ASD AJ LAH
753 subscribers
1.72K photos
194 videos
3 files
486 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
« ሙትቻ ላሉህ ሰዎች እራስህን ለማስረዳት አትሞክር። ለሞትክባቸው ሰዎች የምታባክነው ጊዜ አይኑርህ። ውበትህ ግለፅ ሲወጣ የመጣ ሁሉ ውበትህን አይቶ ላይሆን ይችላልና በአመዳምነት ዘመንህ ላይ ውበትህ የታያቸውን ጠበቅ አድርገህ ያዝ።
ቆንጆ መሆንሽን ከሚያደንቁት የበለጠ የሚያስጠላብሽን ሊያስውቡልሽ የሚጣጣሩትን አትዘንጊ። ቁስልሽን በሰው አትከልዪ። የሚመክሩሽ ሁሉም ከጥቃት አይጠብቁሽም። ጥንቃቄ የብልሆች መንገድ ነው። በጣም ነፃነት በሚሰማሽ ሰው በኩል ስስ ነሽና አትራቆቺ።
ዋጋ የምትከፍዪላቸው ከጌታሽ መንገድ እንዳያስቱሽ አስተውዩ! የምወድሽዋ ልብሽን በቀደር አረጋጊ! የምወድህዋ እራስህ ካልወደቅክ አይጥሉህምና በጌታህ ታግዘህ ፅና። መንገዱ ምን እንዳለው አይታወቅምና ሰላም ለልባችሁ!
©
[አብዱልሀኪም ሰፋ]

❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️

ልባችን ሰላም የሚያገኝበት፣  በሩቋ ሀገር ያሉትም ከአላህ የሆነ እርዳታ እና ድል የሚያገኙበት፣ ተረጋግተው የድል ሰላት የሚሰግዱበት፣  ለተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን ለታመመ መዳንን፣ ለሞቱት ሸሂድነትን  የሚወፈቁበት፣ በሰለዋት፣ በካህፍ እና በዱዓ የደመቀ እና የተዋበ ጁምዓ ይሁንልን💚💚💚
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ሰብት 0️⃣3️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣
―አላህ…የሰዎችን ብሶት አዳማጭ፣ ችግራቸዉን ፈች፣ ለመከራቸው ደራሽ፣ ዕዳቸዉን ከፋይ፣ ጭንቀታቸዉን ተጋሪ፣ ህመማቸዉን ታማሚ፣ ሐዘናቸዉ ተካፋይ፣…ያደረገህ እንደሆን በርግጥም የወደደህ ስለመሆኑ ምልክት ነው። በዚህ ሁኔታህ ላይ የኖርክ እንደሆነ ከፍ እንዳልክ ትኖራለህ»
👤 ኢማም ኢብኑል ቀይም

AbuSufiyan
የፍትሕ ሚኒስቴር ረቂቅ መመሪያ- ግልፅ ለማድረግ !

   የህዝቡ ዝምታ ወይ ጥልቅ ከሆነ ቁጣ ወይ ደግሞ ጥልቅ ከሆነ የግንዛቤ እጥረት ሊሆን ይችላል:: ከቁጣ ከሆነ ይበል የሚያስብል ሆኖ ሲፈነዳ የሚታይ ይሆናል:: ከግንዛቤ እጥረት የመሆን እድሉ ሰፊ ነውና የረቂቅ መመሪያው አንደምታው ምንድን ነው የሚለውን እንደሚከተለው እንመልከት::

