መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
238 subscribers
75 photos
1 video
75 links
Download Telegram
የትኛውም ሰባኪ (መምህርና መጽሐፍ) ስለ እግዚአብሔር ሲናገር ዲያቢሎስንም አይተወውም:: በቀጥታ ሰይጣን አሊያ አጋንንት ባይል እንኳ ስለ ክፉዎቹ ግብር ወዲያም አለ ወዲህ ያነሣል:: ስለ ውሸት፣ ክሕደት፣ ምቀኝነት፣ ዘርኝነት፣ አድመኝነት፣ ንፉግነት፣ ሌብነት፣ ግዴየለሽነት፣.. ሳይገሥጽ የሚሰብክ መንፈሳዊ ትምህርት አለ ይሁን?

እንግዲያስ ዲያቢሎስ ማለት በነዚህ ክፉ ባሕሪያት የሚገለጽ ፍጡር ማለት እኮ ነው:: ችግር የሆነው ይህንን ክፉ ከነስሙና የውጊያ ስልቶቹ ስለተማማርነው ነው? እኔ ሐሰትን ለብቻ ሰይጣንን ለብቻ አድርገው የሚያዩና ይህን ዕይታቸውን የሚያስፋፉ ሰዎች ይደንቁኛል:: ብቻም ሳይሆን ወንጌል "[ዲያቢሎስ] ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል" ስለማለቷ ያነበቡ፥ ካነበቡም እንደሚገባ ያጤኑ አልመሰለኝም:: (ዮሐ. 8፥44)
በዛሬው እለት ግንቦት 12 / 2016 ዓ.ም May 20 2024 በአሜሪካ ላስ ቬጋስ 3950 south Jones Blvd las vegas NV,89103 የተከናወነው የመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ እና የመልአከ ኃይል መምህር ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ መንፈሳዊ አገልግሎት በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል ።

በህዝቡም ጥያቄ መሰረት የማታ’ ጉባኤ እና ነገ May 21 የሚቀጥል መሆኑን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን! ። እናመሰግናለን በነጻ ማስታወቂያ የምትሰሩልን ሰዎች!

ሰይጣን አካል አይደለም፡፡ የራሱ የሆነ የለውም፡፡ አካል ያለው የመንፈሳዊ ሲሆን ሥጋዊ ፍጥረት(ሰው) ጥላ እንጂ፡፡ - ይኸውም ሀሳባቸው ውስጥ ነው፡፡

ለዚህ ነው ፍትህ በፍርድ ሲገለጽ አጠፋፉ እንደ ጢስ ከፍታ በመትነን ነው ሚባለው፡፡

ታሪካዊ መንፈስ ታውቃላችሁ ወይ?
ለዘላለም የሚኖረው ነው 33ዓመት የኖረው።

አብዛኛው ሕብረተሰብ የእግዚአብሔርን የማዳን ነገር ዋጋ ሳይሰጡና በበጎነት ሳይመለከቱ፤ የራሳቸውን ምክንያት በመደርደር፤ ሰው ላይ የሚታየውን ችግር ፋይዳ ቢስ አድርገው፤ ባዶነታቸውን ሳይመለከቱ እንደ ነፍሳቸው ምኞት ይናገራሉ፡፡ “እንዲሁም ክፋትን ይጎነጉናሉ” ብዙው ሰው ረጅሙን ዕድሜ ያሳለፈው በምስጋና፣ በፀሎትና በአምልኮት ሳይሆን፤ በጥላቻ፣ በመለያየት፣ በመሰሪነትና አንዱን አንዱ ጥሎ በማለፍ ስለሆነ፤ በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ሆኖ ኃጢአያትን በመለማመድ፤ ደፋር፣ ኩሩ፣ ቀማኛና ነጣቂ በመሆን፤ ክፋትና ጥፋትን ለማቆየት እየሠራ ይገኛል፡፡
እኛም ታዲያ የምናስበው፣ የምናቅደውና አመለካከታችን ከክፋት ጋር የተያያዘ በመሆኑ፤ የብዙውን ትውልድ ዕድል አጥፍተን፤ ብዙ ከሃዲዎችን ማፍራታችን አንዱ የግፍ ሥራችን ምልክት ነው፡፡ በጎና ቅን ሆነን በመንፈስ ቅዱስ ተዋጅተን ወደ ሰው የምንሄድበት ሕሊና ስላጣን፤ ነገር እየጎነጎንን መሰሪ እቅድ ኑሯችን ውሰጥ ተክለን፤ ከጀርባችን ብዙ ክፋቶችን አዝለን እንኖራለን፡፡

