።CORE NOTE📚
2.24K subscribers
231 photos
99 files
108 links
ᴘʀᴇᴘᴀʀᴇ ʏᴏᴜʀsᴇʟғ ғᴏʀ ᴍᴏʀᴇ.
Contact : @kenny_adane
Follow us:

https://linktr.ee/dr.core1
Download Telegram
💥ሰበር‼️

የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ከስራ ተባረሩ !

መርበርግ የተባለ አደገኛ ቫይረስ የ6 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈ ማግስት የሆስፒታሉ ሜዲካል የዳይሬክሩ መባረር አነጋጋሪ ሆኗል።

ሜዲካል ዳይሬክተሩ የተባረሩትም አለማቀፉ ሚድያ በቫይረሱ የሞቱ ዜጎች መኖራቸውን በማረጋገጣቸው እንደሆነም የውስጥ ምንጮች ነግረውናል።

ከሰሞኑ ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ የ 6 ሰዎች ህልፈትን ተከትሎ የማህበራዊ ሚድያዎች ትኩረት በጂንካ ሆስፒታል ላይ አነጣጥሯል።

ቫይራል ሄሞሬጅክ ፌቨር የተሰኘው አደገኛ የቫይረሶች ቡድን ተከተሰተ መባሉን ተከትሎ በተደረገ የሟቾች የደም ናሙና ምርመራ ውጤት ማርበርግ የተሰኘ አደገኛ ወረርሽኝ መከሰቱ ተሰምቷል።

የሟቾቹ የናሙና ምርመራ ውጤትን መነሻ በማድረግ በፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና በኢትዮጽያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በኩል የወረርሽኙን ክስተት ያረጋገጡ መግለጫዎችም በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻቸው ያሰራጩ ሲሆን አለም ዓቀፉ የጤና ድርጅትም አፋጣኝ የገንዘብ፣ የሙያተኛና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ጣቢያ ዶቼቬሌ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢኒያም አስራት የወረርሽኙ ክስተት ሞት ማስከተሉን ያረጋገጡበትን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ 4 ታካሚዎችና የህክምና እርዳታ ያደረጉላቸው 2 ሀኪሞች፤ 1 ዶክተርና 1 ነርስ ህይወት ማለፍን ያረጋገጡት ሜዲካል ዳይሬክተሩ የሟቾችን ቁጥር መግለጻቸው ተከትሎም ሜዲካል ዳይሬክተሩ ከስራቸው መባረራቸው ተሰምቷል።

የቀረበው ውንጀላም ለአለማቀፉ የሚድያ ተቋም DW የተከሰተውን ሃቅ ያረጋገጠ መረጃ ሰጥተሃል በሚል ውንጀላ መሆኑንም ከሆስፒታሉ የመረጃ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

የፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በሰጡት በመግለጫ በሆስፒታሉ በቫይረሱ የተጠረጠሩ ሰዎችን እንጂ የሞቱ ሰዎች መኖራቸውን ያልገለጹ ቢሆንም ዳይሬክተሩ ይህንኑ ይፉ ማድረጋቸውን ተከተሎ ከስራ መታገዳቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሷቸዋል።

የተከሰተው ቫይረስ እጅግ አደገኛና ገዳይ መሆኑ እየተገለጸ የሟቾችን ቁጥር መደበቅ ለምን እንደተፈለገ የታወቀ ነገር ባይኖርም ሃቁን ባለመደበቃቸው የተወነጀሉት ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቢኒያም አስራት አደገኛ ዛቻና የእስር ማስፈራሪያ እየደረሱባቸው መሆኑንም ለማረጋገጥ ችለናል።

ከስራ የተባረሩበት ደብዳቤ የደረሳቸው ሜዲካል ዳይሬክተሩን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ብናደርግም በዚህ ጉዳይ ምንም አስተያዬት ለማንም መስጠት እንደማይፈልጉ በመግለጽ ስልካቸውን ዘግተዋል።

ሆኖም ግን የእገዳ ደብዳቤው በክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ጫና አድራጊነት የተጻፈባቸው መሆኑን ከሆስፒታሉ የውስጥ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