   አይበለውና ከፀደቀ በየትኛውም የትምህርት ተቋማት ኒቃብ ለብሶ መማር ይከለከላል:: ይህ ከሆነ ለአመታት ሲደረጉ የነበሩ ትግሎች አፈር ከመልበሳቸው ባሻገር የትምህርት ተቋሞቻችን ህጋዊ ስልጣን ኖሯቸው ኒቃቢስቶችን አንቀበልም የማለት ሙሉ ስልጣን ይኖራቸዋል:: "ለምን?" ሲባሉም መመሪያው ስለሚያዝ ነው የሚል ምላሽን ይሰጣሉ:: "ሕገ-መንግስቱስ?" ከተባሉም ውይይት ተደርጎበት ከሕገ-መንግስት ጋር ምንም አይነት መጣረስ እንደሌለበት ታምኖ የፀደቀ ነው የማለት መብቱ አላቸው:: በዚህ ውስጥ ወትሮውንም በትምህርት ስርዓቱ ያልታቀፈው ሙስሊም በዚህ ሳቢያ ይገፋል:: ትምህርትን እየጠላ ከማዕቀፉ በሲስተም ይወጣል::  በሁለተኛ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሶላት በጀመዓ መስገድ ይከለክላል:: ወንድምህ ወይም እህትሽ እየሰገዱ ሄዶ ተከትሎ መስገድ ሊያስቀጣ ማለት ነው:: በዚህም ሂደት ከሚቀጣው ተማሪ ባሻገር በሙስሊሙ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እየጠፋ የትምህርት ስርዓቱን በቋሚነት ችላ የሚልበት ስርዓት ይዘረጋል::

   በሌላ አውድ ገልብጠን ስንመለከተው ደግሞ ሰፊ የሆነ እድል እናገኛለን:: መመሪያው አሉታዊ ይዘት ባላቸው አንቀፆች እንደተሞላ የተገለፀ ቢሆንም በረቂቅ ደረጃ ያለ ስለሆነ ከላይ እስከ ታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተፅዕኖ በመፍጠር ከሕገ-መንግስቱ በማይጣረስ መልኩ እንዲፀድቅ ማድረግ ይቻላል:: በዚያ ሂደት ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት መብታችንና ሴኩላሪዝም በአግባቡ እንዲከበሩ ማድረግ ከቻልን እስከ ዛሬ በተለያየ ምክንያት አንዴ ሒጃብ ለበሳችሁ ሌላ ጊዜ ሶላት ሰገዳችሁ እያሉ ሲበጠብጡ የነበሩ ሁሉ ተጠያቂ ይሆናሉ ማለት ነው::

   ስለሆነም ችላ ሊባል አይገባም:: የዚህ ትውልድ ትልቁ ሀላፊነት ይህንን ፈተና በድል መወጣት ነው:: ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ awareness ከመፍጠር ጀምሮ ባሉት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ ለዘመናት የጭቃ እሾህ ሆኖ ሲነዘንዘን የነበረውን እንቅፋት ማስወገድ ግድ ይለናል::

MohammadamminKassaw
ትኩረት ያልሰጠነው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ
===========================
(ይህ ጉዳይ ከጸደቀ በኋላ ሌላ ዙሩ በከረረ ትግል ውስጥ ሳንገባ በፊት ከወዲሁ እምነታችንን በማይነካ መልኩ መዘጋጀቱን ማረጋገጥ አለብን!)
||
ካስታወሳችሁ ከአንድ ወር በፊት ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችና ከተለያዩ የኃይማኖት ተወካዮች ጋር በተናጠል ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በተለይ ከኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ከኛ ከእስልምና ኃይማኖት መሪዎቻችን ጋር ባደረጓቸው ውይይቶች መንግሥት በቅርቡ ኃይማኖትን የተመለከተ ሕግ እንደሚያወጣ መናገራቸው ይታወሳል። በተለይ ከመጅሊስ መሪዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት መስጂዶች የሚያደርጉት የአዛን ጥሪ፣ እንዲሁም በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሚከናወኑ ቅዳሴና አስተምህሮዎች ሌላውን ሰው ማወክ ስለሌለባቸው አስቡበት በማለት ስለሚወጣው ሕግ ይዘት ፍንጭ ሰጥተው ነበር። 


