የወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ዙሪያ ግንዛቤ ተፈጠረ
18/09/2017 ዓ.ም
* አዲስ አበባ *
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ወንዝና የወንዞች ዳርቻ ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ለሲቪክ ማህበራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
የባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በደንቡ 180/2017 ዙሪያ በተለያዩ መድረኮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ መሰጠቱን እና ግንዛቤ እንደሚቀጥል በመድረኩ መክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል ።
"የወንዝ እና ወንዞች ዳርቻ ብክለት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የህግ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ኮርሳ አቅርበዋል።
በሰነዱ በከተማዋ 76 ወንዞች መኖራቸውና የወንዞች ፅዳት ለህብረተሰቡ የጤና ስጋት በመፍጠራቸው ንጽህናቸው ለመጠበቅ ደንቡን መውጣቱ ገልጸዋል።
የወንዞች ደህንነት ለማስጠበቅ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በዚሁ ዙሪያ ጥናት ማጥናቱን ገልጸው ይህንን ደንብ በሚተላለፉ አካላት ላይ ከ2 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ድረስ የቅጣት መጠን መቀመጡንም አስታውቀዋል።
የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ስራዎች ለመስራት ከሲቪክ ማህበራቱ እገዛ እንደሚያስፈለግ እና ሲቪክ ማህበራቱ በደንብ ቁጥሩ ላይ የተሰጣቸው ስልጠና በሚኖሩበት አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲያስገነዝቡ መልዕክት ተላልፏል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባውን:- የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
18/09/2017 ዓ.ም
* አዲስ አበባ *
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ወንዝና የወንዞች ዳርቻ ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ለሲቪክ ማህበራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
የባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በደንቡ 180/2017 ዙሪያ በተለያዩ መድረኮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ መሰጠቱን እና ግንዛቤ እንደሚቀጥል በመድረኩ መክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል ።
"የወንዝ እና ወንዞች ዳርቻ ብክለት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የህግ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ኮርሳ አቅርበዋል።
በሰነዱ በከተማዋ 76 ወንዞች መኖራቸውና የወንዞች ፅዳት ለህብረተሰቡ የጤና ስጋት በመፍጠራቸው ንጽህናቸው ለመጠበቅ ደንቡን መውጣቱ ገልጸዋል።
የወንዞች ደህንነት ለማስጠበቅ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በዚሁ ዙሪያ ጥናት ማጥናቱን ገልጸው ይህንን ደንብ በሚተላለፉ አካላት ላይ ከ2 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ድረስ የቅጣት መጠን መቀመጡንም አስታውቀዋል።
የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ስራዎች ለመስራት ከሲቪክ ማህበራቱ እገዛ እንደሚያስፈለግ እና ሲቪክ ማህበራቱ በደንብ ቁጥሩ ላይ የተሰጣቸው ስልጠና በሚኖሩበት አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲያስገነዝቡ መልዕክት ተላልፏል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባውን:- የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤1👍1
ባለስልጣኑ ልምዱን እና ተሞክሮውን ለመንገዶች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት አጋራ
18/9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ለመጡ የልዑካን ቡድን አባላት ሙስናና በለሹ አሰራሮችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ በተቋም አደረጃጀት፣ በመመሪያ ዝግጅት ፤በሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር በተመለከተ ያለውን ልምድና ተሞክሮ አጋርቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ በልምድ ማጋራቱ ወቅት የተቋሙ አደረጃጀት እና ተቋሙ በማጠናከር የተቋሙና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ሂደት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልፀዋል።
በልምድ ልውውጡ ባለስልጣኑ እንደየስራ ክፍላቸው ብልሹ አሰራር ከመከላከልና ከመቆጣጠር ረገድ የተተገበሩ ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ገለጸፃ አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋሙ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ለልዑካን ቡድኑ አባላት አስረድተዋል፡፡
የመንገዶች ባለስልጣን የልዑካን ቡድን አባላት ተቋሙ የተደራጀበት እና ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመነጋገር እየሰራ ያለው ውጤታማ ስራዎች አድንቀው የወሰዱት ተሞክሮ እና ልምዱን በተቋማቸው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
18/9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ለመጡ የልዑካን ቡድን አባላት ሙስናና በለሹ አሰራሮችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ በተቋም አደረጃጀት፣ በመመሪያ ዝግጅት ፤በሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር በተመለከተ ያለውን ልምድና ተሞክሮ አጋርቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ በልምድ ማጋራቱ ወቅት የተቋሙ አደረጃጀት እና ተቋሙ በማጠናከር የተቋሙና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ሂደት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልፀዋል።
በልምድ ልውውጡ ባለስልጣኑ እንደየስራ ክፍላቸው ብልሹ አሰራር ከመከላከልና ከመቆጣጠር ረገድ የተተገበሩ ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ገለጸፃ አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋሙ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ለልዑካን ቡድኑ አባላት አስረድተዋል፡፡
የመንገዶች ባለስልጣን የልዑካን ቡድን አባላት ተቋሙ የተደራጀበት እና ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመነጋገር እየሰራ ያለው ውጤታማ ስራዎች አድንቀው የወሰዱት ተሞክሮ እና ልምዱን በተቋማቸው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።