በስራው ታታሪና ትጉህ የሆነው የጂንካው ተወላጅ ዶ/ር ቢኒያም ሆስፒታሉን ለማሻሻል እየተጋ ቢሆንም በተደጋጋሚ ጫና ውስጥ መቆየቱን ጠቁመው እውነተኛ መረጃ መስጠት ኃላፊነቱን በመወጣቱ ሊመሰገን ሲገባው ከስራ መታገዱ ተገቢ አይደለም ብለዋል።

በአለማቀፉ የጤና ተቋም ተረጋግጦ በመንግስት መግለጫ በተሰጠበት ጉዳይ መረጃ ምንም አይነት ክልከላ በሌለበት፤ ዶ/ሩ መባረር እውነታን ለመደበቅ የሚፈልግ አካል ሴራ ሊሆን ይችላል የሚሉት ምንጮቹ ሃቀኛ መረጃ እንዲሸፈን የተፈለገበት ምክንያት ግን ምን ሊሆን እንደሚችል አናቅም ብለዋል።

አስደንጋጭ እልቂት ያስከትላል የሚለው የቫይረሱ ስጋት ባጠላበት ጂንካ ሆስፒታል ከሟቾች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው በርካታ ዜጎች በተጠርጣሪነት ተለይተው በሚገኙበት በዚህ ወቅት

በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ነዋሪ ከመንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችና የጥንቃቄ መልዕክት እየተጠባበቀ ቢሆንም የክልሉ ጤና ቢሮና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት መገኛ በሆነው ጅንካ ክስተቱን በተመለከተ የክልሉ ልሳን የሆነው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅትም፤ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንንም ሆነ ሌሎች ሚድያዎች ዝምታን መምረጣቸው አነጋጋሪ ሆኗል።”

💥 ዶ/ር ቢኒያም አስራት በአስቸኳይ ወደ ስራው እንዲመለስ እንጠይቃለን! እውነት መናገር መረጃ ለሚዲያ መስጠት ወንጀል አይደለም። የሚመለከታቸው አለም አቀፍ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ እንጠይቃለን። EHPM ለአለም አቀፍ ተቋማት እና ኤምባሲዎች በቀጣይ ቀናት ደብዳቤ የሚያስገባ ይሆናል።

በጂንካ ያላቹ ጤና ባለሞያዎች ስለ ዶ/ር ቢኒያም እና በMVD ምክንያት ስለሞቱት 6 ሰዎች የተብራራ መረጃ ላኩልን!

@core_note
😢85
ERMP 2025 (2018 academic year) will be open for a period of Tahisas 6-20, 2018 EC (December 15-29, 2025 GC)

@core_note
1👍1
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
________

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy, Optometry እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በታህሳስ 2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

ስለሆነም አዲስም ሆነ ነባር፣ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hpe.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እና የኦንላይን ምዝገባው ከታህሳስ 02/2018 እስከ ታህሳስ 12/2018 ዓ.ም ብቻ የሚቆይና ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦

ተመዛኞች ምዝገባውን ለማካሄድ የኢትዮጵያ ዲጅታል መታወቂያ- ፋይዳ (Ethiopian Digital ID Card) ግዴታ መሆኑን አውቃችሁ የፋይዳ መለያ ልዩ ቁጥር (FIN) በትክክል እንድታስገቡ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረው መጉላላት የጤና ሚኒስቴር ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑ እናሳውቃለን።

ለተጨማሪ መረጃ የጤና ሚኒስቴር ቴልግራም ቻናል ይመልከቱ t.me/M0H_EThiopia

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
4
የትፍ_ሰዓት_ክፍያ_23_ሚኒስቴር_መስሪያ_ቤቶች.pdf
2.3 MB
"ይህ መመሪያ ሲቪል ሰርቪስ ድረገፅ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተፈፃሚ ይሆናል!"

የትርፍ ሰዓት አከፋፈል መመሪያ ፣ ታህሳስ 7፣ 2018 ዓ.ም

Maximum duty hours = 212 hrs

Calculation based on = 1.25x ,1.5x , 2x , 2.5x

@core_note
👎21👍1
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__________

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው በታህሳስ 23 እና 24/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን ለተጨማሪ መረጃዎች የጤና ሚኒስቴር ቴልግራም ቻናልን( t.me/M0H_EThiopia) ይመልከቱ።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
1
Another intern doctor lost from the University of Gondar. Such a young life gone, this is deeply painful. It forces us to ask what is happening to our medical trainees and who will take responsibility to study the causes and find solutions.

