ASD AJ LAH
667 subscribers
1.71K photos
193 videos
3 files
483 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልኽሚስ 2⃣3⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
አንዳንዴ አብሽር የሚለው ቃል ብቻ ስሜትህን አይለውጠውም ። ከፍቶሀል አዝነሀል አጠገብህ ያሉ ሰዎች አብሽር ብቻ ይሉሀል ። የነሱ አብሽር ማለት በአንዴ ስሜትህን የሚቀይረው ይመስላቸዋል ። የሚያረጉልህ የሚሉህ ቢጠፋቸው እንደሆነ ግልፅ ነው ። ነገር ግን ስሜትህ በአንዴ እንዲቀየር ይጠብቃሉ ። ያንተን መቸገር ያንተን ማጣት ያንተን ክፉ ስሜት ውስጥ መግባት ያንተን ማዘን ከሌሎች ጋር ያነፃፅሩታል ። አንተ እንድትደሰት ሌላ የተከፋ ወይም ያዘነ ሰው ምሳሌ መሆን አለበት ወይ ? ለማዘንም ለመከፋትም የራሴ ጉዳዩች አይበቁኝም ወይ ? ትወጣለህ ትወርዳለህ ምንም የምታየው ነገር የለም ። በዙሪያዬ አሉ የምትላቸው ሰዎች እነሱ ሲፈልጉህ እንጂ አንተ ስትፈልጋቸው አታገኛቸውም ። ላንተ አንድ እርምጃ መጓዝ ይከብዳቸዋል ። በሁሉም ነገር ተስፋ ትቆርጣለህ ። በቃ አለ አይደል ድንገት የሆነ ነገር በመጣ'ና በወሰደን ብለህ ምትመኝበት ስሜት እሱ ስሜት ሲሆን አብሽር የሚለው ቃል ብቻ ስሜትህን አያስተካክለውም ።

©
ለነገሮች በምትሰጠው መልካም ጥርጣሬና ለሰዎች በምትመኘው መልካም ነገር ተጠቃሚ ትሆናለህ... አሲያ አለይሃ ሰላም የፊርዓውን ባለቤት ሙሳን ዐለይሂ ሰላም ህፃን ሆኖ ከባህር ላይ ሲያነሱት "

قُرَّتُ عَيْنٍ لِّي وَلَكَ ۖ لَا تَقْتُلُوهُ عَسَىٰ أَن يَنفَعَنَا أَوْ نَتَّخِذَهُ وَلَدًا
«ለእኔ የዓይኔ መርጊያ ነው፡፡ ለአንተም፡፡ አትግደሉት፡፡ ሊጠቅመን ወይም ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላልና» አለች፡፡
በነበራት መልካም ጥርጣሬ ምክንያት ሙሳ ልጇ ሆነ፣እሱን በምከተሏ ነብይዋ ሆነ ወደ ጀነትም መራት..ከጀነት በላይ ምን አለ?

ነቢ ሙሳ ውሃ ያጠጣጣላቸው እነዚያ አባታቸው ሷሊህ የሆነው ሴቶች አንዷ ለአባቷ "

يَا أَبَتِ اسْتَأْجِرْهُ ۖ إِنَّ خَيْرَ مَنِ اسْتَأْجَرْتَ الْقَوِيُّ الْأَمِينُ
«አባቴ ሆይ ቅጠረው፡፡ ከቀጠርከው ሰው ሁሉ በላጩ ብርቱው ታማኙ ነውና» አለችው፡፡"
ለሙሳ ኸይር በመመኘቷ ምክንያትም ሙሳን የማግባት እድል አገኘች።
©

