TECH ETHIOPIA 🇪🇹
2.8K subscribers
143 photos
1 video
1 file
71 links
Download Telegram
🌻🌼🤲 እንኳን ለ2018 ዓ/ም አዲስ አመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ!!!

መልካም አዲስ ዓመት!!
🤲🌼🌻
👍3❤2
❗️ሁሉም ት/ቤቶች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ማስተማር ይጀምራሉ

በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ከመጪው መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የዘንድሮው ዓመት የመማር ማስተማር ሥራ ይጀመራል።

ለ2018 የትምህርት ዘመን በየደረጃው ለመማር ማስተማር የሚያስፈልጉ ቁሳቁስን ጨምሮ የተለያዩ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ወላጆች፣ መምህራንና የዘርፉ ባለድርሻዎች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ መቅረቡ የሚታወስ ነው።

ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር የሚገኝ ተማሪ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌትና የትኛውንም የትምህርት ሥራ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድርና አዋኪ የሆነ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁስ ይዞ መገኘት ተከልክሏል፡፡

ከነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በመላው ሀገሪቱ የትምህርት ምዝገባ እና ተጓዳኝ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸው ተመላክቷል፡፡

በኢትዮጵያ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ከ7 ሚሊየን በላይ ሕጻናት በተለያዩ ምክንያቶች ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው፡፡

ወላጆች ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ልጅን ወደ ት/ቤት አለመላክ እንደሚያስጠይቅ አውቀው የሚጠበቅባቸው ኃላፊነት እንዲወጡ ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል፡፡
───────────────────
👍4❤3
የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2017 የትምህርት ዘመን የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት በነገው ዕለት ይፋ ይሆናል።

የትምህርት ሚኒስቴር ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው፤ የፈተና ውጤቱን አስመልክቶ በነገው ዕለት ከ10 ሰዓት ጀምሮ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ይሰጣል።

የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ መሰጠቱ ይታወሳል።

በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ በአጠቃላይ 608 ሺህ 742 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ 134 ሺህ 828 ተማሪዎች በበይነ መረብ መፈተናቸው ይታወቃል።

ቀሪዎቹ 473 ሺህ 914 ተማሪዎች ደግሞ በወረቀት ተፈትነዋል።

ፈተናው በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በተቋቋሙ 216 የመፈተኛ ማዕከላት በበይነ መረብ በአራት ዙር እንዲሁም በወረቀት በሁለት ዙር መሰጠቱ የሚታወስ ነው።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
🔥6❤4👏1
ከፍተኛ ተማሪዎችን ያሳለፉ ክልሎች ፦
- አዲስ አበባ፣
- ሐረሪ
- አማራ ክልል ናቸው።

ዘንድሮ " የተፈታኙ ቁጥር ቀንሷል ያለፈው ተማሪ ቁጥር ግን ጨምሯል " ያሉት ትምህርት ሚኒስትሩ ዘንድሮ በአጠቃላይ 48,929 ተማሪዎች ማለፋቸውን ገልጸዋል።

በጾታ ስብጥር ፦
30,451 ወንድ ተማሪዎች አልፈዋል።
18,478 ሴት ተማሪ አልፏል።

አማካይ ውጤት
87 በመቶ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች
86 በመቶ ዓለማቀፍ ትምህርት ቤቶች
5.4 በመቶ የመንግስት ትምህርት ቤቶች
51 በመቶ የግል ትምህርት ቤት ውጤት

https://t.me/amharictutorialclass
👍5❤1🤗1
የ12ኛ ክፍል ውጤት እስከ ዛሬ ቀን 6 ሰዓት ይለቀቃል።

" ምንም የተሳሳተ ነገር እንዳይኖርና áŠĽáˆ­áŒáŒ áŠ› ለመሆን ስለፈለግን የተወሰኑ ልጆች አሉ የተዛባ እሱን አስተካክለን እስከ ነገ ቀን 6:00 ሰዓት የፈተናው ውጤት ይለቀቃል። " - የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ከተፈተኑት አጠቃላይ 585,882 ተማሪዎች ውስጥ 48,920 ወይም 8.4% ከግማሽ በላይ አምጥተው አልፈዋል፣ 536,962 ወይም 91.6% የሚሆኑት ደግሞ አላለፋም።

ለተፈታኞች መልካም ውጤት

Via:
https://t.me/amharictutorialclass
❤5🔥2
🎴Addis Ababa University🎴

መስከረም 5, 2018
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

አንጋፋው  እና ስመጥሩ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስዳችሁ የኢ.ፌ.ዴ.ፊ ትምህርት ሚኒስትር ያስቀመጠውን የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ መስፈርት ላሟላችሁ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል። 
ዩኒቨርሲቲያችን በ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ለመቀበል ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች ከመስከረም 5 እስከ መስከረም 9፣ 2018 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በዩኒቨርሲቲው ፖርታል አማካኝነት መመዝገብ እንደምትችሉ በደስታ እንገልጻለን።

በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና  ቀን፣  ሰዓት እና ማዕከላትን በተመለከተ በዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ መገናኛ ገፆች  እንዲሁም በይፋዊ ድህረገጻችን የምናሳውቀው መሆኑን እንገልፃለን። 

#አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣የተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቤት
# አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይማሩ : ህልሞን ያሳኩ

ለመመዝገብ የመጀመሪያው step 👆👆 account መክፈት ነው ከዛ ከታች ባለው link👇👇 ገብታቹ መመዝገብ

በመሆኑም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች ከመስከረም 05-09/2018 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በዩኒቨርሲቲው ፖርታል (https://portal.aau.edu.et) አማካኝነት መመዝገብ እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡
❤2👍2
ቅሬታዎን ያስገቡ!

በ12ኛ ክፍል ውጤትዎ ላይ ያለዎትን ቅሬታ በኦንላይን በቀጥታ ያስገቡ!

➫ https://result.eaes.et ላይ ይግቡ፣
➫ የአድሚሽን ቁጥርዎን ያስገቡ፣
➫ የመጀመሪያ ስምዎን ያስገቡ፣
➫ ውጤትዎን ይመልከቱ፣
➫ እዛው ገፅ ላይ ወደታች ስክሮል ያድርጉ፣
➫ 'Submit Complaint' የሚለውን ይጫኑ፣
➫ 'My Complaints' የሚለውን ይጫኑ፣
➫ ቅሬታዎን ከማስገባትዎ በፊት ከዚህ በፊት ቅሬታ አስገብተው ከነበረና ምላሽ ከተሰጠዎ ይመልከቱ፣
➫ የተሰጠዎን ምላሽ ይመልከቱ። #EAES
❤1
#ጊዜ
ከዚህ ቀደም በዓለም ላይ ፈጣኑ ሰው ተብሎ ሲሞካሽ የነበረው አፈ ታሪካዊው ሯጭ ኡሴን ቦልት፣ በአሁኑ ጊዜ የ39 ዓመት ጎልማሳ ሲሆን እንደ ደረጃ መውጣት ባሉ ቀላል ነገሮች እየተቸገረ እንደሚገኝ ዘገባዎች ያሳያሉ። በአንድ ወቅት አስደናቂ ፍጥነቱ ዓለምን አስገርሞ የነበረው ይህ የ8 ጊዜ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ፣ የአትሌቲክስ ክብሩ በእርጅና እና በደረሱበት ጉዳቶች ሳቢያ እየደበዘዘ መጥቷል። በመላው ዓለም የሚገኙ አድናቂዎቹ የቦልትን አስደናቂ ታሪክ በማሰብ፣ ሪከርዶች ሊደበዝዙና ሰውነት ሊለወጥ ቢችልም፣ የቦልት የመብረቅ ፍጥነት ታሪክ ግን በዘለቄታው እንደሚያንጸባርቅ ያስታውሳሉ።


❇️ https://t.me/amharictutorialclass ❇️
👍2
ከስልክ ታሪክ አስገራሚ መረጃ! በዓለም ላይ በብዛት የተሸጠው የሞባይል ስልክ አይፎን ወይም ሳምሰንግ ጋላክሲ ሳይሆን፣ ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ ታዋቂነትን ያተረፈው ኖኪያ 1100 ነው።
ይህ ጠንካራና ቅንጡ ያልሆነ ሞባይል በዓለም ዙሪያ ከ250 ሚሊዮን በላይ ተሽጧል። ዘላቂነትንና ቀላልነትን ታሳቢ አድርጎ የተሰራው ኖኪያ 1100፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ባትሪው፣ አቧራ የማያስገባ የቁልፍ ሰሌዳውና የእጅ ባትሪ (ፋና) መብራቱ በአደጉ አገራት ሳይቀር ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል።
ይህ ስልክ በብዙ ቁጥር መሸጡ የብዙ ገፅታዎች ወይም ውስብስብ ነገሮች መኖር ከቀላልነትና ጠቃሚነት ያነሰ ዋጋ ይሰጠው እንደነበር ያሳያል። ይህ ደግሞ ኖኪያ 1100 በሞባይል ኢንደስትሪ ውስጥ እውነተኛ አፈ ታሪክ ሆኖ እንዲቀመጥ አድርጎታል።
❇️ https://t.me/amharictutorialclass ❇️
👍3
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ አገልግሎት ይቋረጣል- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
*
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ መስከረም 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እስከ ለሊቱ 9፡30 ሰዓት ድረስ ከሲቢኢ ብር አገልግሎቶች በስተቀር ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች አገልግሎት ማለትም
 የሞባይል ባንኪንግ
 ኢንተርኔት ባንኪንግ
 ኤቲኤም ማሽኖች
 የፖስ ማሽኖች እና በኮር ባንኪንግ የሚሰጡ አገልግሎቶች (Core Banking Services)
በጊዜያዊነት እንደሚቋረጡ ባንኩ አስታውቋል።