መንግሥትና ሃይማኖት አንዱ በአንዳቸው ተግባርና እንቅስቃሴ ውስጥ ጣልቃ አይገቡም የሚለውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ መሠረት በማድረግ፣ መንግሥት ከኃይማኖት ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት በግልጽ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ በፍትሕ ሚኒስተር በኩል ተዘጋጅቶ አሁን ላይ በሰላም ሚኒስተር አስተባባሪነት ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት መደረግ ተጀምሯል።

ይህ አዲሱ አዋጅ በርካታ ክልከላዎችን የያዘ ሲሆን፤ የሙስሊሞችን በጀማዓህ ሶላት መስገድ፣ የእህቶችን ጂልባብና ኒቃብ መልበስ፣ ጀለቢያ፥ አማኢምና ኮፍያ መልበስና የመሳሰሉትን ለማገድ በር የሚከፍት ህግ ተካቶበታል።

የነርሱ እሳቤ የሌላውንም እምነት ተከታይ ኃይማኖታዊ አለባበሱንና በቡድን ማምለክን ስለምንከለክል፤ ሙስሊሞችንም «እናንተን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም ነው የከለከልነው!» በሚል ሽፋን በመሞገት መከልከል አስበዋል።

እዚህ ላይ ያልገባቸው ነገር የእያንዳንዱ እምነት ዶክትሪን የተለያዬ መሆኑን አለማወቅ ነው። በተለይም የእስልምና እምነት ህግጋት በየትኛውም ታዕምር ቢሆን በሰው ሠራሽ ህግ የሚሻሩ አለመሆናቸውን መረዳት ተስኗቸዋል። እነርሱ ሲጀመር ከፊሎቹ ራቁታቸውን መሄድ ነው የቀራቸው። እንኳን ተከልክለው በፈቃደኝነትም እየተገበሩት አይደለም። ታዲያ እነርሱ ከተዘናጉ እኛም አብረን መታፈን አለብን? በጭራሽ!

አይደለም ኢትዮጵያ አዲስ የምታዘጋጀው ህግ፤ የዓለም መንግስታት ተባብረው አዋጅ ቢያወጡ፤ እስልምናችንን ከተቃረነ ማንም አይሰማቸውም። የራሳቸውን እንደፈለጉ ያድርጉ። የኛን ግን እንዳያስቡት።

በተጨማሪም 24 ሰዓት በካሴት ሳይቀር ተከፍቶ የሚለቀቅን የቤተ ክርስቲያን ቅዳሴና መዝሙር በቀን 5 ጊዜ 5 ደቂቃ ለማትሞላ አጋጣሚ የሚደረግን የአዛን ጥሪ አወዳድሮ አብሮ ጨፍልቆ ለመከልከል መጋጋጥ በየትም ተሰምቶ አይታወቅም።

መንግስት አዛን ከከለከለን በተለይም በዐረቡና በሙስሊሙ ዓለም በኩል ያለውን ግንኙነት እንደሚያበላሽ ጠንቅቆ ይወቀው። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ የሆነ መከራ እንዲለብስ ነው የሚሆነው።

ቀድሞ ከሙስሊሙ ተወካዮችና ምሁራን በኩል የተሰጣቸውን ሃሳብ ወደ ጎን በተመው፤ ይህን ረቂቅ የሚያዘጋጁ አካላት።ሙስሊሙን የሚጨፈልቅ ህግ ማውጣታቸው አላማቸው ምን እንደሆነ ግራ ያጋባል። ባለማወቅ ነው እንዳይባል ቀድሞ መረጃ ተሰጥቷቸዋል፤ ግን ወደ ጎን ብለውት በራሳቸው አካሄድ መሄድን መርጠዋል። በርግጥ ፍትሕ ሚኒስተር ውስጥ እነማን እንደሆኑ እናውቃለን። ከአሁን በፊትም ኡማውን ከወያኔ ጀምሮ ሲጨቁኑ የነበሩ አካላት አሉበት።

