Safo-art
221 subscribers
349 photos
10 links
Download Telegram
የሳምንቱ መልዕክት👇

ዛሬም ስለ ሰው ያለን ፍቅር ላይ እናስተንትን። ሁሌም ስለ ፍቅር እናወራለን እንናገራለን እንሰማለን ግን አስተውለነው እናውቅ ይሆን
ምንም ደስ የሚል ስብከት ብንሰማ ምንም ታላቅ ገድል ብናደርግ ከእየሱስ ፍቅር የሚበልጥ የለም። ግን የክርስቶስ ፍቅር በጥልቀት አስተውለነው እናውቅ ይሆን

👆 ጥያቄዎቹን ለእያንዳንዳችን ይሁኑና።

ኧረ እንደው ለሰው መጥሮን በጥሩ እንመልስ ይሆን??
⭐️" ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።"
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:9)⭐️

እስቲ ራሳችንን እንመልከት🤔
አንድ ሰው ቢሰድበን ለመፈንከት እንነሳለን : ለመግደል : በአጠቃላይ ወደ መጥፎ ጎዳና እንመራለን። ነገር ግን እስቲ ክርስቶስን እንይ... ሲገርፋት : እሾክ በራሱ ላይ ሲጠመጥሙ : ቆምጣጤ ሲያጠጡት : ከባዱን መስቀል ሲያሸክሙት : ምራቅ ሲተፋበት : ልብሶቹን ሲገፋት : ያለ አግባብ ሲፈርዱበት : ገፍተው ሲጥሉት : ጎኑን በጦር ሲወጉት : ሲቸነክሩት : አንድም ቃል አልተነፈሰም። የምህረቱ ብዛት ጥልቅ ነው ኧረ ምንኛ ድንቅ አምላክ ነው ያለን?? "ይቅር በላቸው" ምንኛ ደስ የሚል ቃል ነው

⭐️" ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። "
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:7)⭐️ 😥 እየሱሴ እወድሀለሁ😘😍

ወደ ርዕሳችን እንመለስ እኛስ ይቅር በላቸው እንል ይሆን።🤔 መልሱን ለእያንዳንዳችን።

⭐️" በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፥ የሌላው መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ፥ እንደወንድሞች ተዋደዱ፥ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ፤"
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:8)⭐️

👌 የሌላውን መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ።

የሌላን ሰው መከራስ እንዴት ነው የምናየው

አሁንም ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ እርስቶስን እንመልከት።

እሱ የኛን በደል ሲደመስስ እኮ ማንም የሚያስገድደው አልነበረም። ፍቅር ይዞት ነው እንጂ። (አቤት የ እየሱስ ፍቅር ጥልቀቱ)

⭐️" እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:5)⭐️

ዛሬም እያንዳንዳችን በክርስቶስ ፍቅር የአንድ አባት ልጆች ነን። የሌላው ችግር : ጭንቀት : ሀሳብ ለኛም መሆን አለበት።

ክርስቶስ የህይወታችን መሪ አድርገን ስንነሳ ፍቅርን እንማራለን። (እውነተኞቹ የክርስቶስ ወዳጆች ብዙ የሚያውቁቱ ሳይሆን ብዙ የሚወዱት እንዲሁም ትዕዛዙን የሚፈፅሙት ናቸው።


⭐️" እኔ አምላክህ እግዚአብሔር። አትፍራ፥ እረዳሃለሁ ብዬ ቀኝህን እይዛለሁና። "
(ትንቢተ ኢሳይያስ 41:13)⭐️

እ/ር ሰውን ሁሉ መውደድ የምንችልበቱ ፀጋው ሀይሉን ብርታቱን ያድለን🙏


http://t.me/catholicsbot
Cove : 😅
Join us: @Ygna_telegiram 👈
🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀🏃‍♂🏃‍♀

የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን

የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት

የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።

ላይክ፣ሼር እናርግ

ደስታን እናስተምር፣


ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን:
ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን:
?sher🌹sher🌹

💥 @sew_hun_kesewum_sew_hun💥
💥 @sew_hun_kesewum_sew_hun💥