ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የውል ስምምነት አካሄደ ።
25/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለአመራሮችና ለኦፊሰሮች የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው አመራሮች በተገኙበት የውል ስምምነት ፊርማ አካሄደ ።
በስምምነቱ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ አመራሩና ኦፊሰሩ አቅም ለማሳደግ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዩንቨርስቲው ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በበኩላቸው ተቋሙ እና ከተማው የሰጣቸው ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
25/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለአመራሮችና ለኦፊሰሮች የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው አመራሮች በተገኙበት የውል ስምምነት ፊርማ አካሄደ ።
በስምምነቱ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ አመራሩና ኦፊሰሩ አቅም ለማሳደግ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዩንቨርስቲው ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በበኩላቸው ተቋሙ እና ከተማው የሰጣቸው ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍10❤2
ባለስልጣኑ በሶስት ዙር ሲሰጥ የቆየውን የዲጅታል የመስክ ስራ አስተዳደር ስልጠነና ተጠናቀቀ
26/02 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ቡድን መሪዎች እና ሰራተኞች በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ለማስጀመር በሶስት ዙር የመስክ አስተዳደር /Field managmet system/ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል።
የባለስልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ስልጠናው መጠናቀቁን አስመልክቶ በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ገልፀው አሰራሩ ተግባራዊ በማያደርግ ባለሙያ ተጠያቂነት እንደሚኖር አመላክተዋል ።
በቀጣይም የቅሬታ አስተዳደር ሲስተም /complain managnment system / እና የስማርት ቢሮ ስልጠናዎች የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
26/02 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ቡድን መሪዎች እና ሰራተኞች በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ለማስጀመር በሶስት ዙር የመስክ አስተዳደር /Field managmet system/ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል።
የባለስልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ስልጠናው መጠናቀቁን አስመልክቶ በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ገልፀው አሰራሩ ተግባራዊ በማያደርግ ባለሙያ ተጠያቂነት እንደሚኖር አመላክተዋል ።
በቀጣይም የቅሬታ አስተዳደር ሲስተም /complain managnment system / እና የስማርት ቢሮ ስልጠናዎች የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4
አለርት ሆስፒታል በካይ ኬሚካል ወደ ወንዝ በመልቀቁ 1,000,000/አንድ ሚሊዮን/ ብር መቀጣቱ ተገለፀ
26/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር ጋራ በመሆን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በወንዝና በወንዝ ዳርቻ በካይ ቆሻሻ የለቀቀው አለርት ሆስፒታል የመንግስት ተቋም ላይ 1,000,000/አንድ ሚሊዮን/ ብር በመቅጣቱ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።
የተካሄደው በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ቦታ ዘነበ ወርቅ አለርት ሆስፒታል ብክለቱ በከተማው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባለሙያዎች በላብራቶሪ የተረጋገጠ በመሆኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 1,000,000 (አንድ ሚልየን )ብር የተቀጣ መሆኑ ተገልጿል።
በክፍለ ከተማው በወረዳ 4 በወንዝ ዳርቻ ብክለት የፈፀሙ 6 ላቢያጆዎች እያንዳንዳቸው 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 600,000/ስድስት መቶ ሺህ/ ብር በመቀጣት በክፍለ ከተማው በእለቱ በአጠቃላይ 1,600,0000/አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ተገልጿል ።
ባለስልጣኑ በተደጋጋሚ በተለያዩ አማራጮች የግንዛቤ ፈጠራ ስራ እየሰራ ቢሆንም ከህገ ወጥ ተግባራቶች በማይታቀቡ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል በመሆኑ ነዋሪዎችና ተቋማት ከመሰል ተግባራቸው እንዲታቀቡ አሳስቧል።
የከተማው ነዋሪ በሚኖርበት አካባቢ ህገወጥ ተግባራትን ሲከናወኑ ካስተዋሉ በነፃ ስልክ 9995 ጥቆማ እንዲሰሰጥ ተቋሙ ጥሪውን አስተላልፎዋል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
26/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር ጋራ በመሆን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በወንዝና በወንዝ ዳርቻ በካይ ቆሻሻ የለቀቀው አለርት ሆስፒታል የመንግስት ተቋም ላይ 1,000,000/አንድ ሚሊዮን/ ብር በመቅጣቱ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።
የተካሄደው በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ቦታ ዘነበ ወርቅ አለርት ሆስፒታል ብክለቱ በከተማው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባለሙያዎች በላብራቶሪ የተረጋገጠ በመሆኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 1,000,000 (አንድ ሚልየን )ብር የተቀጣ መሆኑ ተገልጿል።
በክፍለ ከተማው በወረዳ 4 በወንዝ ዳርቻ ብክለት የፈፀሙ 6 ላቢያጆዎች እያንዳንዳቸው 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 600,000/ስድስት መቶ ሺህ/ ብር በመቀጣት በክፍለ ከተማው በእለቱ በአጠቃላይ 1,600,0000/አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ተገልጿል ።
ባለስልጣኑ በተደጋጋሚ በተለያዩ አማራጮች የግንዛቤ ፈጠራ ስራ እየሰራ ቢሆንም ከህገ ወጥ ተግባራቶች በማይታቀቡ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል በመሆኑ ነዋሪዎችና ተቋማት ከመሰል ተግባራቸው እንዲታቀቡ አሳስቧል።
የከተማው ነዋሪ በሚኖርበት አካባቢ ህገወጥ ተግባራትን ሲከናወኑ ካስተዋሉ በነፃ ስልክ 9995 ጥቆማ እንዲሰሰጥ ተቋሙ ጥሪውን አስተላልፎዋል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍13👏5❤3
ባለስልጣኑ በኮሪደር ልማት የሳይክል መንገድ ላይ የጭነት መኪና ያሽከረከረ ግለሰብ የገንዘብ ቅጣት ቀጣ
01/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አራዳ ፓርክ ውስጥ በኮሪደር የለማ የሳይክል መንገድ ላይ በጭነት መኪና በመንቀሳቀስ የደንቤ ጥሰት የፈጸመ አሽከርካሪ በደንብ ቁጥር 167/2016 መሰረት ሹፌሩ 5000 ብር ሲቀጣ ባለቤቱ 50,000 ብር በድምሩ 55,000 ብር በመቅጣት ያቆሸሹትን አካባቢ እንዲያፀዱ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
01/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አራዳ ፓርክ ውስጥ በኮሪደር የለማ የሳይክል መንገድ ላይ በጭነት መኪና በመንቀሳቀስ የደንቤ ጥሰት የፈጸመ አሽከርካሪ በደንብ ቁጥር 167/2016 መሰረት ሹፌሩ 5000 ብር ሲቀጣ ባለቤቱ 50,000 ብር በድምሩ 55,000 ብር በመቅጣት ያቆሸሹትን አካባቢ እንዲያፀዱ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👏1