Dilla Don Bosco Catholic Secondary School
1.66K subscribers
2.02K photos
29 videos
20 files
276 links
Download Telegram
‎የ2018 ዓ.ም የአንደኛ መንፈቅ አመት አንደኛ የሚድ ተርም እና የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ተጀመረ።

‌‎ዲላ፣ ህዳር 8፣ 2018 ዓ.ም (ዶን ቦስኮ ኢ.ቴ.ማ)

‎የት/ቤታችን የ2018 ዓ.ም ከ9-11ኛ ክፍል የሚድ ተርም እና የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና በዛሬው እለት ተጀምሯል።

‎በጠዋቱ መርሀ ግብር 10ኛ እና 12ኛ ክፍል እንዲሁም በከሰዓቱ መርሀ ግብር 9ኛ እና 11ኛ ክፍሎች ይፈተናሉ። የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ሲባል በ14 ክፍሎች እስከ 25 ተማሪዎች ብቻ ተደልድለው ይፈተናሉ።

‎ፈተናው ለ አምስት ቀናት ይሰጣል። በዘንድው አመት ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በ12 ክፍሎች 354 ወንዶች 362 ሴቶች በድምሩ 716 ተማሪዎች በት/ቤቱ ውስጥ ይማራሉ።

‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል

‎ለተጨማሪ መረጃ የትምህርት ቤታችንን የማህበራዊ ድህረ ገፆች ይጠቀሙ:

#ፌስቡክ:
https://m.facebook.com/groups/715959666071910/?ref=share&mibextid=NSMWBT

#ቴሌግራም:
https://t.me/dbict

#ዩቱብ:
https://www.youtube.com/@DBICTC

#ኢሜል:
‎donboscohsdilla@gmail.com

#ቴሌግራም_ቦት
@DonBHS_bot

#ዋትስ_አፕ
https://whatsapp.com/channel/0029Vaa2AUE6buMFIk04MO29
4👍4🤝41
የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል?

📌 "Crazy day፣ olds day፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል።

#Ethiopia | መመሪያው በመንግስት፣ መንግስታዊ ባልሆኑ፣ የግል፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።

በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል።

የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል።

በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል።

በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል።

በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል።

በተጨማሪም በረቂቁ በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች (Crazy Day, Gentle Day, Olds Day, Baby Day, Fruit Day, Tomato
Day, Valentine Day, April the full, Color Day, Pyjama Day…etc) መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል።

የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል።

የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል።

የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል።

መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል።

በተጨማሪ መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በመመሪያው ላይ ምክረ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች በ https://forms.gle/R72ai6EiMnzZtGsC6 እንዲያቀርቡ ጠይቋል።

#TikvahethMagazine
😐76🤝3
ሴት ተማሪዎች አርቴፊሻል ነገር ማድረግ አይችሉም!

📌ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም መቀባት፣ ቅንድብ መቀንደብና መኳኳል፣ አላስፈላጊ ጌጣ ጌጦችን አድርጎ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ የሚከለክል መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጀ፡፡

#Ethiopia | ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ማንኛውም ተማሪዎች ከተፈጥሮ ጸጉራቸው በስተቀር አርቴፊሻል ፀጉር መቀጠል አይችሉም ተብሏል፡፡

ከዚህ ባለፈም በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ በዓላት በተለይም እንደ ክሬዚ ዴይ፣ ኦልድ ዴይ፣ ቤቢ ዴይ፣ ቶማቶ ዴይ፣ ከለር ዴይ፣ ቫላንታይን ዴይ እና ሌሎችም የበዓል ቀናቶች ተብለው የሚከበሩ በዓላት ማክበር በመመሪያው ተከልክሏል፡፡

በትምህርት ቤት የደንብ ልብስ በተገቢ መንገድ መልሰብ ሲል ባወጣው መመሪያ ስር ሴቶች ጉርድ ቀሚስ ከባት በታች የሆነ ቁመት ያለው ለብሶ መገኘት አለባቸው ተብሏል፡፡

ከደንብ ልብስ ውጪ ቢሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን አለባበስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል ይላል ረቂቅ መመሪያው፡፡