ከእነሱ ሁሉ የተሻለው እንደ አሜኬላ ነው” ያለው የነብዩ ቃል፤ አሜኬላ ተደብቆ የሚወጋ ከታች ስትረግጠው ከላይ የሚቧጥጥ፣ ጫማ አልፎ የሚያቆስል፣ የሚያደማ፣ የማያስሮጥ፣ ቁስል የሚሆን፣ እግርን የሚቆጠቁጥ፣ የሚያም፣ የሚያስጨንቅ፣ አረማመድን የሚገታ፣ የወደፊት ተስፋን የሚያመክን እና ቁልቁል የሚያሽከረክር ነው፡፡ ዛሬም የተሻለ የተባለው ሰው ሁሉ ልክ እንደ እሾህ የሚዋጋ ሆኖ በሥልጣን፣ በማዕረግ፣ በከፍታ ለሌላው ሰው እንደ አሜኬላ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ ቅን የሆነውም፤ እንደ ኩርንችት ነው፡፡ ኩርንችት ደግሞ እንደ ደበኛ አድፋጭ፣ ተንኮለኛ፣ ምቀኛና ነገረኛ ምሳሌ በመሆን፤ በተፈጥሮ ሂደትም በምትረግጥበት ስፍራ ላይ እግርህንና ኮቴህን ተደብቆ የሚወጋ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ኩርንችትና አሜኬላ በሁሉም አቅጣጫ በኑሮችን ውስጥ የተለመደ አድርገን፤ በክፋትና በግፍ አሠራር የሌሎችን ሕይወት በግልጽና በስውር ስንጎዳ ይታያል፡፡

እኛም የኃያሉ አምላካችን የእግዚአብሔር ጥበቃና ምሕረት አብሮን እስካለ ድረስ፤ እንደተያዝን አንቀርም፡፡ ከታሰርንበት እንፈታለን፤ ከወደቅንበትም እንነሣለን!
ድ ን ቅ ፡ ፍ ጥ ረ ቱ ን ፡ በ ል ጅ ነ ት ፡ አ ደ ሰ ው ፡ ፡ የእግዚአብሔር ሥራ እንደሆነ መሰራቱ የግድ ነው፡፡
በቃ የግድ ነው!

በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ሜሪላንድ እና ላስ ቬጋስ የነበረን የ አምስት ቀን የቀን እና የማታ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው እለት ግንቦት 13 2016ዓ.ም ( May 21 ) በልዑል እግዚአብሔር ፍቃድ በሰላም ተጠናቋል! አገልግሎታችን ብዙ ህዝበ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ኃይል ለዘመናት ከተተበተቡበት ከመተተኛው ፤ ከደብተራው ከጠንቋዩ ክፉ የዲያቢሎስ እስራት ብዙ ምዕመናን የተፈቱበት ዲያቢሎስ በዘመናችን ምን ያህል የጥፋት መረብ ዘርግቶ እንደሚራመድ ከቤተእግዚአብሔር ቤት ጀምሮ የራሱን የጥፋት መረብ በሰዎች እየዘረጋ እንዴት የክፋት የዘረኝነት ፤ የአድመኝነት ፤ የግፍ ፤ የጥላቻ ፤ የፍቅረነዋይ ስራውን እንደሚሰራ በጥልቀት የተረዳንበት ቅዱሱን ወንጌል በሰፊው የተማርንበት ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ ነው! ይህን አገልግሎት ( kesis Hailemelekot Girma )https://youtube.com/@kesishailemelekotgirmatube7285?si=xv1p4AA05ECjcHaY በሚለው YouTube channel በተከታታይ በቅርቡ እንደምንለቅላችሁ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን!

እንደግሌ እምነት ሰዎች በክፉ መናፍስት በኩል ያለባቸውን ጦርነት በሚገባ በመገንዘብ በአንፃሩም ደግሞ እግዚአብሔር ለኛ የሰጠውን የፍቅር ስጦታና የጸጋ ኃይል ከመግለጥ አኳያ በሁለት እግራቸው ቆመው ለሃይማኖታቸው ያላቸውን ቦታና ክፍል አሳድገው እንዲመላለሱ ማድረግ በተቀዳሚነት የቤተክርስቲያን ተልዕኮና ራእይ ነው፡፡
ከስሟ እንደምንረዳው ቤተክርስቲያን <<የክርስቲያን ቤት>> ነች፡፡ ክርስቲያን የሚለው ከወጣ ቤት የሚለው ብቻ ይቀራል፡፡ የቤተክርስቲያን መቆምና መኖር ለእግዚአብሔር አይደለም፡፡ ለሰዎች ነው፡፡ ሚሊዮን ቤተክርስቲያናት ቆመው የእግዚአብሔርን ስምና ኃይል የማይጠሩ ሰዎች አንድም ከሌሉ እንግዲያው የሰማዩ አምላክ ማረፊያው የት ነው?

