Dark truth
የመጀመሪያዋ ወይም የመጨረሻዋ አልያም የእሷ ብቻ ላትሆን ትችላለህ። ካንተ በፊት አፍቅራለች እና እንደገና በፍቅር ወድቃለች። ግን አሁን ከወደደችህ ሌላ ምን ዋጋ አለው? እርሷ ፍጹም አይደለችም አንተም አይደለህም። ሁለታችሁም ፍጹም አትሆኑም። ግን አንድ ጊዜ እንኳ ልታስቅህ ከቻለች ሁለቴ እንዳታስብ። ሰው መሆንህን እና መሳሳትህን የምታምን ከሆነ ያዛት እና የምትችለውን ሁሉ ስጣት። ቅኔ አትቀኝልህም በእያንዳንዱ…
ወንዶች ሁል ጊዜ የሴቶች የመጀመሪያ ፍቅረኛ መሆን ይፈልጋሉ። ይህ የእነሱ ተንኮለኛ ከንቱነት ነው። እኛ ሴቶች ስለ ነገሮች የበለጠ ስውር ደመ ነፍስ አለን። የምንወደው የወንዱ የመጨረሻ ፍቅረኛ መሆን ነው።
Oscar Wilde
(A Woman of No Importance)
@darktrut
👍12
Dark truth
አንድም ወላጅ ደካማ ልጅ አይፈልግም፤ ማንኛዋም እህት ደካማ ወንድም አትፈልግም፤ የትኛውም ልጅ ደካማ አባት አይፈልግም፤ ሚስቶች በጠቅላላ ደካማ ባል አይፈለጉም። ሁሉም ጠንካራ እና የበላይ እንድትሆን ይፈልጋሉ። በዚያን ጊዜ ብቻ ደስተኛ፣ ኩራት፣ የደህንነት ስሜት እና መብት ይሰማቸው ይጀምራል። ምክንያቱም ወንዶች የተፈጠሩት ለዚህ ነው። ለጥቃት የተጋለጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ofcourse ወንዶችም ሰዎች ናቸው።…
Repost🎯ከመድከም በላይ ስቃይ አያገኘንም፤ ከስንፍና የሚበልጥ ቀፋፊ ነገር የለም!። እየታገልን እንኖራለን ፥ እየተዋጋን እንሞታለን!። ይህ የጠንካሮች ህግ ነው፤ መጨረስ ወይንም አለመጀመር. .
@darktrut
❤10👍2🤔1
Dark truth
Repost🎯 ከመድከም በላይ ስቃይ አያገኘንም፤ ከስንፍና የሚበልጥ ቀፋፊ ነገር የለም!። እየታገልን እንኖራለን ፥ እየተዋጋን እንሞታለን!። ይህ የጠንካሮች ህግ ነው፤ መጨረስ ወይንም አለመጀመር. . @darktrut
ስወለድ ከማልቀሴ በፊት ብልቴን ነው ያየውት። እነሆ ቆለጥ ያንጠለጠልኩ ወንድ ልጅ ነኝ፤ ሸቀጤ አይሸጥ አይለወጥ ይልቅ ለሸቀጤ የሚያስፈልገውን ለማሟላት ሌላ ወጪ ያስፈልገኛል። ከዚህ በኋላ የሚጠብቀኝን መከራ ሳስበው አምርሬ አለቀስኩ🦵🏼😥
@darktrut
@darktrut
😁10👍4
Dark truth
“'ሴቶች ብርህን ብቻ ነው የሚፈልጉት!' የሚባለው አባባል ገንዘብ የሌላቸው ወንዶች የፈጠሩት የመጽናኛ ተረት ተረት ነው።” ―ፊና
እውነት ነው ገንዘብ ፍቅርን አይገዛም ፤ ነገር ግን ፍቅረኛን ይገዛል። then ከፍቅር የምንፈልገው ሁሉ ከፍቅረኛችን እንሸምታለን እንደማለት ያለህ ነው..