ትምህርት ቤት ውስጥ መፈፀም የተከለከሉ ድርጊቶች ብሎ ከዘረዘራቸው መካከል ደግሞ የትምህርት ቤቱን መምህራን፣ የትምህርት አመራር፣ ሠራተኞችና ሌሎች የትምህርት ማህበረሰብ አካላትን መዝለፍ፣ መስደብ፣ ማንቋሸሽና አካላዊ ጥቃት መፈጸም ቅጣት የሚያስከትል ተግባር ነው ተብሏል፡፡

ተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም ሞባይል እና የሙዚቃ ማዳመጫ መሣሪያዎችን ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይዞ መገኘት ረቂቅ መመሪያው ከልክሏል፡፡

በቃል፣ በምልክትም ሆነ በጽሑፍ ፀያፍ ነገሮችን መግለፅ፤ ጨዋነት የጎደላቸውን እንዲሁም ሐይማኖታዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ምስሎችና ጽሑፎች በትምህርት ቤት ውስጥ ይዞ መገኘትና ማሰራጨት አይፈቀድም፡፡

በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ የማንኛውንም ዓይነት የኃይማኖት አምልኮ ሥርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማካሄድ ይከለክላል፡፡

ማንኛውም ተማሪ አገራዊ እሴት ያልሆኑና መጤ የሆኑ ነገሮችን በሰውነት ላይ ምልክት ማድረግ፤ ከአገራዊ እሴት ጋር የሚቃረኑ አሉታዊ መጤ ምልክቶችን በሰውነት ላይ መነቀስ፣ ማሳየት፣ ማድረግ፣ መጠቀም ፍፁም የተከለከለ ነው ብሏል ረቂቅ መመሪያው፡፡

ከ9 እስከ 12ተኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች አንድ ተማሪ በሥነ-ምግባር ጉድለት እጅ ከፍንጅ ከተያዘና የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚያውክ ሆኖ ከተገኘ ውሳኔ እስኪሰጠው ከትምህርት ቤት ሊታገድ እንደሚችልም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡

ተማሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት አጥፍተው ሲገኙ በተለይም ከ7 እስከ 12ተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች እስከ 1 ዓመት ድረስ እንደ ጥፋቱ መጠን ታይቶ ከትምህርት ሊታገዱ ይችላልም ሲል ረቂቅ መመርያው አስቀምጧል፡፡

በሌላ በኩል በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀረበ ረቂቅ ደንብ ተሰናድቷል፡፡

በዚህ ረቂቅ ደንብ ትምባሆ(ሲጋራ፣ ሺሻ)፣ ጫት፣ አልኮል የናርኮቲክ እና ሳይኮትሮፒክ ዝርያ ያላቸው አደገኛ ህገ ወጥ መድኃኒቶች እና ሱስ አስያዥ ዕፆች ትምህርት ቤት አካባቢ መሸጥም ሆነ ይዞ መገኘትን ይከለክላል።

የአልኮል መሸጫ እና ማከፋፈያ ቤቶች፣ የሲጋራ መሻጫ ሱቆች፣ ሺሻ ቤቶች፣ ጫት መሸጫና መቃሚያ ቤቶች፣ ጭፈራ ቤቶች፤ ቁማር ቤቶች፤ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች እና የሰውነት መታሻ ወይም ማሳጅ ቤቶች በትምህርት ቤቶች በ500 ሜትር ርቀት ውስጥ መክፈት አይቻልም፡፡

ፊልም ማጫዎቻ ቤቶች፣ ፕሌይ ስቴሽን ቤቶች፣ ዲ.ኤስ.ቲቪ ቤቶች፣ ከረንቡላ፣ ፑል፣ ጆተኒ፣ ቢንጎ እና የስፖርት ቁማር መጫወቻ ቤቶችም በትምህርት ቤት አቅራቢያ መክፈትን ከልክሏል ሲል ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።
9👏4😐4👌2🤝1
‎የ2018 ዓ.ም 8ኛው ዙር የኮዲንግ ስልጠና ተጀመረ

‎ዲላ፣ ህዳር 13፣ 2018 ዓ.ም  (ዶን ቦስኮ ኢ.ቴ.ማ)
‎ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 7ዙሮች ከ300 በላይ ተማሪዎችን ያሰለጠነው የቦስኮ ኮዲንግ አካዳሚ በዛሬው እለት 8ኛ ዙር ስልጠናውን በይፉ ጀምሯል።