اللهم صل وسلم وزد وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وعلى آله وصحبه أجمعين
በምድር እና በሰማይ ተወዳጅነትን የምታገኙበት…መልካም ስራቸው ከሚበዛላቸው፣ ጊዜያቸውን በኸይር ከሚያሳልፉት፣ ለወንጀላቸው መሀርታን አግኘተው በጀነት ከሚበሰሩት ሰዎች መሀል የምንሆንበት ወዶ በላካቸው እና  እዝነቱን በእርሳቸው ባሳየን ወዱ ነብያችን የበዛ ሰለዋት ምናወርድበት በሱራህ አልካህፍ በዱዓእ በሰላት በቲላዋ በተሳኩ ምኞቶች በጀባሩ ራህመት የታጀበ የተዋበ ምርጥየ ጁምዐን ተመኘሁ።

https://t.me/asdajlahh
« ሰለዋት ማለት ያዋጣል
ከችግር ቶሎ ያወጣል »

እውነት ነው በዳዒሙ ሹም ላይ ሰላትና ሰለዋት ማውረድ ከጭንቅ ፣ ከድህነት ፣ ከልፍስፍስነት ፣ ከበሽታና ሀሜት ከተሰኙ ችግሮች ያወጣል ። ሪዝቁ እንዲሰፋ ፣ ፊቱ እንዲያበራ ፣ መንፈሳዊም አካላዊ ጥንካሬ እንዲኖረው የሚሻ ሰው ሰለዋትን ያበዛል ። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላን ማውሳት በነብዩ አለይሂ ሰላት ወሰላም ላይ ሰለዋት ማውረድ የቀደምት አበዎች ፣ የደጋጎች ፣ የዐሪፎች ፣ የመሻይኾች ምግባር ብቻ ሳይሆን የአላሁ ተዓላና የነብዩ አለይሂ ሰላም ትዕዛዝ ነውና ። የመረጣቸውና የተመረጡት በዚህ ተጠምደዋል ።

«… እርሱን ተዉት ; አላህና መልዕክተኛውን ይወዳል!» ወዷቸው ያላቀውና ያወሳቸውስ…?

ዐለይሂ አፍደሉ ሰላት ወሰላም 💚

አብዱ ረዛቅ
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ጁምዓ 2️⃣4️⃣ #ሸዋል 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣
የተላከልኝን ቴክስት ከአንድ ሳምንት በኋላ አልሀምዱሊላህ ደህና ነኝ ብየ በመመለስ ላይ
ሙገሳ ሲበዛ…
ደህና እደሩ
ህንፃህን ለማሰራት ሚሊዮን ብር መድበህ መሀንዲስ ትቀጥራለህ ፤ የምትጀምረው ንግድ እንዲሰምር ቢዝነስ ምሩቅ ትቀጥራለህ ፤ ህመምህ እንዲፈወስ ጥሩ ሀኪም ትፈልጋለህ…ታድያ የአንተ የአለማወቅ ችግር እንዲፈታ ዐሊሞችን ማመከሩን ለምን ዘነጋህ…ለምን ራስህ ፈትዋ ሰጪ አደረግክ?

ፈጅር ሰላት ላይ አንድ ዳዒ ወደራሳችን መለስ ብለን እንድናስብ ብሎ የጠየቀን ጥያቄ
ሞት ማንንም አያለያይም…መለያየት ማለት ያኔ ባለ ቀኝ እጆቹ ወደ ጀነት ባለግራዎቹ ወደጀሀነም ሲባሉ አንደኛችን ወደጀነት አንደኛችን ደግሞ ወደጀሀነም የሄድን ግዜ ነው።

አላህ መልካሙን ይግጠመን
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ሰብት 2️⃣5️⃣ #ሸዋል 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በሀገራችን ታካሚዎች እና በጤና ባለሞያው መሀል የሚፈጠረውን "የንግግር ክፍተት" በመጠኑም ቢሆን እነዚህ ነጥቦች ያስተካክሉታል ብዬ አሰብኩ።

አያድርግባቹ እና ምን አልባት እናንተ ወይም የእናንተ የሆነ ሰው ከታመመባቹ እነዚህን ነገሮች ልማድ በማድረግ ብዙ ነገር ማትረፍ ትችላላቹ

1. ሁልጊዜ ሀኪማችሁን እነዚህን ጥያቄዎች መጠየቅ
👉 የተገኘብኝ በሽታ ምንድነው?
👉 በሽታው ከምን ሊመጣ ቻለ?
👉 በሽታውን እንዴት መከላከል ይቻላል?
👉 በሽታው ከሰው ወደሰው ይተላለፋል?