በአጭሩ እየመጣ ያለው ረቂቅ አዋጅ የእምነት ነፃነትን የሚጋፋና ኃይማኖቶች ከእምነታቸው አስተምህሮ ይልቅ በሃገሪቱ መንግስት ቁጥጥር እንዲዳኙ የሚያደርግ አደገኛ አዝማሚያ ያለው ነውና ከወዲሁ እንዲስተካከል ማድረግ አለብን።

እኛ በደፈናው ባልተጻፈ ህግ ሲጨቁኑን የነበረውን ጉዳይ ጽፈው በግልፅ አስተካክለው ይመጣሉ ስንል፤ ጭራሽ በግልፅ ከልክለውና ሌላም ዱብእዳ አክለው መጡ።

ማንም አይሰማቸውም!

ህዝብ መረጃ ይኑረው። በደንብ መረጃዎችን አንሸራሽሩ። ረቂቅ አዋጁ ነገ ከኃይማኖት ተቋማት ተወካዮች ጋር ውይይት ያደርጋል ተብሏል። እዛም ላይ የኛ ተወካዮች በደንብ ጉዳዩን ያንሱት። አላህ የደነገገው ሸሪዓህ በተራ ሰዎች ህግ በፍፁም አይሻርም፤ አይሻሻልም።
ሸሪዓን የሚቃረን ህግ ካለ ራሱ ይቀየር እንጂ ሸሪዓህ አይቀየርም። እኛ ሸሪዓን አልደነገግነውም፤ የደነገገው አላህ ነው። ያልደነገግነውን አናሻሽልም። እነርሱ ግን ረቂቁን ያወጡት ራሳቸው ስለሆኑ ራሳቸው አሻሽለው ይምጡ።
Period


||
t.me/MuradTadesse
x.com/MuradTadesse
fb.com/MuradTadesseOfficial
ASD AJ LAH
ትኩረት ያልሰጠነው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ =========================== (ይህ ጉዳይ ከጸደቀ በኋላ ሌላ ዙሩ በከረረ ትግል ውስጥ ሳንገባ በፊት ከወዲሁ እምነታችንን በማይነካ መልኩ መዘጋጀቱን ማረጋገጥ አለብን!) || ካስታወሳችሁ ከአንድ ወር በፊት ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችና ከተለያዩ የኃይማኖት ተወካዮች ጋር በተናጠል ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በተለይ…
መቃወም ያለብን ከመጽደቁ በፊት ነው። ምክንያቱም ያለአግባብ ሌላ መስዋዕትነት ላለመክፈል!
ይህ ማለት ግን ቢጸድቅ ራሱ እንደተለመደው መስዋዕትነት ከፍለን እምነታችንን እናስከብራለን እንጂ አንድ ጊዜ ከጸደቀ የማይነካ ነው ማለት አይደለም። በባሌም በቦሌም እምነታችንን የሚነካን ነገር መጋፈጣችን ላይቀር ነገር፤ አጉል ሌላ ገመድ ጉተታ ውስጥ ባያስገቡን ጥሩ ነው። እነርሱም ያለው ሃገራዊ ተጨባጭ አንሷቸው ሌላ የግጭት ድግስ ባይጠምቁ ይሻላል።
ሙስሊም በእምነቱ ስለማይደራደር ከታሪክ ቢማሩ ይሻላል።




ለጉዳዩ አዲስ የሆነ ይህን ጽሑፍ ያንብብ፦
https://t.me/MuradTadesse/35687
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 0⃣4⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣
ኒካህ ለማሰር በ3500 የተከራየሀውን ቤት አልጋ ብቻ ሲሞላው ትንሿን ቤትህን የምታይበት አተያይ😓
እንግዳ ሆኘ በተጠራሁበት ቤት ምግብ ሲቀርብ

Me:- ባላየ
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልስነይን 0⃣5⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኑ ጘዛን ላስታውሳችሁ 🇵🇸💣
የአብዛኛው ወጣት ጥያቄ ይመስለኛል...