👍6❤2
የሕይወትን ስራ እና አላማ የሚገልጡ ዘጠኙ የጃፓናውያን የሕይወት መርሆዎች ፥
@darktrut
GAMAN
-በአስቸጋሪ ጊዜያት ውስጥ ሆነው እንኳ የራስዎን ክብር ይጠብቁ በፈተና ሁኔታ ውስጥ እንኳ ሆነው እነዚህን ፈተናዎች ውስጥ ሆነው እንኳ የስሜታዊ ብስለት እና ራስን የመግዛትን ወይም የመቆጣጠርን ክህሎት ያሳዩ ታጋሽ፣ ጠንካሮች እና አስተዋይ መሆንዎን ያስታውሱ።
KAIZEN
-በሁሉም የሕይወትዎ ዘርፎች ሁልጊዜ ለውጥን ይፈልጉ። ወሳኝብየሆነ ለውጥ እንኳ ከብዶኛል ብለው ቢያስቡም... ትናንሽ ለውጦች እንኳን ሊጨመሩ እና በጊዜ ሂደት ትልቅ ተጽእኖ ሊፈጥሩ ይችላሉ@darktrut
❤3👍2
“ውስጥ ያሉት መውጣት ካልቻሉ ፥ ውጭ ያሉት መግባት ካልፈለጉ፤ መቃብር ስፍራ ለምን በግርግዳ እንደሚከለል ግራ ይጋባኛል።” 🧐
፦Mark twain
@darktrut
፦Mark twain
@darktrut
👍12❤4🔥1😁1
❤12🔥3
የፈላስፋው ፍሬድሪክ ኒቼን ደብዳቤዎች ያነበበ ሰው በብቸኝነት ስሜት ብዙ እንደተሰቃየ ይገነዘባል። በ1887 ዓ.ም ለጓደኛው ኮቭሪክ እንዲህ ሲል ደብዳቤ ጻፈለት፦
“ልጅ እያለሁ ብቻዬን ነበርኩ ዛሬ ላይ አርባ አራት አመት ሞልቶኝም ብቻዬን ነኝ። የሰው ልጅ ሁሌም እንደናፈቀኝና እንደፈለኩት ነው። እኔ ግን ይሄ ፍለጋ ሁሌም እራሴን ያስገኝልኛል ምንም እንኳን እራሴን ባልናፍቅም። ከእንግዲህ ወዲህ ማንም ወደ እኔ የሚመጣ የለም፤ እኔማ ወደ ሁሉም ሄጄ ነበር ቢሆንም አንድም አላገኘሁም!።”@darktrut
💔18😢5❤1👍1
ድንገት በቻት ነበር የተዋወቅነው ብቻዬን በነበርኩበት ሰአት ...እሷ ሁሉን ሆነችልኝ በአካል አብሬ ከማሳልፈው ጊዜ በላይ እሷ ጋር የምናወራው ይበልጥ ነበር በቃ አብራኝ ነበር የምትውለው ከምላችሁ በላይ የምትገርም ሴት ናት የሚያውቀኝ የልብ ጓደኛዬ እንኳ የሷን ያህል የሚጨነቅልኝ አይመስለኝም ነበር ከፋኝ ስላት ትዘፍንልኛለች.. ድምጿ ያምራል... አይተውት የማያውቁትን አካል መልኩን ያላዩትን ማፍቀር እንደሚቻል ያወኩት ያኔ ነበር(አጠር አድርጌ ልንገራችሁ ብዬ ነው).....ከዛ እንዳፈቀርኳት ነገርኳት አይሆንም አለችኝ ጓደኝነቱ ይበልጥብናል አለችኝ እኔም ይሄን ግጥም ፃፍኩላት .....አንብቡልኝማ(ደሞ ርዕስም አልሰጠሁትም በቃ ዝምብላችሁ አንብቡት)
በሳቅሽ ጥልቅ ሀዘኔን ረሳሁት፣
ድብርት ስሙን ዘነጋሁት፣
ቀልድ ሳይኖርሽ እየፈጠርሽ የሌለሽን አጫወትሽኝ፣
መከፋቴን ነጠቅሽና ድርብ ደስታን አቀበልሽኝ።
እንዲያ ሲሆን ሞኙ ልቤን መውደድ ጎኑን ጎሻሸመው፣
ንፁህነት የለበሰ ፍቅር ሚባል ያልነካካው ፣
ብትፈልጊም ጓደኝነት አፈቀረሽ ምን ላድርገው?
እና.. ጥፋቴ ምንድነው ላልሽኝ ምን እንደሆን ቆይ ልንገርሽ፣
ለማታውቂው አንድ ተራ ሰው ይሄን ሁሉ ያደረግሽው አንቺ ማነሽ?
ማን ብትሆኚ ምን ብትሆኚ....
ድንገት በ chat ላወቅሽኝ ሰው...
እንዳይከፋኝ ተጠንቅቀሽ፣
እንዳላዝን አስተውለሽ ፣
ምታወሪኝ በድምፅሽ ሳይ ሳቅ ጨምረሽ፣
ከእለታት በሆነ ቀን ቢደብረኝ ፣
ሀዘን ቢጤ ቢጫጫነኝ፣
አትከፋ እኔን ይክፋኝ፣
ብለሽ ዘፍነሽ ያፅናናሽኝ፣
እምባን በሳቅ የለወጥሽኝ፣
እኮ ለምን የረሳሁትን ሳቅ ዘመዴን ያስታወስሽኝ?