2. በተለይ የቀዶ ህክምና የሚደረግላቹ ሰዎች መጠየቅ ያለባቹ
👉 ከቀዶ ህክምና ውጪ ሌላ አማራጭ ህክምና አለው?
👉 የቀዶ ህክምና ባይደረግልኝ ምን ሊከሰት ይችላል?
👉 ያሉት የቀዶ ህክምና አማራጮች ምንድናቸው?
👉 የታቀደው የቀዶ ህክምና ምንድነው? እና ከተሰራ በኋላ ውጤቱ ምንድነው?
👉 የቀዶ ህክምናው ከተሰራ በኋላ ማድረግ ያለብኝ የሌለብኝ ነገሮች?
👉 ከቀዶ ህክምናው ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮች ምንድናቸው?

3. የታዘዘላችሁን የምርመራ ውጤቶች እና መድሀኒቶች በፎቶ 📸 መያዝ እንዲሁም አለርጂክ የሆነባችሁን መድሀኒት ስም ለይቶ ማወቅ።

👉 በተለይይ ለተጓዳኝ በሽታዎች ለረዥም ጊዜ በክትትል የምትወስዷቸው መድሀኒቶች ካሉ በተቻለ መጠን ስማቸውን መጠናቸውን እና አወሳሰዳቸውን ማወቅ።

4. ሁልጊዜ ሆስፒታል🏥 በተለይ ሪፈር ተብላቹ ወደ ሪፈራል ሆስፒታል ስትሄዱ 🚑 ከዚህ በፊት የነበራችሁን የምርመራ ውጤቶች እና የወሰዳችሁትን መድሀኒቶች ወይም እየወሰዳችሁት ያለ መድሀኒት ካለ ይዞ መሄድ።

5. በተቻለ መጠን የጤና ታሪካችሁን ስለሚያውቀው ክትትላችሁን በአንድ ሀኪም ቢያደርጉ ይመረጣል።

ታዲያ እነዚህን ከላይ የጠቀስኳቸውን ነጥቦች ልማድ ማድረግ ለታካሚዎች ከምታስቡት በላይ
👉 ያላግባብ ከሚደረግላቹ ተደጋጋሚ ምርመራዎች
👉 ያላግባብ ከሚታዘዝላቹ ተደጋጋሚ መድሀኒቶች እንዲሁም
👉 ከአላስፈላጊ ወጪ እና የጊዜያቹ መባከን ይጠብቃቹሀል።

👉 እንዲሁም ለጤና ባለሞያው በቀላሉ የጤና ታሪካችሁን እንዲረዳ እና ተገቢውን ምርመራ እንዲሁም ህክምና በጊዜ እንድታገኙ ይረዳቹሀል ማለት ነው።

👨‍⚕️ ዶ/ር ዮናታን ከተማ: በቅዱስ ፓውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ቀዶ ህክምና ሬዚደንት ሐኪም
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
" የኦንላይን ፈተናው በተመረጡ 25 ከተሞች ይሰጣል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ገልጿል።

ተፈታኝ ተማሪዎች በኦንላይን ለሚሰጠው ፈተና እንዲዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከሁሉም ክልሎች በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና ጎን ለጎን የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው #ቤተሰቦቻቸው_ጋር_እያደሩ ፈተናውን ይወስዳሉ ሲሉ አሳውቀዋል።

ወ/ሮ አየለች ፤ ተማሪዎች ለፈተናው እንዲዘጋጁ፣ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ ወላጆችንም ልጆቻቸውን እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ፈተናው በኦንላይን የሚሰጥባቸውን 25 ከተሞች በዝርዝር ይፋ አላደረገም።

የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopia
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 2⃣6⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
ይህ ሀላል ነው ይህ ሀራም ነው ብሎ የሚነግርህ የሚንሺካሾክልህ ድምፅ ውስጥህ ካለ አደራህን ይህን ድምፅ እንዳታጣው።

