም ዘንድ ከሞቱ አስቀድሞ አስተማረ፡፡
👉‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው››ዮሓ፤፮፤፭፬ በማለት እስከዓለም ፍጻሜ የሰው ልጅ ሌላ መስዋዕት ሳያስፈልገው በአምላካችን ሥጋና ደም ሕይወት እንደሚያገኝ አስተማረ፡፡  የምስጢረ ቁርባንን ትምህርት በወቅቱ የነበሩ አይሁድ ሰምተው ምስጢሩ ስላልገባቸው ‹‹ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይቻላል›› በማለት ጠይቀው ነበር፡፡ ደቀመዛሙርቱም ትምህርቱ ከብዷቸው ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ምስጢሩን ተረድተው አለምን ዞረው ወንጌልን አስተምረዋል…።
ከምስጢረ ቁርባን መሳተፍ የሚያስገኘው ጸጋ ምንድነው??

👉ቅዱስ ቁርባን የዘላለም ሕይወት ያሰጠናል፡፡ጌታችን በማይታበል አማናዊ ቃሉ ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ›› በማለት እንደተናገረ የተቀበልነው ቅዱስ ቁርባን የሕያው አምላክ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም ነውና የዘላለም ሕይወት ባለቤት መሆናችንን ያረጋግጣል፡፡
👉ሥርየተ ኃጢአትን ያስገኛል፡፡
አባቶቻችን ‹‹ሰው ሆኖ የማይበድል እንጨት ሆኖ የማይነድ የለም፤ ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት አይጠፋም›› እንዲሉ ደካማና ስሑት የሚሆን ሰብአዊ ባሕርያችን ወደ ስህተት ጎዳና ሲነዳንና ኃጢአት ሲያገኘን በደላችንን ለካህን ተናዝዘን፣ ቀኖና ተቀብለንና ንስሐችንን ጨርሰን በካህኑ ፈቃጅነት ቅዱስ ቁርባንን ስንቀበል የቀደመ ኃጢአት በደላችን ሁሉ እሳት ላይ እንደወደቀ ቅቤ ቀልጦ ጠፍቶ ነጻ ያደርገናል፡፡
👉የኃጢአት ልጓም ሆኖ ያገለግለናል፡፡
ሥጋው ለኃጢአት የሚጓጓና የሚሰነካከል እንዳይሆን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ይጠብቀዋል፡፡ በሥጋውና በደሙ የተዋሐደው አምላክ ኃጢአትን ተደፋፍሮ እንዳይሠራ ይወቅሰዋል፡፡ የኃጢአት ውጤት ሞት መሆኑን ያሳስበዋል፡፡ በአጠቃላይ ወደ ቅድስናና ጽድቅ የሚመራ መንፈሰ እግዚአብሔር ስለተዋሐደን ለጽድቅ ሥራ የምንተጋ ለኃጢአት እጅ የማንሰጥ እንሆናለን፡፡
፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣,,,፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣,,,፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ወስብሃት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር...ይቆየን!!!
፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣,,,፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣,,,፣፣፣፣፣፣፣፣
     🌈 መጋቢት፡10/07/2017🪐
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
  ደ/ብ/ዩ ቀን ግ/ጉ ት/ት እና ሐ/አ/ክ
💚💛❤️▰▰▰▰▰▰❤️💛💚
👍201🏆1
እንኳን አደረሰን እንኳን  አደረሳችሁ!

''ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ።(መዝ 122፥1-2)

እኔሆ በጉጉት ስጠበቅ የነበረው
የደብረብርሃን ዩንቨርስቲ
የቀን ግብ ጉባኤ
18ኛ ዓመት
የምሥረታ በዓል
ደረሰ
ይሄውም
ከመጋቢት 19-21/07/ 2017 ዓ.ም
መምህራነ ወንጌል
እንድሁም ዘማሪያን
የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂ ተማሪዎች
በዩኒቨርስቲያችን የምገኙ ሠራተኞች
አሁን ላይ በግቢው የምገኙ ተማሪዎችን ጨምሮ
በአንድነት በታላቅ ድምቀት ይከበራል

ስለሆነም ከመጋቢት 19-21/07/2017 ዓ.ም
በደብረብርሃን ዩንቨርስቲ የቀን ግቢ ጉባኤ አዳራሽ በመገኘት ይህንን ታላቅ በዓል እንድታከብሩ ስትል እናት ግቢ ጉባኤ ጥሪዋን ታስተላልፋለች!

ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን !

የደብረብርሃን ዩንቨርስቲ የቀን ግቢ ጉባኤ
👍73👏2🕊1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
🌲🌷🌳🌳🌷🌳🌳🌷🌷🌳🌲       
✍️ይነበብ 👇👇👇👇👇
👉ላለመቁረብ የሚቀርቡ ተገቢ ያልሆኑ         ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸው 👈

🍃ቀስ ብዬ እደርሳለሁ ፣ ምን አስቸኮለኝ?
ያዕ. 4 ÷ 13-15 -አሁንም። ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና። ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።
🍂ወደፊት ብሳሳትስ፣ ብወድቅስ?
1ኛ.ዬሐ. 5 ÷3-4
💨ሀጢያተኛ ስለሆንኩ አይገባኝም
ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።(ኢሳ 1:9) 
መድኃኒት የሚያስፈልገው ለታመመ ነው።
💥በስራ ቦታዬና በማህበራዊ ኑሮዬ ተፅዕኖ ቢያመጣብኝስ?
ቲቶ. 2 ÷ 7-8 -የሚቃወም ሰው ስለ እኛ የሚናገረውን መጥፎ ነገር ሲያጣ እንዲያፍር፥ በነገር ሁሉ መልካምን በማድረግህ ምሳሌ የሚሆን ራስህን አሳይ፤ በትምህርትህም ደኅንነትን፥ ጭምትነትን፥ ጤናማና የማይነቀፍ ንግግርን ግለጥ....
🌿የቅዱስ ቁርባን ዝግጅት🌿

ቅድመ ቊርባን
​​ከመቁረባችን በፊት ሊደረጉ የሚገባቸው ቅድመ ዝግጅቶች/ነገሮች
1) ንስሐ መግባት

🔸እራስን ለካህን ማሳየት/ ማስመርመር፣ ቀኖና ተቀብሎ በሚገባ መፈጸም ይገባናል፡፡ ንስሐ ሳይገባ በድፍረት መቀበል ግን እንደ በደል ይሆንብናልና፡፡ 1ኛ ቆሮ. 11፡27
2) ስጋዊ ንጽህና  መጠበቅ
🔸ሰውነትን መታጠብ /ከቁርባን በፊት ያለው ቀን ላይ /
🔸ካለን ነጭ ልብስ  ፤ ከሌለን ንጹሕ ልብስ መልበስ/ነጭ ልብስ የምንለብሰው በመንግስተ ሰማያት የምንኖረው ሕይወትን ለማሰብ ነው።/
🔸 ነጠላ ማጣፋት
3) ከመቁረባችን  ከሶስት ቀን በፊት ከግብረ ስጋ ግንኙነት መታቀብ /መከልከል/
4) አፋችንን እሬት እሬት እስኪለን ድረስ መጾም
🔸ለአስራ ስምንት ሰዓታት/ የክርስቶስን መከራ፣ ሕማማተ መስቀል አሰብን የሚያሰኘንም ከበረከቱ የሚያሳትፈንም ይህ ነውና/
🔸ከምግብ፣ ከውሀ፣ ገላን ከመታጠብ፣ ጥርስን ከመቦረሽ፣ ጥፍርን/በጸጉርን ከመሰራት/ከመቆረጥ፣ ልብስ ከማጠብ፣ ከማንኛውም ወደ አፍ ከሚገቡ ነገሮች መጠበቅ ያስፈልጋል።
5) አካል ላይ ከሚደርስ ማንኛውም አደጋ መጠበቅ(እንቅፋት፣ቁስል፣ነስር፣አፍ የሚገባ ትንኝ ፣ ዝንብ፣ መድማት...)
6) ለወንዶች ዝንየት/ ህልመ ለሊት ፤ ለሴቶች የወር አበባ ከታየ በዚያን ቀን ስጋ ወደሙን መቀበል ክልክል ነው፡፡
ጊዜ ቊርባን
በቁርባን ቀን እና ጊዜ ሊደረጉ የሚገባቸው ነገሮች
🔸ከኪዳን በፊት ጀምሮ ቤ/ክ መገኘት እና ቅዳሴ መፈጸም
🔸 ጸሎት
🔸አፍን በመጎናጸፊያ(በነጠላ) መሸፈን
🔸ቅዱስ ቁርባን ከተቀበሉ በላ ወዲያው ቅዳሴ ጠበል መጠጣት አይገባም ቆመው ያስቀደሱበት ቦታ በመሄድ ድርገት እስኪመለስ ድረስ መቆም ይገባል።
🔸 ከቤተ መቅደስ ሳይጋፋ በቀስታ ወጥቶ በደጀ ሰላም ዛቲ ቀምሶ አፍን ማደፍ ይገባል።
ድኅረ ቊርባን
ከቊርባን በኃላ ሊደረጉ የሚገባቸው ነገሮች
🔸ከንግግር መቆጠብ( በምግብ አፍን እስከሚያድፉ)
🔸 በእርጋታ መንቀሳቀስ
🔸በውሃ መታጠብ አይፈቀድም ስለዚህ ለንጽህና ሶፍት መጠቀም
🔸ትንፋሽን እፍ ብሎ አለማውጣት
🔸ማንኛውንም ነገር አለመትፋት(ምራቅ ፣ምግብ...)
🔸አለመራቆት-እስከ ማታ በለበሱት መፅናት ይገባል።
🔸አብዝቶ አለመመገብ፣አለመጠጣት
🔸 ነገር እና መንገድ አለማብዛት
🔸 ቢቻል በአንድነት ሆኖ መንፈሳዊውን ነገር እየተጨዋወቱ መቆየት ፤
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
እግዚአብሔር በቸርነቱ ለዚህ ክብር ያብቃን!!!
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
🌱መጋቢት 11/07/2017 ዓ.ም🌱
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ 
ደ/ብ/ዩ ቀን ግቢ ጉባኤ ት/ት እና ሐ/አ/ክ
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
👍25
ሁሉም ክፍላቶች ከነገ ማለትም ዕለተ ዓርብ 12/07/2017 ዓ.ም ጀምረው እስከ ቀጣይ ማክሰኞ እና ረቡዕ ድረስ ለተመራቂ ተማሪዎች ወይም ቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን አባል ለነበሩት ልጆቿ በተቻለ መጠን ለሁለተኛ ግዜ ቅስቀሳ እንዲደረግ የማስታወቂያ እና ቅስቀሳ ክፍል አሳስቧል።

በቅስቀሳውም ወቅትም በየክፍሉ በመዞር እና በመደወልም መረጃ የሚሰበስቡ አካላት እንዳሉ ጠቅሰው በመጨረሻም በተሳካ ቅስቀሳ ብዙ አባል ያስመዘገቡ ክፍላቶች ልዩ ሽልማት እንደምዘጋጅላቸውም ጠቁመዋል።
👍13🏆8
ነገ ማለትም ቅዳሜ 13/07/2017 ዓ.ም ጠዋት ከ 3:00-6:00 የበረከት ሥራ ስላለ ሁላችንም የግቢ ጉባኤ አባል ተቀሳቅሰን በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ እንድንሆን በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን!
👍8👏2
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ዕለተ ቅዳሜ ቀን 13/07/2017 ዓ.ም