ይሁን ተይው መልሱ ይቅር፣
ግን ይሄነትሽን ይቻላል ወይ አለማፍቀር?
ቢቻል ኑሮ ምን በወጣኝ፣
እንዲህ አጥቼሽ ብቸኝነት የሚቀጣኝ።
ቢቻልማ ሁሉን ትቼ፣
ማፍቀር ሚባል ረስቼ፣
እንኳን ጓድሽ ባሪያሽ መሆን መች ጠልቼ።
#እውነተኛ_ታሪክ
@darktrut
በሳቅሽ ጥልቅ ሀዘኔን ረሳሁት፣
ድብርት ስሙን ዘነጋሁት፣
ቀልድ ሳይኖርሽ እየፈጠርሽ የሌለሽን አጫወትሽኝ፣
መከፋቴን ነጠቅሽና ድርብ ደስታን አቀበልሽኝ።
እንዲያ ሲሆን ሞኙ ልቤን መውደድ ጎኑን ጎሻሸመው፣
ንፁህነት የለበሰ ፍቅር ሚባል ያልነካካው ፣
ብትፈልጊም ጓደኝነት አፈቀረሽ ምን ላድርገው?
እና.. ጥፋቴ ምንድነው ላልሽኝ ምን እንደሆን ቆይ ልንገርሽ፣
ለማታውቂው አንድ ተራ ሰው ይሄን ሁሉ ያደረግሽው አንቺ ማነሽ?
ማን ብትሆኚ ምን ብትሆኚ....
ድንገት በ chat ላወቅሽኝ ሰው...
እንዳይከፋኝ ተጠንቅቀሽ፣
እንዳላዝን አስተውለሽ ፣
ምታወሪኝ በድምፅሽ ሳይ ሳቅ ጨምረሽ፣
ከእለታት በሆነ ቀን ቢደብረኝ ፣
ሀዘን ቢጤ ቢጫጫነኝ፣
አትከፋ እኔን ይክፋኝ፣
ብለሽ ዘፍነሽ ያፅናናሽኝ፣
እምባን በሳቅ የለወጥሽኝ፣
እኮ ለምን የረሳሁትን ሳቅ ዘመዴን ያስታወስሽኝ?
ይሁን ተይው መልሱ ይቅር፣
ግን ይሄነትሽን ይቻላል ወይ አለማፍቀር?
ቢቻል ኑሮ ምን በወጣኝ፣
እንዲህ አጥቼሽ ብቸኝነት የሚቀጣኝ።
ቢቻልማ ሁሉን ትቼ፣
ማፍቀር ሚባል ረስቼ፣
እንኳን ጓድሽ ባሪያሽ መሆን መች ጠልቼ።
#እውነተኛ_ታሪክ
@darktrut
😢8💔7❤1👍1🤝1
ሁሌም አውቀክም ቢሆን ለቀልድም እንኳን ቢሆን በራስክ ላይ መጥፎ ንግግሮችን አትናገር ሳታስበው እራስክ ያልከው ነገር ተብትቦክ ታገኘዋለክ።
ሁሌም መልካምን ቃል ዝራ።
@darktrut
❤18👍1
ክረምት ሆኖ የሚያስተክዝ ብርድና ዝናብ ሲመጣ ፣ ሰው በየቤቱ ገብቶ እሳት ሲሞቅ ፣ ቡና ሲጠጣ ፣ ቆሎ ሲቆረጥም ፣ አሹቅ ሲቅም ብቻዬን እከተማ እወጣለሁ። ጭር ይላል። ሁሉ በየቤቱ ነበር። በስክርክር የቦይ አበላ ስጫወት እቆይና . . . ተዳክሜ ወንዝ ዳር እየተንዘፈዘፍኩ እቆማለሁ። ብርዱ ውስጤ ነበር። እውነቴን ነው ውስጤ ነበር። እንደኳስ ተድበልብሎ የተቀመጠ ብርድ ነው። ታድያ ወደሞላው ወንዝ ጉሮሮዬ እስኪበጠስ እጮሃለሁ . . .ምንአልባት የውስጤ ቅዝቃዜ እንደ ትውከት ተወርውሮ ቢወጣ ብዬ። ተጣብቆ ይቀመጣል። ብርዱ አንጀቴ ላይ እንደኖረ ፣ ጎጆውንም በሲምንቶ እንደቀለሰ ኮሶ ተጣብቆ ይቀመጣል. . ከዚያ የቀን ሕልሜን እጀምራለሁ . . .፦ ግራጫ- ቃጭሎች 📖
@darktrut
👍16❤9