Dan Admasu
5.45K subscribers
30 photos
2 videos
26 links
ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር ያርጉ በተጨማሪም ዩትዩብ ላይ ያገኙናል
👇👇⭕️Subscribe⭕️Subscribe👇👇
ዳን አድማሱ የዩቲዩብ ቻናል ሊንኩን በመጫን https://bit.ly/3ckOkCF ቤተሰብ ይሁኑ።

ሰላም ለ ኢትዮጵያ
ሰላም ለሰው ልጆች በሙሉ
አንድኢትዮጵያ
#ዳን_አድማሱ
Download Telegram
"ላይለ ኩሉ" የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ማታ !!!

#ዳን_አድማሱ
#Dan_admasu
አንድ ኢትዮጵያ !!!
"ላይለ ኩሉ" የሙዚቃ ቪዲዮ ዛሬ ማታ !!!

#ዳን_አድማሱ
#Dan_admasu
"ላይለ ኩሉ"
--------------
አደይ አዳዬ እማ ደብተራ ኦሪቷ
ሀዘን ገብቷት ዛሬ ላልቶ መቀነቷ

አስኬማውን ደፍቶ መንጋውን ካልመራ
መምሬ አያስብልም ጥምጣምና ጭራ

ፍሙ ቢንቀለቀል ምን ቢያነደው ንዳድ
ምነው አልሰማ አለ ለገመ ያ ምጣድ

ጋሞ ጪማ አዋቲ ተው ባይ ቢገኝባት
ፍቅር በረታው ልብ ሳር አብርዷል እሳት

https://youtu.be/zLvbN2ZpdbI
#ዳን_አድማሱ
#Dan_admasu
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !

በመጀመሪያ ሁሉን ላደረገ እግዚአብሔር አምላክ ምስጋና ይግባው በመቀጠልም በኔ በታናሹ ባሪያዋ አፍ ስሟን እንድጠራት እና እንዳመሰግናት ለረዳችኝ ለፈቀደችልኝ  አቁራሪተ መዓት ፣ የ ገብርኤል ብስራት ፣ ንፅህተ ንጹሃን ፣ ሃገረ እግዚአብሔር ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ፣ ማህደረ ሰላም ፣ መዓርገ ሕይወት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብር ይግባት አሜን !

ከዚህም በማስከተል በምገልጽላችሁ ቦታ በ ኦረቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በ ምስራቅ ጎጃም  ዞን በ አነደድ ወረዳ ልዩ ስሙ የገሚት በዓታ ማርያም እየተሰራ ባለው ቤተ ክርሰቲያን ገቢው ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚሆን እና እየተሰራ ያለውን ስራ ለማስተዋወቅ በሚል የበረከቱን ስራ በመዝሙር የተሳተፍኩኝ ሲሆን የህም መዝሙር ዳን አድመሱ በሚለው በራሳችን ዩ ቲዩብ ( Dan Admasu YouTube https://bit.ly/3ckOkCF  ) ዛሬማታ የሚለቀቅ መሆኑን እየገለጽኩ መላው ኦርቶዶክሳውያን በቅንነት የተሰራ በመሆኑ በቅንነት ትሰሙት ዘንድ እኔ ታናሽ ልጃችሁ እና አገልጋያችሁ በትህትና እየጠየኩ ኦርቶዶክሳውያን ቦታው ድረስ በመሄድ በገደሚቱ እንዲሁም በእመቤታችን ቅደስት ድንግል ማርያም ኪዳነ ምህረት እና በዓለም ቤዛው መድሃኒያለም ጸበል የሚገኘውን ፈውስና በረከት እንዲካፈሉ እንዲሁም እየተሰራ ላለው ቤተ ክርስቲያንም እዚህ ላይ ባለው የ ባንክ ቁጥር እና አድራሻ የበኩልዎን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ስል በትህትና ጠየኩ እግዚአብሔር ሃገራችንን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን።

1000365725358 ገዳሚት ባታ ለማርያም ብለው በማስገባት የ በረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ

#ዳን_አድማሱ #Dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
ተለቀቀ
"ማርያም ቅኔ"

ዳን አድማሱ አዲስ መዝሙር https://youtu.be/baCUPEufvyo

#ዳን_አድማሱ
#Dan_admasu
"ፍሙ ቢንቀለቀል ምን ቢያነደው ንዳድ
ምነው አልሰማ አለ ለገመ ያ ምጣድ "

