ASD AJ LAH
753 subscribers
1.72K photos
194 videos
3 files
486 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
" የኦንላይን ፈተናው በተመረጡ 25 ከተሞች ይሰጣል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ገልጿል።

ተፈታኝ ተማሪዎች በኦንላይን ለሚሰጠው ፈተና እንዲዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከሁሉም ክልሎች በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና ጎን ለጎን የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው #ቤተሰቦቻቸው_ጋር_እያደሩ ፈተናውን ይወስዳሉ ሲሉ አሳውቀዋል።

ወ/ሮ አየለች ፤ ተማሪዎች ለፈተናው እንዲዘጋጁ፣ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ ወላጆችንም ልጆቻቸውን እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ፈተናው በኦንላይን የሚሰጥባቸውን 25 ከተሞች በዝርዝር ይፋ አላደረገም።

የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopia
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 2⃣6⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
ይህ ሀላል ነው ይህ ሀራም ነው ብሎ የሚነግርህ የሚንሺካሾክልህ ድምፅ ውስጥህ ካለ አደራህን ይህን ድምፅ እንዳታጣው።

ነጂብ መሕፉዝ
የዛሬውን ውሎህን በአላህ መልእክተኛ ላይ ሰለዋት በማውረድ ጀምረው
..አንዳንድ መከራዎች ፈተናዎች ምንነታቸውን እንጂ የሚፈጥሩት ስሜት የሚገለፅ አይደለም..በዝምታ ውስጥ የሚብላላ እና የሚፋጅ ረመጥ ነው..እሷም ከዚህ የተለየ አልገጠማትም ሰው መሆን ጋር ተያይዞ የሚመጣው ስንኩልና እሷም ጋር ደርሷል ውስጧን ዳብሷታል ወደፊት ያለችው ቀርቶ አሁኗ ባላሰበችው አቅጣጫ ሲጓዝ ወደ መስመሩ ለመመለስ እየታገለች ነው በስስ ፈገግታ የታጀበ ፊት ግን ተለይቷት አያውቅም አዎ እንደነበረችው መቆየት ነበረባት በሷ ፅኑ ወኔ ፀንተው የሚኖሩ ነፍሶች በዙርያዋ አሉና ጌታዋን ስታማርር አትገኝም ለጠያቂዎቿ ሁሉ መልሷ "አልሐምዱሊላህ" ነው

..በአንዱ ቀን ስትብከነከን አጠገቧ ደረስሁ..ከጥሞናዋ ላናጥባት አልፈለኩም..ድምፅ ሳላሰማ አጠገቧ ተቀመጥኩ..ከጥቂት ቆይታዎች በኋላ እንደመባነን አለችና ሰላምታ አቀረበችልኝ..ያ የሚያስደንቀኝ ሰላማዊ ፈገግታ ፊቷ ላይ አለ ምን አይነት አቻቻል ነው ብዬ ተገረምኩ..የራሴን ደካማነት እና ባዶነት ከሷ ፈገግታ ላይ ሸከፍኩ..ምን ሲያብከነክናት እንደነበር ጠየቅኳት..ከጥቂት የዝምታ ቆይታዎች በኋላ ፊቷን ልትጠልቅ በምታዘቀዝቀው ፀሓይ ሰጥታ ..
"..አሏህ ግን የእዝነቱ ረቂቅነት አይገርምህም..?!» ስትል ንግግሯን ጀመረች..
«ሸሽቸው አልራቀኝም..ቀርቤው አላጣውም..ለምኜው አላሳፈረኝም..ሀቁን አጓድዬ አልተወኝም..ሳምፀው አላባረረኝም..ሳማርረው አልተወኝም..በመሐሉ መንገድ ስስት ደሞ በተለያዩ ፈተናዎች ወደሱ ይጠራኛል..እኔ በፈተናዎቼ እፅናናለሁ..የሚወደውን እንጂ አይጣራምና..»ብላ ንግግሯን ገታች..ትናንሽ አይኗቿ እንባን አዝለው የፀሃዩ ነፀብራቅ ሲያርፍባቸው ሉል ይመስላሉ..በረጅሙ ተነፈሰች..ከዚያም ፈገግ እያለች እንዲህ ስትል ንግግሯ ላይ አከለችበት
«..አላህዋ ለኔ የዋለውን ለማን ዋለ?! የሚለው ነው ከሐሳቤም ገዝፎ ይዞኝ የጠፋው..»