Rest in peace, Dr. Mary Abebe.
😢30
Urogynecology and reconstructive pelvic surgery sub-speciality graduates of Jimma University, 2026

Picture 1: pictured from left to right: Dr. Bezza Kedida, Dr. Eyob Asefa, Dr. Ukasha Ayanage, Dr. Rebi Ali

Picture 2 & 4: pictured with their instructors

Picture 3: pictured with their instructors from Lyon University, Professor George M, & Dr. Stephen
3
#Update
#NGAT‼️

የNGAT ምዝገባ ተጀምሯል‼️


ምዝገባው የሚጠናቀቀው፦
ጥር 14/2018 ዓ.ም

የመመዝገቢያ ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ (ሊንኩ ክፍት እስከሚደረግ በትዕግስት ይሞክሩ።)

🔔 ሁሉም አመልካቾች የፋይዳ መታወቂያ ሊኖራችሁ ይገባል የተባለ ሲሆን፤ የምዝገባ እና የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር በኩል ብቻ መከፈል ይኖርባችኋል።

ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ወደፊት የሚያሳውቅ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል።

Follow us at @core_note
6🙏3
Dear ERMP 2025 applicants

After a lengthy journey of screening of registered applicants, we are on the final step of finalizing the confirmation process, and by early next week, we’ll post a list of eligible candidates for the exam disaggregated by exam hub, together with an instruction about the exam. So far, more than 3000 applicants have been registered, and 2534 of them are confirmed.

Hereby, we would like to inform you that the ERMP 2025 (2018 academic year) entrance exam is scheduled to be conducted on Yekatit 9 and 10, 2018 EC (February 16 and 17, 2026 GC) nationally in the selected exam hubs.


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
6
ማስታወቂያ
ለጤና ባለሙያዎች በሙሉ

ጤና ሚኒስቴር የጤናና ጤና ነክ ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ደህንነትን እና ጥራት ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ የቁጥጥር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህ መሰረት የጤናና ጤና ነክ ተቋማት እና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ የቁጥጥር ዘርፉን አቅምና ውጤታማነት ለማሻሻል ከሚሰሩ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ውስጥ አንደኛው የጤና ቁጥጥር ስርዓትን ዲጂታላይዝድ ማድረግ ነው።

ስለዚህ ይህንን የቁጥጥር ስራ ለመስራት ማንኛዉም በጤናው ዘርፍ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ከዚህ በታች በተዘረዘሩ መስፈርቶች መሰረት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 20 ቀናት ከዚህ በታች የተቀመጠዉን ማስፈንጠሪያ በመጫን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን።

https://forms.gle/fV4vKAJLtQ24M6x28

መስፈርት
▫️ በጤና ተቋማትና ባለሙያዎች የቁጥጥርና ሌሎች ስራዎችን በተመለከተ ዘርፉን ለማገዝ ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች
▫️ እውቅና ካለው የከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቀ እና የታደሰ የሙያ ፈቃድ ያለው/ያላት
▫️ ከሚሰሩበት ተቋም በተመደቡበት ሙያ የስራ ልምድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል
▫️ ከሚሰሩበት ተቋም የእውቅና/የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል
▫️ የመስመር ላይ (Online) ስልጠና ለመውሰድ ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች

ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት

1. ስፔሻሊስት ሃኪም
2. ጠቅላላ ሃኪም
3. ጤና መኮንን
4. ላቦራቶሪ
5. ፋርማሲ
6. አንስቴቲስት
7. ነርስ
8. ባዮሜዲካል ኢንጂነር
9. ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂስት
10. ሚድዋይፈሪ
11. የኣካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያ
12. ሌሎች የጤና የሙያ ዘርፎች

ማሳሰቢያ፡-
▫️ አመልካች የትምህርት ማስረጃ/ዲግሪ፣ የስራ ልምድ፤የሙያ ፈቃድ እና ከቁጥጥር ስራው ጋር ተያያዥነት ያለው የስልጠና ሰርተፊኬት ካለ በPDF ማያያዝ ይኖርበታል
▫️ በጤና ተቋማትና ባለሙያዎች የቁጥጥር፤የክሊኒካል ኦዲት ስራ እና ጥራት/quality Improvement ላይ ተሳትፎ የነበረው ይበረታታል
▫️ ለበለጠ መረጃዎች semreselam.tsega@moh.gov.et, hiwot.abebe@moh.gov.et

