መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
243 subscribers
101 photos
1 video
87 links
Download Telegram
ቤተ ክርስቲያን ማለት ምእመናን ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተዋጁ የሕያዋን ስብስብ ናት፡፡ እነዚህ ምእመናን በግጭትና ፤ በትዳር አለመግባባት በዓለም ፍርድ ቤት በዲያቢሎስ ተይዘው መቆም አይገባቸውም፡፡
https://vm.tiktok.com/ZMM4m2Jdf/
ሞቶልኝ ነው እንጂ ገድለውት አይደለም!
በዛሬው እለት ግንቦት 4 / 2016 ዓ.ም May 12 2024 በአሜሪካ ሜሪላንድ 16000 Croom Airport Road Upper Marlboro MD 20772 የተከናወነው የመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ እና የመልአከ ኃይል መምህር ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ መንፈሳዊ አገልግሎት በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል ።

በህዝቡም ጥያቄ መሰረት የማታ’ ጉባኤ እና ነገ May 13 እና May 14 እንደቀጠለ ነው ። እናመሰግናለን በነጻ ማስታወቂያ የምትሰሩልን ሰዎች!

ባልታጠቡ ጋኖች ላይ ወይኑ አይሞላም፡፡ ከክፋት ባልጸዳ ልብ ላይ ሰማያዊ ጥበብ አይኖርም፡፡ ከምቀኝት ባልወጣ አስተሳሰብ ላይ ብልጽግና አይመጣም፡፡ ከተንኮል ባልተለየ እቅድ ላይ ስኬት አይኖርም፡፡ ንስሐ ባልገባ ክርስትና ላይ የአምላክ ንጹሕ ሥራዎች አይጸኑም፥ ኃጢአት እያጎመዘዘ ያናውጣቸዋልና፡፡

የአዲሱ አቁማዳ ባሕሪይ አዲሱን የወይን ጠጅ ይቀበላል፡፡ አዲሱም የወይን ጠጅ አዲሱ አቁማዳ ይስማማዋል፡፡ ሁለቱ እርስ በእርስ ይጠባበቃሉ፡፡ ንስሐ የገባ ሕይወትና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ በእርግጥም እርስ በእርሳቸው ይጠባበቃሉ፡፡ ሕግ በሰው ትከበራለች፥ ሰውየውም በሕጊቱ ይከብራል፡፡ ወንጌል በምዕመን ትገለጻለች፥ ምዕመንም በወንጌል ይገለጻል፡፡

ስለዚህ ጠላት ልክ ነዋ! ለምን ታሰቃየኛለህ ትለው ዘንድ አትችልም፡፡ ፈቃዱን፣ ስሜቱን፣ ጠባዩንና ሥርዓቱን እስከጠበክለት ድረስ፤ እርሱ ደግሞ አንተን በክፋት ይጠብቅብህ ዘንድ መብት አለው፡፡ በጎነትን ሳታስቀድም፣ ርኅራኄን ሳትወደው፣ ምቀኝነትን ሳትተወው፣ ጉቦን ሳትጠየፈው .. በጠቅላላው ኃጢአትን ሳትናዘዘው፤ "ከክፉ ሁሉ አድነኝ" እንጂ ብለህ መጸለይ መንፈሳዊ ስላቅ ይሆንብሃል፡፡ ከተኩላው በረት ሰተት ብለህ ገብተህ ከተኩላ አስጥለኝ እንደምን ትላለህ?
https://www.youtube.com/live/SJUCB0lxLi0?si=984LP7eSjriU4_px
መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ Live YouTube ገብተዋል

ልዩ ትምህርት ርዕስ 1 እንዳያውቁት አይናቸው ተይዞ ነበር! ርዕስ ክፍል 2 ይህም ቃል ቅዠት መስሎ ታያቸው! በመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ

በአሜሪካ ሜሪላንድ በ 16000 Croom Airport Road Upper Marlboro MD 20772 ማህበረ ምዕመናን ባዘጋጁት መንፈሳዊ ጉባኤ ግንቦት 4 / 2016 ዓ.ም May 12 / 2024 የተከናወነ የወንጌል ትምህርት እና የፈውስ አገልግሎት
አገልግሎታችን በ Las Vegas እንደቀጠለ ነው!

ለ ሶስት ተከታታይ ቀናት በሜሪላንድ የነበረንን መንፈሳዊ አገልግሎት በ እግዚአብሔር ፍቃድ በሰላም ጨርሰናል!

ቅድስናን ስናሞግስ ርኩሰትን በማውገዝ ነው፤ መልካምን መልካም ያልነው ከመጥፎው ለይተን ነው፤ ነግቷል እኮ ያስባለን የለሊቱ ማለፍ ነው፤ መጠንን ትንሽ ብለን የመዘንነው ከትልቁ አንጻር ነው:: .. [ከፀሐይ በታች ያለቺው] ዓለም እንደዚህ ናት::

አዳም ክፉና ደጉን የሚለይና የሚስማማ ባሕሪይ ይዞ ምድራዊ ኑሮውን ከጀመረ ወዲህ ሰውነት በሁለት መስተቃርን ዋልታዎች መካከል የሚባትት ሕልውና ሆኗል:: (ዘፍ. 3፥22) መጽሐፍ ቅዱስ ከመነሻው ታሪክ አንስቶ የሚነግረን ይህንን ነው:: ከእናንተ መካከል ከዚህ እውነት ውጪ የሆነ የመጽሐፍ ታሪክ የሚያነሣልኝ አለ?

ስለ አዳም ስናወራ ስለ እባብ ተንኮል እናነሣለን:: ስለ አቤል ደግነት ስናነብ ድንጋይ ስለ ጨበጠው ቃየንም እናውቃለን:: ስለ ኖኅ መርከብ ለማውራት የኖኅ ጎረቤቶች ያስፈልጋሉ:: ስለ አብርሃም ጥሪ ስንማር ዙሪያውን ስለ ከበበው ባዕድ አምልኮት መገንዘብ ግድ ይላል:: ሙሴን ስንተርክ ፈርዖንን ማውጣት አንችልም:: ዳዊትን ከጎልያድና ከሳዖል ውጪ ማንሳት ታሪኩን አያሟላም:: ወደ ሐዲስ ኪዳንም አለፍ ብንል ያለው ይኸው ነገር ነው:: ሰብአ ሰገል ሲታሰቡ ሄሮድስ አይዘነጋም:: ለተቀበሉት የእግዚአብሔር ልጅነትን ሰጣቸው ያለው የገዛ ወገኖቹ እንዳልተቀበሉት ነግሮን ሲያበቃ ነው:: (ዮሐ.1፥11-12) በአጠቃላይ የጽድቅ ዕሴቶችን የሚያበረታታው መንፈሳዊው ዓለም ከኩኔው ጎራ ያሉትን በአንድም በሌላም መንገድ ሳይጠቅሳቸው አያልፍም:: ታዲያሳ ትሕትናን ለማስተልቅ ትዕቢትን ካላሳነሱ እንደምን ይሆናል?