አንድ ወቅት ላይ የእግዚአብሔር አገልጋይ ዮናስ ከሰማይ አምላክ ፊት ሸሽቶ በመርከብ በኩል ለማምለጥ ወደ ታቺኛው የመርከቢቱ ክፍል ወርዶ ተኛ፡፡ ማዕበልም መጥቶ መርከቢቱ በወጀብ ስትናጥ አገልጋዩ ተኝቶ ነበረ፡፡

ዛሬም የሆነው ይህ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከመረጣቸውና የአገር ቁጭት ካደረባቸው አገልጋዮች በተለየ ብዙ አገልጋዮች የሕዝበ ክርስቲያኑ እሮሮና ሰቆቃ አይሰማቸውም፡፡ ሕመማቸው አያማቸውም፡፡ ትርምሱን የሚያስቁሙበትን ሰማያዊ ጉልበት መያዝ እንዳይችሉ እየሄዱ ግን በቁማቸው ወርደው ቀንም ማታም ተኝተዋል፡፡ በማረ ድምፅና ገጽታ አውደምሕረት ላይ ይቆማሉ፡፡ በየመድረኩ ይሰብካሉ፡፡ በእልልታና ጭብጨባ በተለይ ታጅበው ቃሉን ይናገራሉ፡፡ ግን ጧፍ አብርቶ ጉባዔው ሲያልቅ ያበራውን ጧፍ አጥፍቶ የተበተነው ሕዝብ፤ ቤቱ ሲገባ እንዳጠፋው ጧፍ የጠቆረና የከሰለ ኑሮ እንደሚመራ አልተረዱለትም፡፡ ቢረዱም እዚህ ግባ የሚባል ሁለንተናዊ መፍትሔ እንደአገልጋይነት ማምጣት አቅቷቸዋል፡፡ የእነርሱ ስራ አጋንንት ዘራቸው ሲነካ ለምን ይነካል በማለት እራሳቸው ተሰደው ማሳደድ እና ብዙ ምዕመናን ላያቸው በነጭ ነጠላ በርቶ ቢታይም፤ ልብና ሕሊናቸው ውስጥ ባህሪያቸውን ተለማምዶ ከሚያንከራታቸው የጨላማ ኃይል ጋር የሚያሳልፉት የመከራ ጊዜ ለአገልጋዮችም ሆነ ለበረቱ ምዕመናን አይታያቸውም፡፡ ዘምረውና 'ቃለ ሕይወት ያሰማልን' ብለው የገቡት ምዕመኖች፤ የኑሮን ጣዕመ ዜማን አጥተው፤ 'ቃለ ሕይወት ያሰማልን' ያሉትን የሕይወትን ቃል በአኗኗራቸው መተርጎም አቅቷቸው እንደሚባትቱ ለመረዳት የሚችሉበትን ልብ አልያዙም፡፡ ስለዚህ የሚተረክ እንጂ የሚኖር ክርስቲያንነት ከባህሪያችን፣ ከጠባያችን፣ ከቤታችን፣ ከኑሮአችን አልገለጥ አለ፡፡ ነጠላ ሲውልቅ አብሮ በሚወልቅ ሃይማኖት ታጅረን የኛም የብዙዎቻችን ጊዜና በረከት ውልቅልቁ ወጣ፡፡ በየቤቱ ቢታይ ከችግርና ትንቅንቅ ኑሮ ጋር ግብግብ ያልገጠመ ክርሰቲያን ማግኘት አዳጋች ነው፡፡ ይኼ እንግዲህ ነባራዊው የሚመረው እውነታችን ነው፡፡ ከእግዚአብሔር አንፃር ሲታይ ሁላችንም ሊባል በተቃረበ ደረጃ የወደቅንበትን ኑሮ እንካደው ካላልን በቀር ዘመንና ትውልዳችን የሚያሳየው ይኼንኑ የሕይወት ምስክርነት ነው፡፡