ነሲም ሚራዥ
ASD AJ LAH
እነfatherዎች ሽምግልና ሄደው ሲሰክሱ ሳክስ 1 ልጃችሁን ካልሰጣችሁን አንቀመጥም…😅 #ሸዋል
ሳክስ 2

ልጅየው ደህና ጀንጅኖ ያሳመናትን ሊያጭ ሽማግሌ ቢልክ ሽማግሌዎቹ "ባይገርማችሁ ከልጆቼ በላይ ነው ምወዳት"😅
አይተዋት ራሱ አያውቁም እኮ🤣

#ሸዋል
ASD AJ LAH
ሳክስ 3 የልጅት ወላጆች ቀድመው በልጃቸው ውሳኔ ተስማምተው ሳለ "እስኪ የዛሬ አስር አመት ኑ!"😅 #ሸዋል
ሳክስ 4

ባል ሚሆናትን ብቻ ከመመኘታቸው ጋር "ልጁ ምን አለው? በምንድን ሚያስተዳድራት? ምንድን ነው የሚያበላት"

ሽማግሌዎቹ "አይዞት የ……አባት ምን ቢያጣ የሚያበላት አሳር አይጠፋውም"😓

#ሸዋል
ASD AJ LAH
ሳክስ 4 ባል ሚሆናትን ብቻ ከመመኘታቸው ጋር "ልጁ ምን አለው? በምንድን ሚያስተዳድራት? ምንድን ነው የሚያበላት" ሽማግሌዎቹ "አይዞት የ……አባት ምን ቢያጣ የሚያበላት አሳር አይጠፋውም"😓 #ሸዋል
ሳክስ 5

የልጅት አባት "ልጁ ዲኑ ላይ እንዴት ነው? "

ሽማግሌዎች" የዱሀ እና የለይል ሰላትን ጨምሮ በቀን 7 ግዜ ይሰግዳል ባይገርማችሁ በየቀኑ መስጂድ እግራቸውን አስፍተው እየቆሙ መስጂድ ከሚያጣብቡ እና የውሀ ቧንቧ ከሚሰብሩት መሀከል ነው"



የልጅት አባት ወድያውኑ ኦ😮

#ሸዋል
ሁለተኛዬን ሽማግሌ ሆኘ ልድረው የሚፈልግ ካለ በውስጥ ያናግረኝ ስለነበረን ቆይታ ከልብ አመሰግናለሁ በሌላ ሳክስ እስክንገናኝ መልካም አዳር

#ሸዋል
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልስነይን 2⃣7⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
ASD AJ LAH
Photo
አንዳንድ ሰዎች እልም ጥፍት ብለው ይቆዩና ድንገት መጥተው ሳይቆዩ በድጋሚ እልም ጥፍት ይሉባቹሃል ። አላህን የሚፈሩት (ተቂይ) የሆኑት ላላችሁ ኒዕማ ማሻ አላህ ብለው ለገጠማችሁ ችግር እንደናንተው ተጨንቀው በዱዓ ያስቧቹሃል ። ዳግም የሚመጡትም ከነገሩ ጋር ቀጥለዋል ወይስ ተፈርጀዋል የሚለውን ለማወቅ ሲሆን ሌሎቹ ምን ላይ እንደሆናችሁ ለማወቅ ብቻ ነበር ወደ እናንተ የሚመጡት ። « በልጠውኛል ? ፣ ከእኔ የተሻለ ህይወት ላይ ናቸውን » ይህን ለማወቅ ብቻ 🙂

***
ይጠግኑልኝ ይሆን ብላችሁ የነገራችኋቸውን ስብራት ይባስ እንዳይጠገን አድርገውት ይሄዳሉ ። ህመማችሁን ፣ ችግራችሁን ዋጥ አድርጋችሁ :- « እንዳይደብራችሁ ! አልወደቅንም ፣ አልተሰበርንም አንላችሁም ; ከወደቅንበት ግን አልቀረንም እንደተሰበርን አልኖርንም አላህ አንስቶናል ። ነፍሳችንን ለአላህ ሰጥተናል በሏቸው ። መኽሉቅ ዘንድ ኻሊቁን እንዳንከስ አደራ ። የሰብር ትርጉም ይህ ነውና በምስጋና ቻል በማድረግ እንለፍ ።