#ዳን_አድማሱ
#dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
"ጠላትን የምታሳፍር እውነተኛው ጻድቅ ዮሴፍ ሆይ የሃይማኖት ጠላቶች በላያችን በድንፋታ በተነሱ ጊዜ ያቺ ረደኤትህ ረዳት ትሁነን"

የማትፈርሰው ዓለት ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን የመሰረታት ውይም የቤተ ክርስቲያን መሰረቷና ዓለቷ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መዳኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እርሱም በደሙ መሰረታት  ስለዚህም መሰረቷም ጉለላቷም ጣራው ግድግዳዋም የክርስቶስ ደም ሆኖ ሳለ ቤተ ክርስቲያን የመክፈል እንቅሳቃሴዎች የእግዚአብሔርን መንግስት እንደመክፈል የእግዚአብሔርን መንግስት እንደመቃወም እንዲሁም የእግዚአብሔርን መንበር እንደመነቅነቅ ይቆጠራል!!!!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት ስንል ለፖለቲካ ፍጆታ እና በሰው ዘናድ ድጋፍ ያስግኝልናል በሚል ለአፍ ቃል ማሳመሪያ ብለን አጉል ብንራቀቅ አባቶቻችንን ብንሸነግል ምዕመኑን ብናሞኝ ጠባቂዋ መንፈስ ቅዱስ ነው እና ሰው ያላወቀውን ልብ የሸመቀውን የውስጡን  የክፉ ምክረ ሃሳብ እግዚአብሔር አምላክ ገልጦ የክፋቱን ስራ በአደባባይ ያሰጣዋል::

አሁንም በዚህ ጊዜ ያየነው ይህንኑ ነው ይቺን ታላቅ ሀገር እንዲመራ እድል የገጥመው ሁሉ ማንኛውም አካል ቤተ ክርስቲያንን አማካሪው እና አስተማሪው አድረጎ በመውሰድ ሌሎች መሪዎች የወደቁበትን ሚስጥር በማወቅ  የራሱን ጠንካራ መንግስታዊ አስተዳደር በመመስረት የተፈራ እና የተከበረ ታሪክ ይሰራ ነበር ብዬ አምናለው።

ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያኗ የሚመስለን ድንጋዩ ቆርቆሮ ምስማሩ ብሎኬቱ መስሎን እሱን ካፈረስን እሷ የለችም ብለን የምናምን የዘመኑ ጅሎች ካለን ይህ አሁን ከላይ የጠቀስኩትን ቁሳቁስ መስሏቸው ከግራኝ ጀምሮ እስከ ጉዲት ተሞክሮ ያልተሳካ የዘመናት ልምምድ ነው ።
አሁን እኛ ባለንበት ዘመንም ይህን ለማደረግ ብዙ እርቀት ለመሄድ ቢሞከርም አሁንም መሰረቷ የክርስቶስ ደም ነውና አልተቻለም አይቻልምም።

አለት ሲከፈል አየው ኪሚል ቅዠት ጀመሮ ተገንጣይን እና ህጋዊን እኩል እስከሚያይ አስተዳደር ድረስ ፈጦ የሚታል ጥላቻ ላይ ያደረሳትን  ነገር ብናውቀው ለህሊናችንም ዕረፍት ነበር። መንግስት ቢቀያየር ከትኛውም የእምነት አካል ቢነግስ እንደ መንግስት ተቀብላና አክባራ እውቅና የምትሰጥን የእምነት ተቋም  በዘር እና በቋንቋ መክሰስና መውቀስ ፍትሀዊ አይደለሽም ብሎ መኮነን ክርስቶስን ፍትሀዊ አይደለህም እንደማለት ነው። ማለትም ነው። 

ምክንያቱም ይቺ እምነት ተወካይነቷ ወይም እንደራሴነቷ ለእግዚአብሔር ነውና። ከዘር ከጥላቻ ከቋንቋና ከሀሰት ጋር እንድትቆም ሰማያዊ ተልኮዋ አይፈቅድምና እንደው ሊባሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ነች ይሏታል በሚባለው በሀገራችን ቢህል ብንዘጋው ይቀላል።

ይቺ በዘመናት ውጣውረድ በከባድ ፈተና ወስጥ ሳትበገር አልፋ እዚህ የደረሰች ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ዛሬም እንዳለፈው እንደወም በተሻል ችግሮቿን እንደምታልፍ እሙን ነው። ሌላው የሀገር መሰሶ ሲነካ ሁሉም መነካቱ የማይቀር ነው እና ሁላችንም ቤተ ዕምነቶች የምንጠብቃት የሁላችን ጉዳይ ልናደርጋት ይገባል በማለት መልዕክቴን አበቃለው።