"የቱ ጋር ነው የተሳሳትኩት ፈጣሪዬ??.. ለምን እድገቴ እንዲህ የዘገየ መሰለ?.. የቱ ነገር ነው ከህልሜ ጋር ያለኝን ርቀት ያሰፋብኝ?.. የቱ ልምምዴ?.. የትኛውስ ክፉ ስራዬ ነው መንገዴን ያረዘመው?......"

ወጣቱ ይጠይቃል.. አሁን ግን የምር ነው የሚጠይቀው.. መልሱ ደግሞ ለአሁን አጥጋቢ ባይመስለንም እንዳንሰላች.. 🙏
የእውነት ፈጣሪያችን የሻትነውን ሁሉ የሚሰጠበት የራሱ የሆነ ፍፁም ትክክል የሆነ ወቅት አለው.. 😊

'ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ የሰራው በጊዜው ነው አዎ በጊዜው!!.. በእርግጥም እኛም ቀን አለን እሺ አህባቢ 👐


Afdel
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 0⃣6⃣ #ዙልቀዓዳ  1⃣4⃣4⃣5⃣
ወንድም ፈቂህ ገለቶ ወደ አኼራ መሄዱን ሰምተን አዝነናል።
በአንድ ኢንተርቪው ላይ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለቤበሚያደርገው የዳዕዋ ስራ ምክንያት በቀናት ልዩነት ሶስት ግዜ እንደታሰረ እንዲሁም ከቤተሰቦቹ ከአካባቢው ሰዎች ተፅእኖ ያድርበት እንደነበር ሲያስረዳ ፅናቱን ለራስ ያስመኝ ነበር።
አላህ ይዘንለት
ASD AJ LAH
ወንድም ፈቂህ ገለቶ ወደ አኼራ መሄዱን ሰምተን አዝነናል። በአንድ ኢንተርቪው ላይ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለቤበሚያደርገው የዳዕዋ ስራ ምክንያት በቀናት ልዩነት ሶስት ግዜ እንደታሰረ እንዲሁም ከቤተሰቦቹ ከአካባቢው ሰዎች ተፅእኖ ያድርበት እንደነበር ሲያስረዳ ፅናቱን ለራስ ያስመኝ ነበር። አላህ ይዘንለት
ይሄ ዛሂድ ይህ መንገደኛ የአላህ ባሪያ ማለፉን ሰማሁ😢
ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን !

ዱኒያን ለአላህ ብሎ ትቶ በዝህድና የአላህና መልእክተኛውን መልእክት እያስተላሉፉ ኖሮ መሞት ምንኛ መታደል ነው !

እንዳለመታደል ሆኖ ልፋቱን ባናግዘውም ተገቢውን ክብር ባንሰጠውም አላህ ግን አንዱንም መልካም ስራውን ሳያስቀር በብዙ አባዝቶ ትልቅ ደረጃን እንደሚያጎናፅፈው ተስፋ እናደርጋለን !

አላህ ሆይ በራህመትህ ተቀበለው ከዚህች ዱኒያ በበለጠቺዋ ጀነትህም አጣቅመው !

ሰዒድ
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ.pdf
1.9 MB
ይህንን ቻሌንጅ ተቀላቀሉ
==================
ይህንን ባለ 15 ገፅ የመንግስትንና የኃይማኖቶችን ግንኙነት በተመለከተ በዝርዝር ያብራራል የተባለለትን አዲሱን ረቂቅ አዋጅ ሶፍት ኮፒ በስልካችሁ ላይ ላለ ሰው ሁሉ፣ በምታገኙት ግሩፕና ቻነል እንዲሁም በማንኛውም ገፅ ላይ በማሰራጨት መረጃው በእያንዳንዱ ሙስሊም እጅ ላይ ደርሶ እንዲያነበው እናድርግ።