ነጂብ መሕፉዝ
የዛሬውን ውሎህን በአላህ መልእክተኛ ላይ ሰለዋት በማውረድ ጀምረው
..አንዳንድ መከራዎች ፈተናዎች ምንነታቸውን እንጂ የሚፈጥሩት ስሜት የሚገለፅ አይደለም..በዝምታ ውስጥ የሚብላላ እና የሚፋጅ ረመጥ ነው..እሷም ከዚህ የተለየ አልገጠማትም ሰው መሆን ጋር ተያይዞ የሚመጣው ስንኩልና እሷም ጋር ደርሷል ውስጧን ዳብሷታል ወደፊት ያለችው ቀርቶ አሁኗ ባላሰበችው አቅጣጫ ሲጓዝ ወደ መስመሩ ለመመለስ እየታገለች ነው በስስ ፈገግታ የታጀበ ፊት ግን ተለይቷት አያውቅም አዎ እንደነበረችው መቆየት ነበረባት በሷ ፅኑ ወኔ ፀንተው የሚኖሩ ነፍሶች በዙርያዋ አሉና ጌታዋን ስታማርር አትገኝም ለጠያቂዎቿ ሁሉ መልሷ "አልሐምዱሊላህ" ነው

..በአንዱ ቀን ስትብከነከን አጠገቧ ደረስሁ..ከጥሞናዋ ላናጥባት አልፈለኩም..ድምፅ ሳላሰማ አጠገቧ ተቀመጥኩ..ከጥቂት ቆይታዎች በኋላ እንደመባነን አለችና ሰላምታ አቀረበችልኝ..ያ የሚያስደንቀኝ ሰላማዊ ፈገግታ ፊቷ ላይ አለ ምን አይነት አቻቻል ነው ብዬ ተገረምኩ..የራሴን ደካማነት እና ባዶነት ከሷ ፈገግታ ላይ ሸከፍኩ..ምን ሲያብከነክናት እንደነበር ጠየቅኳት..ከጥቂት የዝምታ ቆይታዎች በኋላ ፊቷን ልትጠልቅ በምታዘቀዝቀው ፀሓይ ሰጥታ ..
"..አሏህ ግን የእዝነቱ ረቂቅነት አይገርምህም..?!» ስትል ንግግሯን ጀመረች..
«ሸሽቸው አልራቀኝም..ቀርቤው አላጣውም..ለምኜው አላሳፈረኝም..ሀቁን አጓድዬ አልተወኝም..ሳምፀው አላባረረኝም..ሳማርረው አልተወኝም..በመሐሉ መንገድ ስስት ደሞ በተለያዩ ፈተናዎች ወደሱ ይጠራኛል..እኔ በፈተናዎቼ እፅናናለሁ..የሚወደውን እንጂ አይጣራምና..»ብላ ንግግሯን ገታች..ትናንሽ አይኗቿ እንባን አዝለው የፀሃዩ ነፀብራቅ ሲያርፍባቸው ሉል ይመስላሉ..በረጅሙ ተነፈሰች..ከዚያም ፈገግ እያለች እንዲህ ስትል ንግግሯ ላይ አከለችበት
«..አላህዋ ለኔ የዋለውን ለማን ዋለ?! የሚለው ነው ከሐሳቤም ገዝፎ ይዞኝ የጠፋው..»

ነሲም ሚራዥ
ASD AJ LAH
እነfatherዎች ሽምግልና ሄደው ሲሰክሱ ሳክስ 1 ልጃችሁን ካልሰጣችሁን አንቀመጥም…😅 #ሸዋል
ሳክስ 2

ልጅየው ደህና ጀንጅኖ ያሳመናትን ሊያጭ ሽማግሌ ቢልክ ሽማግሌዎቹ "ባይገርማችሁ ከልጆቼ በላይ ነው ምወዳት"😅
አይተዋት ራሱ አያውቁም እኮ🤣

#ሸዋል