ቤተ ክርስቲያኔ ዕውቀት የገበየውብሽ ጥበብን የታደልኩብሽ ምግባርንና ሰውመሆንን ብቻ የተማርኩብሽ ጉልላቴ ሁሌም አለው ከጎንሽ ዘብ ሆኜ  ለክብርሽ ልጠብቅሽ የሰማይ ሀምሳል መንበር የእግዚአብሔር ሀገር በምድር ቀዳማዊት ሉላዊት አጸድ ቤተ መቅደስሽ ይከበር

       #እንዲት ዕምነት
       #እንዲት ጥምቀት
       #እንዲት ሀይማኖት
       #እንድ ሲኖዶስ
       #እንድ መንበር
       #እንድ ፓትሪያሪክ
ሎቱስባት


#ዳን_አድማሱ
#Dan_Admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
ነገ ማታ #ቅዳሜ በጎልድ አዲስ እንገናኝ // #Gold_Addis #Saturday_night

#ዳን_አድማሱ
#dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
ዛሬ ማታ በጎልድ አዲስ እንገናኝ // #Gold_Addis #Saturday_night #ቅዳሜ

#ዳን_አድማሱ
#dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
ዛሬ ማታ በጎልድ አዲስ እንገናኝ // #Gold_Addis

#ዳን_አድማሱ
#dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
በመላው ዓለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! መልካም በዓል ።


#ዳን_አድማሱ
#dan_admasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
ጋዜጠኛ እና የፕሮግራም አቅራቢ አሰፋው መሸሻ ነብስ ይማር !!!
"ከጠለሸው ሰማይ ከወረሰን ዳዋ
አለች አንዲት ጀንበር በቅርብ የምትወጣ ዳግማዊት ዓድዋ"

ክብር ለሚኒሊክ!
ክብር ለጣይቱ!
ክብር ኢትዮጵያን ብለው ለተሰዉ ጀግኖች አርበኞቻችን በሙሉ!

#ዳን አድማሱ
"ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም አምይዕዜሰ፤ ኮነ፤ ፍስሐ፤ ወሠላም።"
"ክብር ለስላሴ ይሁን"

በመጀመሪያ ተማሪና ታናሽ ሳለሁ በእናንተ በውድ የኢትዮጵያ ሀገሬ ህዝብ ፊት ሞገስ እንዲኖረኝ ያደረገኝ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን አንዲሁም የነገሮቼ ሁሉ መቋጠሪያ መሰሪያዋ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን ላመስግን ።

በመቀጠልም እናንተ ውድ የሀገሬ ልጆች ኢትዮጵያውያን ሁሌም ለምታሳዩኝ ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ማበርታት ከአንገቴቀለስ ከወገቤ ጎንብስ ብዬ የአክብሮት ምስጋናዬን አቀረብኩኝ ። በመቀጠልም ይህ #ላይለ_ኩሉ የተሰኘው ስራ ለዚህ ክብር እንዲበቃ ብቻውን አልቆመምና ብቻዬንም አልተወጣሁትምና ከሀሳቡ ጥንስስ ጀምሮ እስከፍጻሜው ድረስ አብሮኝ ለደከመው ታላቁ የሙዚቃ ሊቅ ለኔ ደሞ ታላቅ ወንድሜ ጭምር ዳግማዊ አሊ እንዲሁ ለእህትና ወንድሞቼ ሳባ (ሚሚ) አሸናፊ (አሹዬ) እንዲሁም እንደራሱ ስራ በዝናብና ፀሀይ ሳይበገር ቀን ከለሊት ደክሞ ጥልቅ ወንድማዊ ፍቅሩን ላሳየኝ የባለብዙ ጥበብ ባለቤት ወንድሜ ደራሲና ዳይሬክተር አንተነህ ሀይሌ እንዲሁም እውነት ፊልም ፕሮዳክሽን መላው ክሩ አባላትን ላመሰግን እወዳለሁ እንዲሁም የክብር ሽልማት አዘጋጆች መላው ክሩ እግዚአብሔር አብዝቶ ክብረትን ይስጥልኝ እላለሁ ።

#ዳን_አድማሱ
#Danadmasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ !

ኢድ ሙባረክ !

#ዳን_አድማሱ
#Danadmasu
YouTube:- https://bit.ly/3ckOkCF
Telegram:- https://t.me/Dan_Admasu