ለዚህ ረቂቅ አዋጅ ግብዓት ይሆን ዘንድ የቀረበውን ባለ 164 ገፅ ጥናት ማንበብ ለሚፈልግም ሶፍት ኮፒው በዚህ ሊንክ ይገኛል።

https://t.me/MuradTadesse/35708

*
ሰው ጽሑፉን ዝም ብሎ ቢያነበውም ከላይ ሲመለከታቸው አንቀፆቹ ጤነኛ ሊመስሉት ስለሚችሉ፤ ፍንጭ ይሰጠው ዘንድ ረቂቅ አዋጁ ከኛ ከሙስሊሞች ጋር የሚያጋጩትንና ጥያቄ የሚያጭሩ 15+ ነጥቦች የተጠቀሱበትን ይህንን ጽሑፍም ጨምሩለት።

https://t.me/MuradTadesse/35742


ይህንን የአዲሱን ረቂቅ አዋጅ PDF ለሁሉም በማሰራጨት መረጃው እንዲደርሰው እናድርግ። የላ ቻሌንጃችን ይጀመር!

አብዛሃኛው ሰው ከጀርባ ምን እየተካሄደ እንዳለ መረጃው የለውም። ጭራሽ አዲስ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ራሱ እንኳን ከመረጃው የራቀው ማኅበረሰብ ሚዲያ ላይ አለን የሚለው ራሱ በበቂ ሁኔታ የሰማ አይመስለኝም። ወሬውን ቢሰማም ዶክመንቱ በተጨባጭ ያልደረሰው ብዙ ነውና ይህንን በማድረግ ግንዛቤ እንፍጠር።

የፌዴራሉ መጅሊስም በዚህ ጉዳይ ተቃውሞ ያወጣውን ባለ 4 ገፅ መግለጫ አያይዘን እናሰራጨው። መግለጫው በዚህ ሊንክ ይገኛል።
https://t.me/MuradTadesse/35632?single
ከተቋማችንም ጎን እንቁም።

የላ! ከአሁኑ ይጀመርና ያሰራጨ ሰው ለማነቃቂያ ስክሪን ሹቱን ኮመንት ላይ አስቀምጡት!
ASD AJ LAH
ወንድም ፈቂህ ገለቶ ወደ አኼራ መሄዱን ሰምተን አዝነናል። በአንድ ኢንተርቪው ላይ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለቤበሚያደርገው የዳዕዋ ስራ ምክንያት በቀናት ልዩነት ሶስት ግዜ እንደታሰረ እንዲሁም ከቤተሰቦቹ ከአካባቢው ሰዎች ተፅእኖ ያድርበት እንደነበር ሲያስረዳ ፅናቱን ለራስ ያስመኝ ነበር። አላህ ይዘንለት
ከአሳሳ እስከ ሮቤ፣ ከኮኮሳ እስከ አዳማ ፣ ከአርሲ እስከ ባሌ፣ እስከ ሸገርና ጎንደር ድረስ ጭምር ታሪክ አለን ከዚህ ሰው ጋር፡፡
በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በጎዳና ላይ ደዕዋ ሲያደርግ ታውቁታላታችሁ፡፡ ምንም ማንንም የማይፈራ ሙጃሂድ ነው። ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በየፖሊስ ጣቢያው ሲንከራተትም አጋጥሞኛል፡፡

ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀን ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ አላረፈም። ኢስላምን ለማድረስ ሁሌ እንደተጓዘ ስለማየው ቤት ይገባ ይሆን ብዬ እጠይቃለሁ ብዙ ጊዜ፡፡ ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ማረፉን ሰማሁ፡፡

ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንልህ፡፡

ሰው በኖረበት ነገር ላይ ይሞታል፤
በሞተበት ነገር ላይም ይቀሰቀሳል፡፡

ደጋግ ባሮችህ ወዳንተ እየመጡ ነው።
አላህ ሆይ!
ዐለይከ ረበና ቢሑስኒልኺታሚ እንላለን ።

Abx