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
3👍1
ሀኪሞች ለምን ይሰደዳሉ?!
መሐመድ ሹኩር (ዶ/ር)

" ኢትዮጵያ በፈረመችው የአቡጃ ዲክላሬሽን ሀገራት ከ15 በመቶ በታች ያልሆነ የጤና በጀት ነው የሚመድቡት። የእኛ ዓመታዊ በጀታችን ገና 3 በመቶ ነው። ብዙ ሀገራት ይህን አሳክተዋል፤ ጎረቤቶቻችንም ይህን ያህል ባይደርሱም ከእኛ የተሻለ እየመደቡ ነው ያሉት።

የእኛ የጤና በጀት ካለው የሕክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒቶች ዋጋ መጨመር፣ ካዳዲስ በሽታዎች መከሰት፣ ከሕክምና ውጭ ጋር ተያይዞ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንዲቻል የታሰበ ነገር ቢኖር ? "

መሐመድ ሹኩር (ዶ/ር) ለ ጠ/ሚኒስትሩ ዛሬ ካቀረቡት

©Tikvah
@core_note
10
Some points to increase couples satisfaction during ultrasound scanning

My own perspective

As is well known, pregnancy is a new, unique and exciting experience for the woman in particular, and the couple as a family. So during ANC visits, among the elements that are essential, sonographic scanning is one of them.

Hence rather than just scanning with muted and gloomy look, there are some points I have gained from my own small experience can be used to increase our client’s satisfaction

1. Do not prohibit the husband from entering the ultrasound room

In countries like Ethiopia, where ANC ultrasound rooms are super busy— with more than 30-40 mothers scanned in most of the hospitals—this may seem impractical. But think of it: what additional time would be wasted by just allowing her spouse to enter the room with her? Infinitesimal, right?

I am not calling for inviting the husband in (that would be compelling though) but at least do not prohibit him or kick him out when he is eager to get involved in the procedure.

2. Discuss your findings with her/them

The usual trend, especially in public hospitals, is to inform her/them when there are abnormal observations. Even if the sonographic findings are normal, tell her/them that the unborn baby is doing well in the womb.

Tell her about the presentation (አቀማመጡ ጥሩ ነው), the biophysical profile (እንቅስቃሴው አሪፍ ነው፣ የእንሽርት ውሃው በቂ አለ) and the likes, even if she doesn’t ask. Reassure her. She will appreciate it and it will create a good rapport with you.

3. Tell them the sex of the baby

Though this is somewhat controversial, it is routine to see couples informed about the sex of their unborn child in private settings. But the same personnel who does this in private practice are usually hesitant to do the same in public hospitals. Why?

I am not saying you have to tell to all pregnant women without their consent as there are some women who prefer to know only after their child is born. But why do you yell at a mother who is keenly interested to know the sex of her baby? That is her right, and telling her doesn’t make you any less professional.

However, taking much time figuring out the sex while compromising the anatomical scan and biophysical profile is not acceptable. But for those asking for it, just tell them what you see, nothing wrong with this.

4. Let her watch the ultrasound screen

Rotate the screen to her side and arrange it so she faces the screen and can watch her baby “play” (gross body movements and extremity movements). That will create a lasting memory and have a better impact on positive pregnancy experience.

5. Ask her whether she has any concerns or ailments

This is also usually overlooked. Rather than just having her leave after scanning, take a minute and ask her if she has any concerns, questions or ailments. You will get paramount information that could change your management plan.

Although there are other things that could be done for better patient satisfaction, I have focused on the above five points which I consider are usually undervalued.

Dr. Zelalem Girma: Obstetrician and Gynecologist
16👍1🔥1
Medical Ethics.pdf
1 MB
💼 Book: the CORE - Medical Ethics