❇️https://t.me/amharictutorialclass❇️
❤2👍1
የ15 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ-አሜሪካዊው ሄማን በቀለ፣ የ TIME መጽሔት የ2024 የዓመቱ ህፃን ተብሎ ተመርጧል።
ይህ እውቅና ያገኘው የቆዳ ካንሰርን ለማከም የሚረዳ ልዩ ሳሙና በመፍጠሩ ነው። ሳሙናው ኢሚኩይሞድ የተባለውን መድኃኒት በቅባታማ ናኖፓርቲክል ውስጥ በማስቀመጥ የፈጠራ ስራውን ሰርቷል። ይህ ደግሞ መድኃኒቱ ከታጠበ በኋላም በቆዳ ላይ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ ያደርገዋል።
እ.ኤ.አ. በ2023 የ 3M Young Scientist Challenge ውድድርን ያሸነፈው ይህ ፕሮጀክት፣ በአሁኑ ጊዜ በመጀመሪያ ደረጃ የሙከራ ሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን በአይጦች ላይም ጥናቶች እየተደረጉ ነው። ተጨማሪ ምርምር፣ የባለቤትነት መብት (ፓተንት) እና ፈቃዶች የሚያስፈልጉ ቢሆንም፣ ባለሙያዎች ዝቅተኛ ወጪ ባለው እና በቀላሉ ተደራሽ በሆነው በዚህ ሃሳቡ ላይ ትልቅ እምቅ ችሎታ እንዳለው ይናገራሉ።
❇️ https://t.me/amharictutorialclass ✅
❤4🤗1
በጣም ትልቅ በሆነ የበጎ አድራጊነት ተግባር፣ ቢል ጌትስ 52 ቢሊዮን ዶላር በመለገሱ ከዓለማችን 10 እጅግ ሀብታም ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ወጥቷል። በብሉምበርግ ቢሊየነሮች ዝርዝር መሠረት፣ ጌትስ አሁን በ12ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ የልግስና ተግባሩ ላይ ያለውን ከፍተኛ ተጽእኖ ያሳያል።
​የማይክሮሶፍት ተባባሪ መስራች የሆነው ቢል ጌትስ፣ በቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በኩል በአለም አቀፍ የጤና፣ የትምህርት እና የአየር ንብረት ተነሳሽነት ፕሮጀክቶች ላይ ላደረገው ቁርጠኝነት ይታወቃል። ይህ የቅርብ ጊዜ ልገሳ የዓለምን በጣም አንገብጋቢ ችግሮችን ለመፍታት ሀብቱን ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት ያጠናክራል።
​ብዙዎች የጌትስን ልግስና የሚያወድሱ ቢሆንም፣ ይህ እርምጃ የሀብት ክፍፍል፣ የበጎ አድራጎት እና የቢሊየነሮች በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ተጽእኖ በተመለከተ ውይይቶችን እያነሳ ነው። ጌትስ ራሱ ለዘለቄታው ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት አብዛኛውን ሀብቱን ለመለገስ እንደሚፈልግ ደጋግሞ ገልጿል።

❇️ https://t.me/amharictutorialclass ✅
❤3👍1
🐀 አይጥ የኤቲኤም ማሽን ሰብሮ በመግባት 19,000 ዶላር የሚገመት ገንዘብ በላ
እ.ኤ.አ. በ2016 በሰሜን ምስራቅ ሕንድ፣ ቲንሱኪያ ከተማ ውስጥ አንድ ተንኮለኛ አይጥ የሕንድ ስቴት ባንክ ኤቲኤም ማሽን ውስጥ ትንሽ የኬብል ቀዳዳ አግኝቶ ይገባል።
የተበላሸውን ማሽን ለመጠገን የመጡት የቴክኒክ ባለሙያዎች ባዩት ነገር ደነገጡ፡ በአይጡ በመበላት ወደ አመድነት የተቀየረ ከ1.3 ሚሊዮን ሩፒ (በወቅቱ ከ19,000 ዶላር በላይ) የሚሆን በገንዘብ መካከል የሞተ አይጥ ጎጆ ሰርቶ ተቀምጦ ነበር።
ይህ ክስተት በጣም ጥብቅ ጥበቃ ባላቸው የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎች ላይ እንኳን የሚከሰቱ ያልተጠበቁ ድክመቶችን ያሳያል።

❇️ https://t.me/amharictutorialclass ✅
❤1
ማስታወቂያ

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፡-

1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

2.አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።

#MOE
❤3👍2