እኛ ግን በተገፋን ቁጥር በረከትና ጸጋችን በሚታይ ተግባር እየጨመረ ስለሄደ በርቱ! ክርስቶስን አይሁዳውያን አስረው ሲጎትቱት የሚፈልጉትን እያደረጉ መስሎ ነበር የታያቸው፡፡ እርሱ ግን የመጎተቱ መጨረሻ እስከ መሰቀል ድረስ ቢያደርሰው ግዜ ለሁሉ ድኅነት ሆኖ ሰው አደረገን፡፡ ስለዚህ መውጊያውን ብታቃወሙ በራሳችሁ ይብሳል እንጂ የእግዚአብሔር ሥራ እንደሆነ መሰራቱ የግድ ነው፡፡

ሁላችንም ሰብሰብ ብለን ወደ ልባችን፤ እስኪ እንዴት ነው ሕይወቴ? ምንድነው እያሳለፍኩ ያለሁት? ምን አይነት ነገር እየገጠመኝ ነው ብሎ መጠየቅና እነዚህን መልስ ለማግኘት ከንጹሕ ልብና ታማኝነት ጋር ወደ እግዚአብሔር እውነት መጠጋት መጨረሻው እንደ ቀኙ ወንበዴ በዳግም ምጽዕት መታሰብ ነው፡፡

እኛም የኃያሉ አምላካችን የእግዚአብሔር ጥበቃና ምሕረት አብሮን እስካለ ድረስ፤ እንደተያዝን አንቀርም፡፡ ከታሰርንበት እንፈታለን፤ ከወደቅንበትም እንነሣለን!

╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከመልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
14/09/2016 ዓ.ም ከአሜሪካ 🇺🇸 Las Vegas
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
መልካም ልደት አባት
ብዙ ልል ጀምር እና ቃላቶቹ አንሰውብኝ በቃላቶቹ መልሼ እናደዳለሁ .... ምክንያቱም ያንተ እውነት ለዚህ ዘመን ፤ ትውልድ ከቃላቶች በላይ ነው። እኔ ስለምሰስተው ሰው መናገር አልወድም ምክንያቱም የምወደው ሰው እጅግ ውድ ስለሚሆንብኝ ... የውድነትህን መጠን ማን ይረዳልኛል ???? እውነቱን ለማወቅ ጎጆህን ተግባርህን ማየት በቂ ነው። እንደኖህ እግዚአብሔር ወደምድር ሲያይ ደስ የሚሰኝብህ ታላቅ አባት ነህ!!!!! 🙏🙏🙏
አባቴ አርዓያዬ ፤ መሪዬ ፤ ጠባቂዬም ነህ ....
ደግሞ እኮ የኔ ብቻ አይደለህም የሚሊዮኖች ነህ!
እንኳን ተወለድክልን የሚሊዮኖች አባት🙏
💚💚 💛💛
መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ ዛሬ ግንቦት 29 የተወለዱበት ቀን ነው! 65ኛ ዓመታቸውንም ይዘዋል!
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ

የመልአኩ ምልጃው ቃልኪዳን በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን ሀገራችንን ሰላሙን ይሰጠን ዘድ አሳስብልን&#33;

ከቤተ-ሳይዳ የመጻሕፍትና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ መደብር

አድራሻ ፦ 22 ማዞሪያ ጌታሁን በሻህ ሕንፃ ፊት ለፊት ከአክሱም ሆቴል ወረድ ብሎ ሀኮማል ባስራው አዲሱ ትጋት የገበያ ማእከል (አዲስ ቀይ ህንጻ) የመጀመሪያው ፍሎር ከንብ ባንክ ጎን ያገኙናል። ለበለጠ መረጃ ለዚሁ አገልግሎት ብቻ የሚውል በእዚህ ስልክ መደወል ይቻላል 0919959995 P.O.Box 25084 Code 1000 ይህ ስልክ ሌላ አገልግሎት አያስተናግድም

እናንተም በቤተ ሳይዳ እየተገኛችሁ የቱባረከ መንፈሳዊ መሳሪያዎችን እየወሰዳችሁ ፍቅር፣ሰላም፣ደስታ፣ የነሳንን ጠላት እየተፋለማችሁ ወድ ክርስቶስ መንግስት የሚወስደውን መንገድ እንድትይዙ አደራ እላለሁ።

የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ወደ ሕይወት የለወጠው፥ ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ፈተና የታደጋት፥ የእግዚአብሔር የሆኑትን ሁሉ የሚረዳና የሚጠብቅ ገናናው ሊቀ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በአገራችን፥ በሕዝባችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተጻፈውን የደብተራውን ፤ የጠንቋዩን ፤የሟርተኛውን ክፉ ሴራ ሁሉ ይበጣጥስልን።

+++ወስብሐት ለእግዚአብሔር+++