📚 @core_note
https://t.me/corenotebook
3
ቀን 12/6/2018

ለጤና ሚኒስቴር ፣
አዲስ አበባ

​ጉዳዩ፡ በ2018 ዓ.ም (2026 እ.አ.አ) የሕክምና ስፔሻሊቲ መግቢያ ፈተና (ERMP) ውጤት ላይ የቀረበ አቤቱታ

​እኛ የ2018 ዓ.ም የሕክምና ስፔሻሊቲ መግቢያ ፈተና (ERMP) ተፈታኝ ሐኪሞች፣ በቅርቡ በኮምፒውተር (CBT) አማካኝነት በተሰጠው ፈተና ሂደትና ውጤት ላይ የታዩ ከፍተኛ ግድፈቶችን በመጥቀስ ይህንን የቅሬታ ደብዳቤ አቅርበናል።
​ፈተናው በቴክኒክም ሆነ በይዘት ረገድ የሚከተሉት መሠረታዊ ችግሮች የታዩበት መሆኑን እንገልጻለን፡-
፩. ​የቴክኒክ ብልሽት (የምስሎች አለመታየት)፦ በፈተናው ወቅት የራጅ (X-ray) ምስሎችን አይቶ ለመመለስ የሚጠይቁ ጥያቄዎች የነበሩ ቢሆንም፣ ምስሎቹ በሲስተሙ ላይ ባለመታየታቸው ተፈታኞች ጥያቄዎቹን መመለስ ሳይችሉ ቀርተዋል። ይህም በሲስተሙ ብቃት ላይ ጥርጣሬ ከመፍጠሩም በላይ ውጤታችን ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ አሳርፏል።
፪. ​ከፍተኛ የጥያቄዎች ድግግሞሽ፦ በዘንድሮው ፈተና ላይ ካለፉት ዓመታት የተወሰዱ ጥያቄዎች ከ35% በላይ (መጠነኛ ማስተካከያ ብቻ የተደረገባቸውን ሳይጨምር) ተደግመው ቀርበዋል። አንድ አገር አቀፍ ፈተና እንዲህ ያለ ከፍተኛ የድግግሞሽ መጠን መያዙ የፈተናውን ሚስጥራዊነትና ተዓማኒነት (Exam Integrity) ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ከመሆኑም በላይ፣ አዲሱን ተፈታኝ በትክክል ለመመዘን የሚያስችል የጥራት ደረጃ ላይ እንዳልነበረ ያሳያል።

፫. ​የውጤት መዛባትና የእርማት ስህተት፦ ብዙ ተፈታኞች ከፈተናው በኋላ የሰሩትን ስሌት ሲያሰሉ ከፍተኛ ውጤት እንደሚጠብቁ እርግጠኛ ቢሆኑም፣ ሲስተሙ የሰጣቸው ውጤት ግን እጅግ የወረደ ሆኖ ተገኝቷል። ይህም በኮምፒውተር እርማት (Grading Algorithm) ወቅት የቴክኒክ ስህተቶች ወይም የመልስ አቆጣጠር ችግሮች (Bugs) እንዳሉ በግልጽ ያሳያል።
፬. የይዘት አለመመጣጠን (Blueprint Violation)፦ ፈተናው አስቀድሞ በተቀመጠውና ተፈታኞች እንዲዘጋጁበት በተደረገው የፈተና ማዕቀፍ (Blueprint) መሠረት አልተዘጋጀም። በተወሰኑ የሕክምና ዘርፎች ላይ ብቻ ያተኮረና ሌሎችን ዘርፎች ያገለለ ሆኖ በመገኘቱ፣ የተፈታኞችን አጠቃላይ ዕውቀት በትክክል መመዘን አልቻለም።

​ይህ ፈተና የብዙ ሐኪሞችን የቀጣይ የትምህርት እና የሥራ ዕጣ ፈንታ የሚወስን የላቀ ሙያዊ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሚከተሉትን እርምጃዎች በአስቸኳይ እንዲወስድልን እንጠይቃለን፡-
​የፈተናው ሂደትና የሲስተሙ ትክክለኛነት በቴክኒክ ባለሙያዎች እንዲመረመር/እንዲያስመረምር፤
​የመልስ ቁልፎቹ በከፍተኛ የሕክምና ባለሙያዎች በድጋሚ ታይተው ስህተቶች እንዲታረሙ፤
​የምስል አለመታየትና የጥያቄ ድግግሞሽ ያመጣው ተፅዕኖ ታይቶ ውጤታችን በድጋሚ እንዲሰላ።
​የሕክምና ማኅበረሰቡ በፈተናው ሂደት ላይ ያለውን አመኔታ ለመመለስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ሚኒስቴሩ የሚሰጠው አፋጣኝ ምላሽ ወሳኝ መሆኑን እንገልጻለን።

​ከአክብሮታዊ ሰላምታ ጋር፣

የ2018 ዓ.ም (2026) ERMP ተፈታኝ ሐኪሞች
@core_note
29😘1