አብዱ ረዛቅ

መልካም ውሎ
ሰውነታቸው በጥይት አካላቸው በእሳት አሩር እየተጠበሰ "አላሁ አክበር" የሚለውን መፈክር ደግመው ደጋግመው የሚያሰሙ ፅኑዎች

ሞት ሲያንዣብብ ከበራቸው በ"ላኢላሀ ኢለላህ" ህይወታቸውን የሚቋጩ ልጆቻቸው ከስማቸው ይልቅ የጌታቸውን ስም እንዴት መጥራት እንዳለባቸው የሚያውቁ ትውልዶች

አዎ
መላእክት ክንፎቻቸውን የዘረጉባት ሀገር የተባረከች የፍልስጤም ምድር። የእምነት ጽናትን የጨበጡ ፍጡሮች መፍለቂያ እንደ አለት የጠነከረ እምነት ባለቤቶች
ኢማን ኢማን የሚሸትበት ወንድ ተፀንሶ ጀግና የሚወለድባት የሙጃሂዶች መፍለቂያ

እናንተ የፍልስጤም ህዝቦች ሆይ ታገሱ


Mahi mahisho
ከሶፍ ውጭ ለብቻ መቆም
~
ሶፍ ሳይሞላ ለብቻ መቆም ክልክል ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ፦
እንዲህ ብለዋል፦
لا تصح صلاة المنفرد خلف الصف
"ከሶፍ ኋላ ተነጥሎ ለሚሰግድ ሰው ሶላት የለውም።" [አሕመድ፡ 15862]

ስለዚህ:-
1- ሶፍ ያልሞላ ከሆነ ለብቻ መቆም በጥብቅ የተከለከለ ነው።
2- ሶፉ የሞላ ከሆነ፣ ዘርዘር ብለው በመሰለፋቸው ሳያስቸግር የሚያስገባው ክፍተት ካገኘ አጠጋግቶ ይግባ።
3- የሚያስገባው ክፍተት ከሌለ ብቻውን ቆሞ ይሰግዳል። አላህ እንዲህ ይላል፦
{ فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُمۡ }
"አላህንም የቻላችሁትን የክል ፍሩት።" [አተጋቡን፡ 16]

ከዚህ ውጭ ሶፍ ላይ ያለን ሰው ወደ ኋላ መሳብ አይቻልም። ምክንያቱም ይህንን የሚደግፍ ሶሒሕ ማስረጃ የለምና። በዚህ ላይ የሚጠቀሰውም ሐዲሥ ደካማ ነው። በዚያ ላይ ከሶፍ አውጥቶ ወደ ኋላ መጎተት ጥፋቶች አሉበት።
* ሰውን መወስወስ አለበት።
* የሚሳበውን ሰው የተሻለ ደረጃ ካለው ፊተኛው ሶፍ ዝቅ ማድረግ አለበት።
* የፊተኛው ሶፍ ላይ ክፍተት መፍጠር አለበት። ይህም በጥብቅ የተከለከለ ነው። አዋቂው አላህ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል
IbnuMunewor
ማን ያውቃል
በሕይወትህ ፈጽሞ ያላሰብከው መልካም ነገር ሊፈፀም ጫፍ ደርሶ ይሆናል። አትመለሰ፣ ተስፋ አትቁረጥ።

ABX
በቀን 3 ጊዜ የምትበሉ ሰዎች ምን አስባችሁ ነው? ሀሰን አል በስሪ (ረህመቱላሂ አለይህ) በቀን 3 ጊዜ ለሚበላ ሰው ቤተሰቦቹ መኖ ቤት ይገንቡለት ብለዋል:: አስቡበት:: ምግብ ቀንሱ:: ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትም ሆነ ነፍስ ከአላህ ጋር በሚኖራት ግንኙነት ወደ አላህ ቀረብ እንድትል ትልቅ አስተዋፅዖ አለው:: ሆድ ሲሞላ ጭንቅላት ባዶ ይሆናል ይባልስ የል¿

Mohammadammin
ከፊልም የተወሰደ ምስል ነዋ የሚመስል…ይህ በገሀዱ ዐለም በኛዋ ውድ ሀገር ፈለስጢን የተፈፀመ ውድመት ነው። አላህ ብስራቱን ቅርብ ያድርግላቸው