ASD AJ LAH
755 subscribers
1.73K photos
194 videos
3 files
487 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
ASD AJ LAH
የጎንደሩን ጭፍጨፋ የደገፉ እና ያስተባበሩት አባ ዩራኒየም ወደ በፊቱ የሀላፊነት ቦታቸው መመለሳቸውን ሀሩን ሚድያ ዘግቦ አየሁት
በሚያዝያ 18/2014 የጎንደር ጭፍጨፋ ወቅት በግጭት ሰባኪነታቸውና በሀሰተኛ መረጃቸው የሚታወሱት ሊቀ ኅሩይ አባ ዮሴፍ ደስታ ወደ ቀድሞ ሀገረ ስበከታቸው መመለሳቸው ተገለጸ

ሀሩን ሚዲያ፥ ሚያዝያ 18/2015

በጎንደር ሙስሊሞች ላይ በተፈጸመው ጭፍጨፋ በወቅቱ በግጭት ሰባኪነታቸውና በሀሰተኛ መረጃቸው የሚታወሱት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ የነበሩት ሊቀ ኅሩይ አባ ዮሴፍ ደስታ በፈጸሙት መሠረት የለሽ ውንጀላ ሳቢያ በወቅቱ ከቤተ ክርስቲያኗ እንዲሁም ከሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ውግዘት አስተናግደው ነበር። በዚህም ሳቢያ እስካሁኑ ወቅት ድረስ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ውስጥ ሲሰሩ ቆይተዋል። በወቅቱ ተናግረውት የነበረውና የጎንደር ሙስሊም 500 ሚሊየን ብር የሚገመት ዩራኒየም ቦንብ እያብላላ መሆኑን የገለጹበት መንገድ በብዙ ሰው ዘንድ እጅግ ያስገረመና ያነጋገረ እንደ ሀይማኖት መሪነታቸውም ትዝብት ውስጥ የጣላቸው ክስተት ነበር።

አሁን ግን በጥያቄያቸው መሠረት ቀድሞ ይሰሩበት ወደነበረውና ከሙስሊሙ ጭፍጨፋ ወቅት ጋ ተያይዞ ስማቸው በጥቁር መዝገብ ወደሚታወስበት የጎንደር ሀገረ ስብከት በስራ አስኪያጅነት መሾማቸውን ለማወቅ ተችሏል። በዚህም ምክንያት ከቀድሞ ማንነታቸውና አሁን ካለው የክልሉ የሰላም ሁኔታ ጋ ተደማምሮ በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘንድ ትልቅ ስጋት መፈጠሩን የአካባቢው ሙስሊሞች ገልጸውልናል። ግለሰቡ ከተለመደው የግጭት ጠማቂነት ባህሪያቸው በመነሳት በአካባቢው ያለውን ግጭት እንዳያስፋፉትና በሙስሊሙ ዘንድ ያለውን ግፍም በማንሰራፋት እሳቱን እንዳያፋፍሙት ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው ሙስሊሞቹ ጨምረው ገልጸዋል። ሰላም ወዳድ የአካባቢው ነዋሪ ሁሉ ይህንን ጉዳይ በአንክሮ በመከታተል ከዚህ በፊት ያለፈውን አይነት አደገኛ ክስተት እንዳይደገም የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግም ህዝበ ሙስሊሙ አበክሮ ጠይቋል።

© ሀሩን ሚዲያ
የስነልቦና አማካሪ:- ለሚስትህ አንድም ቀን አበባ ገዝተህላት አታውቅም ለምን?

ባል:- አበባ እንደምትሸጥ አልነገረችኝም እኮ😓

ዶክተሩ🤦🏽‍♂
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል።

" በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ " ሲሉ አሳውቀዋል።

ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፤ " ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው " ብለዋል።

ተፈታኝ ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል።

ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ብለዋል።

#MoE

tikvahethiopia
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 1⃣9⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
ምን ይታዘዝሎት