የሳምንቱ መርሐ ግብር


ቅዳሜ

ጠዋት ከ 3:00-6:00 የበረከት ሥራ ስላለ ሁላችሁም ተቀሳቅሳችሁ እንድትመጡ ።
ከሰዓት ከ10:00-12:00 የክፍላት ውይይት።

እሁድ

ከ8-10ሰዓት ለ2ኛ ዓመት ክርስቲያናዊ ህይወት እና ስነምግባር ኮርስ ቦታ አዳራሽ ።
ከ8-10 ሰዓት ለ4ኛ እና 5ኛ ዓመት ነገረ ቤተክርስቲያን ኮርስ ቦታ ቤዝመንት።
ከ10-12ሰዓት ለ1ኛ ዓመት ሀይማኖት እና ሳይንስ ኮርስ ቦታ አዳራሽ ።
ከ10-12ሰዓት ለ3ኛ ዓመት የቤተክርስቲያን ታሪክ ኮርስ ቦታ ቤዝመንት።

ሰኞ

ከ12:15-1:30 መዝሙር ጥናት ።
ከሰዓት ከ11-12 ሰዓት ከአባል ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ ምሰጥበት ቀን ነው።
ማክሰኞ

ጠዋት ከ12:15-1:30 መዝሙር ጥናት ።
ከሰዓት ከ11:00-12:00 መዝሙር ጥናት ።
ረብዕ

ጠዋት ከ12:15-1:30 የአዳራሽ ጽዳት ስለምንኖር ሁሉም የግቢ ጉባኤው አባል እንድገኝ።
ከሰዓት ከ11-12 ሰዓት የህይወት ትምህርት ።

ሐሙስ

ጠዋዉ ከ12:15-1:30 ቅዳሴ ተሰጥኦ ።
ከሰዓት ምንም አይነት መርሐ ግብር አይኖርም።
ዓርብ

ጠዋት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ስለሆነ  ምንም አይነት መርሐ ግብር አይኖርም ።
ከሰዓት ከ10:00-12:00 የዓርብ ጸሎት ከምመጡ እንግዶች ጋር በአንድነት የምናደርስበት እና በተጋባዥ መምህራን ት/ት የምሰጥበት ቀን ነው።

አብነት ትምህርት በነበረበት ይቀጥላል ከቅዳሜ ውጭ!
     
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።
👍32😭1
እነዚህ በደብረብርሃን ዩንቨርስቲ በቀን ግቢ ጉባኤ ለ18ኛ ዓመት ለግቢ ጉባኤያችን የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የተዘጋጁ ናቸው ሁላችሁም እየገዛችሁ ይህንን ታላቅ በዓል በድምቀት ከምመጡ እንግዶቻችንም ጋር በአንድነት እናከብራለን።
በፈለጋቹት size ታገኛላችሁ
1,medium
2,large
3,xxl
አለላችሁ በየክፍል ተጠሪዎቻችሁ በኩል
ወይም ደግሞ በግቢ ጉባኤው ልማት ሱቅ አካባቢ ይገኛል።
ባሉበት ሁነው ይዘዙን እናደርሳለን :-+251924275669

ዋጋ=300 ብር ብቻ
3👍2
አራት ቀናቶች ብቻ ቀሩት!!!
የግቢ ጉባኤያችን የ18ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል አራት ቀናቶ ብቻ ቀርተውታል
ሁላችንም በዓሉ የደመቀ እና የተሳካ እንድሆን የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
በተቻለ መጠን ለቀድሞ ተማሪዎቻችን መደወል ከዛም መልዕክት (text) በመላክ ማስታወስ ከእኛ የምጠበቅ ነገር ነው
በመቀጠል ይህንን ባነር ሁላችሁም የግቢ ጉባኤ ልጆች profile በማድረግ ድባቡን አድምቁት።
ይህ የእናት ግቢ ጉባኤ የጥሪ ድምፅ ነው ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን።
5👍2🕊2🏆1