‎በስልጠናው ለመሳተፍ 60 ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን በተለያዩ የግል ፕሮግራም ያልተገኙ ተማሪዎች እንዳሉ ሆነው በዛሬው እለት 37 ተማሪዎች ስልጠናውን ለመከታተል በማዕከሉ ተገኝተዋል።

‎ስልጠናው አምስት ወራትን የሚወስድ ሲሆን ዘወትር ቅዳሜ ጠዋት ከ2:30-5:30 ይሰጣል።

‎በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር በሁለት የኮምፒውተር ማዕከላት አምስት ኮርሱች ተካተዋል ስልጠናው ይሰጣል።


‎በዚህ ዙር በተለየ ሁኔታ 18 ሰልጣኞች በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ዲላ አጥቢያ ድጋፍ ሰጭነት ስልጠናውን እንዲከታተሉ ተደርጓል። በዚህም ቤተክርስቲያኒቱ ተማሪዎች የዘመኑን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆኑ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለምታደርገው ጥረት ምስጋና ሊቸራት ይገባል።

‎ከስልጠናው ጎን ለጎን ለሰልጣኞች በቂ ግንዛቤ በመስጠት የ5ሚሊዮን ኮደርስ የኦንላይን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል።

‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል።
6👍1👌1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ኢቲቪ የልጆች አለም ቻናል በዲላ ዶን ቦስኮ ት/ቤቶች ያደረገው ቆይታ። ቅዳሜ ከ8:00 ጀምሮ ይተላለፉል።
👌42😐2
#ከ# 1.7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የ 5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት ወስደዋል፡፡

እርስዎም ስልጠናውን በነጻ በመውሰድ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ይቀበሉ።

የስልጠና ዘርፎች፦

🌐 ዌብ ፕሮግራሚንግ
🤖 አንድሮይድ ማበልፀግ
📊 ዳታ ሳይንስ
🧠 አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ

ይመዝገቡ 👇
https://www.ethiocoders.et/

በ 8 ሳምንታት ውስጥ ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ፥ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፊኬት ያገኛሉ።
3👌1
‎ማስታወቂያ

‎ለት/ቤታችን መምህራን እና ተማሪዎች

‎መደበኛ የመማር ማስተማር ስራ ነገ እሮብ ህዳር 24/2818 ዓ.ም የሚኖር መሆኑን እየገለፅን ለትምህርት አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ በተለመደው ሰዓት ት/ቤት እንድትገኙ እንገልፃለን።

‎የት/ቤቱ አስተዳደር
😐16👌7🕊5🤝21
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
50ኛ ዓመት ዶን ቦስኮ ሳሊዛውያን በኢትዮጵያ ዶክመንተሪ ቪዲዮ (ሁለተኛ ቤት ዲላ)
6👌1
‎ዜና እረፍት
‌‎የቀድሞ የትምህርት ቤታችን ተማሪ የነበረው #ያብስራ_ጌትነት በድንገተኛ የመኪና አደጋ ከዚህ አለም በሞት ተለይቶናል።

‌‎ፈጣሪ ነፍሱን ይማርልን ለቤተሰቦቹ እና ጓደኞቹ መፅናናትን እንመኛለን።

‎የት/ቤቱ አስተዳደር
🕊88🙏33👌1
የምስራቅና የመካከለኛ ሀገራት የፖን አፍሪካ የተማሪዎች እግር ኳስ ውድድር በዩጋንዳ ካምፖላ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።
በኡጋንዳ አስተናጋጅነት የአፍሪካ የትምህርት ቤቶች እግር ኳስ ውድድር ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ሀገራችን ኢትዮጵያ ባካሄደችው ጨዋታ ከምድቧ ፍፁም የበላይነቷን አረጋግጣ በሁለቱም ጾታዎች ለዋንጫ አልፋለች ።

በውድድሩ በአጠቃላይ ከምድቧ 1ኛ ሆና ያለፈችው ኢትዮጵያ ዛሬ ማክሰኞ በሁለቱም ፆታዎች ለዋንጫ የምትጫወት ይሆናል።
ሀገራችን የወከሉ ታዳጊ ተማሪዎችም መልካም እድል እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
5🏆2