ከእሁድ ስፖርት መልስ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ያኔ ስፖርት መስራት ምናምን የጀመርክ ሰሞን
የማታ ኢንጂነሪንግ ተምረህ ስትመረቅ የምትሰራው ህንፃ
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልስነይን 2⃣0⃣ #ሸዋል 1⃣4⃣4⃣5⃣
.....የማፍቀር ዋጋው ህመም ነው.... ታመህ የምትገዛው ደስታ ፍቅር ይባላል... "..ትላንትና እና ነገ የራሳቸው ጉዳይ.." ብለህ የማለፍ ግድየለሽ ልቦናን ፈልፍለህ ትፈጥራለህ....የአወዳደቅ ጥሩ የለውም... በፍቅር መውደቅ ግን እየቆየ የሚደምቅ ጌጥ ነው...... ልደግመው ብፈልግ የማልችልበት አይነት አወዳደቅ..... በልቤ የሚያብረቀርቁ የነበሩ የማፍቀር ድፍረት አንዳንዶቹ ስወድቅ ረገፉ... .."እሷ"ውስጥ ያለ ሌላ ቀለም ውበት በምን ይገለፃል...... ይሄስ እድለኛነት አይደል?..... በኑሮህ አሻራ ላይ የፍቅር ጣት ይነካሀል...... አንተ እድለኛ ነህ... ትወዳለህ... ትርቃለህ... ሰፌድ መሳይ ጉዞ ነው ...ክብ... ግን የማይገጥም..... አንዱ ከአንዱ የሚለያይ ይመስልሀል... ግን በፍፁም.....መንገዴ አያሳፍረኝም እኔነቴ ጋር ፀብ የለኝም...... እኔ የአጋጣሚዎቼ ውጤት ነኝ... እኔ መንገዴን መስላለሁ....

ነሲም
በተለምዶ «ያራዳ ልጅ» የሚባለው ዱኒያ ላይ ከሰው ልጆች ጋር እንዴት መኗኗር እንዳለበት አውቆ የሚኖረው ነው ። እውነት ነው ይህ ሰው አራዳ ነው ። ከአራዳዎች ጋር መኗኗር ደስ ይላል ። ቀላልና ተግባቢ ናቸው ። ላይፋቸውን እንጂ የሰው ላይፍ ላይ እንቅፋት ሲሆኑ አትመለከትም ። ሀያታቸው ሁሉ «በቃ ይመቸው!» ነው ። አኼራስ ካልክ ብዙዎቹ ያራዳ ልጆች የተሸጡበት ነው ።

የፈለገ ያራዳ ልጅ ሁን ፣ በየላውንጅና ክለቡ እሷኮ ይባልልህ ፣ ሙሉ የመሃል ልጅ ምርጥዬ ናት ብሎ ይመስክርልህ አኼራ ስትሄድ ፋራ ከሆንክ ግን ምን ጥቅም ብራዘር ?!

ደባሪ ሙድ ውስጥ ገብተው የጠፉ አሉ ። ከትርፏ ላይፏ በሚለው ሙዱን ሾፈው እጥፍ ያሉም ብዙ ናቸው ። የሱስና የጨብሲ ሙዱን ፈቶ መስጂድ የጠቀለለ ብዙ ያራዳ ልጅ አለ። ላይፍን አዯት ከትርፏ ኪሳራው ስለሚያመዝን በዱኒያ በሚያኗኑራቸው ምርጥዬ ባህሪ ለአኼራ ሲከስቡ ፣ አኼራን ሲሸምቱበት ስታይ እRድና ሞልቶ ፈሰሰ ትላለህ ። ምን አለ ሁሉም እንደነርሱ አራዳ በሆነ ፣ ያራዳ ልጆች በሙሉ ምን አለበት ለአላህ በዋሉ ፣ ለረሱል ትዕዛዝ ባደሩ ትላለህ ።

ከዱኒያ ሿሿ ጠብቆ በሁለቱም ዓለም እRድናን ይግጠመን አቦ 🫡

አብዱ ረዛቅ
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 2⃣1⃣ #ሸዋል  1⃣4⃣4⃣5⃣
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሱብሀነለዚ ዘየነ ሪጃለ ቢሊሀእ

ወንዶችን በፂም ላሳመረው ጌታ ጥራት ይገባው😅
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።

የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።

በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል። 

መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይን) ከሚሰጥባቸው ከተሞች አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስለመሆኑ ተሰምቷል።

ይህን ተከትሎ የፈተና ቅድመ ዝግጅት ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ሲካሄድ ውሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፤ " የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማው በኦንላይን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።

ለፈተናው ኮምፒዩተሮች፣ ላፕቶፖችና ታብሌቶችን ጨምሮ ሌሎች ግብአቶችን የማሟላት ስራ ተጀምሯል ተብሏል።

የግል ትምህርት ቤቶች ለፈተናው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ከወዲሁ እንዲጀምሩ ጥሪ ቀርቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ማሳወቁ ይታወሳል።

ሙሉ በሙሉ ፈተናው በኦንላይን ባይሰጥም  በተመረጡ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቀሩት ተማሪዎች በተለመደው ሁኔታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በወረቀት ይፈተናሉ።

እስካሁን በየትኞቹ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን ይወስዳሉ የሚለው አይታወቅም። በምን አግባብ ተማሪዎቹ እንደሚመረጡም ለጊዜው በይፋ የሚታወቅ ነገር የለም።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia