Dilla Don Bosco Catholic Secondary School
1.67K subscribers
2.02K photos
29 videos
20 files
276 links
Download Telegram
‎የቦስኮ ኮዲንግ ክበብ አባላት የተሰጣቸውን የድረ ገፅ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ በማጠናቀቃቸው የገንዘብ እና ሰርተፍኬት ሽልማት ተሰጣቸው።

‎ዲላ፣ ጠቅምት 20፣ 2018 ዓ.ም  (ዶን ቦስኮ ኢ.ቴ.ማ)
‎በት/ቤቱ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የኮዲንግ ስልጠና የወሰዱ ተማሪዎችን እና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ እና ተጓዳኝ የትምህርት መስኮች ለማጥናት ፍላጎት ያላቸውን ለመደገፍ በማሰብ የተቋቋመው #ቦስኮ_ኮዲንግ ክበብ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

‎በክበቡ ውስጥ 30 አባላት የክፍል ደረጃቸው ከ9-12የሆኑ ተማሪዎች ይገኛሉ።

‎በ2017 ዓ.ም በድረ ገፅ ግንባታ በቡድን ሆነው እንዲሰለጥኑ በማድረግ አራት ፕሮጀክቶችን በአራት ቡድኖች እንዲሰሩ ተደርጓል።

‎በቡድን ጥሩ አፈፃፀም ያላቸው እና የተሰጣቸውን ፕሮጀክት ስራ በጥሩ ሁኔታ ለሰሩ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃ ላገኙ የክበቡ ቡድን አባላት በዛሬው እለት የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት እና አንደኛ ደረጃ ለወጣው ቡድን ሰርተፍኬት በተጨማሪነት ተሰጥቷል።

‎አስር ሺህ ብር ገንዘቡን ድጋፍ ለክበቡ ያደረገው የቀድሞ የትምህርት ቤታችን ተማሪ የነበረው #ነብዩ_ኤልያስ ነው።

‎ላደረገልን ድጋፍ በክበቡ አባላት ስም ከልብ አመሰግናለሁ።


‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ።
8👌2👏1
‎ማስታወቂያ

‎ለኮዲንግ ስልጠና ፈላጊዎች

‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ለ8ኛ ዙር የኮዲንግ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል።

▶️ የክፍል ደረጃ: ከ6ኛ እስከ 10 ኛ ክፍል
▶️ የምዝገባ ቀናት: ከሰኛ ጥቅምት 24 ጀምሮ
▶️ የምዝገባ ቦታ: በት/ቤቱ ኢኮቴ ማዕከል እና ኦንላይን
▶️ ስልጠናው የሚሰጠው: ዘወትር ቅዳሜ ጠዋት
▶️ ስልጠናው የሚወስደው ጊዜ :አምስት ወራት

‎ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ


‎ለበለጠ መረጃ: 0911984389
‎ቴሌግራም: @anduict
‎ኢሜል: andutsega@gmail.com

‎ስልጠናው ቅዳሜ ህዳር 6/2018 ዓ.ም ይጀምራል

‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ።

‎በሚከተለው የጎጉል ፎርም በኦላይን መመዝገብ ይቻላል

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSez0eOwB7nMFVbuBmf59Olv4p5PnYxQgztdss3KRZibW0jyXw/viewform?usp=header
5🎉1👌1
ማስታወቂያ

‎ለ8ኛ ዙር የኮዲንግ ስልጠና የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ከዚህ በፊት ቅዳሜ ሕዳር 6/2018 ዓ.ም ይጀምራል የተባለው ስልጠና በሚድ ተርም ፈተና ምክንያት ወደ ቅዳሜ ሕዳር 13/2018 ዓ.ም የተሸጋገረ መሆኑን እንገልፃለን።

‎እስከ አሁን ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች ውስን ቦታ ስላለ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

‎የዲላ ዶን ቦስኮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል።

በኦንላይን ለመመዝገብ የጎጉል ፎርሙን ተጠቀሙ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSez0eOwB7nMFVbuBmf59Olv4p5PnYxQgztdss3KRZibW0jyXw/viewform?usp=header
2👍1
‎የ2018 ዓ.ም የአንደኛ መንፈቅ አመት አንደኛ የሚድ ተርም እና የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ተጀመረ።

‌‎ዲላ፣ ህዳር 8፣ 2018 ዓ.ም (ዶን ቦስኮ ኢ.ቴ.ማ)

‎የት/ቤታችን የ2018 ዓ.ም ከ9-11ኛ ክፍል የሚድ ተርም እና የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና በዛሬው እለት ተጀምሯል።

‎በጠዋቱ መርሀ ግብር 10ኛ እና 12ኛ ክፍል እንዲሁም በከሰዓቱ መርሀ ግብር 9ኛ እና 11ኛ ክፍሎች ይፈተናሉ። የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ሲባል በ14 ክፍሎች እስከ 25 ተማሪዎች ብቻ ተደልድለው ይፈተናሉ።

‎ፈተናው ለ አምስት ቀናት ይሰጣል። በዘንድው አመት ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በ12 ክፍሎች 354 ወንዶች 362 ሴቶች በድምሩ 716 ተማሪዎች በት/ቤቱ ውስጥ ይማራሉ።

‎የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል

‎ለተጨማሪ መረጃ የትምህርት ቤታችንን የማህበራዊ ድህረ ገፆች ይጠቀሙ:

#ፌስቡክ:
https://m.facebook.com/groups/715959666071910/?ref=share&mibextid=NSMWBT

#ቴሌግራም:
https://t.me/dbict

#ዩቱብ:
https://www.youtube.com/@DBICTC

#ኢሜል:
‎donboscohsdilla@gmail.com

#ቴሌግራም_ቦት
@DonBHS_bot

#ዋትስ_አፕ
https://whatsapp.com/channel/0029Vaa2AUE6buMFIk04MO29
4👍4🤝41
የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል?

📌 "Crazy day፣ olds day፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል።

#Ethiopia | መመሪያው በመንግስት፣ መንግስታዊ ባልሆኑ፣ የግል፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።

በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል።

የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል።

በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል።

በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል።

በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል።

በተጨማሪም በረቂቁ በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች (Crazy Day, Gentle Day, Olds Day, Baby Day, Fruit Day, Tomato
Day, Valentine Day, April the full, Color Day, Pyjama Day…etc) መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል።

የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል።

የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል።

የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል።

መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል።

በተጨማሪ መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በመመሪያው ላይ ምክረ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች በ https://forms.gle/R72ai6EiMnzZtGsC6 እንዲያቀርቡ ጠይቋል።

#TikvahethMagazine
😐76🤝3