ኤልሮኢ:
ጥር 26/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር ተወልደ ኢየሱስ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 1÷1_12
ን/ዲ 1ጴጥ 1÷13_22
ን/ካ ግብ፡ሐዋ10÷1_11
#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ 47፥8
በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ
በሀገረ እግዚአ ኃያላን በሀገረ አምላክነ
እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም::
#ትርጉም፦
እንደሰማን እንዲሁ አየን
በሠራዊት ጌታ ከተማ በአምላካችን ሀገር
እግዚአብሔር ለዓለም አጸናት
#የዕለቱ ወንጌል፦ ሉቃ 2፥36 - ፍጻሜ
ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ጥር 26/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር ተወልደ ኢየሱስ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 1÷1_12
ን/ዲ 1ጴጥ 1÷13_22
ን/ካ ግብ፡ሐዋ10÷1_11
#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ 47፥8
በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ
በሀገረ እግዚአ ኃያላን በሀገረ አምላክነ
እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም::
#ትርጉም፦
እንደሰማን እንዲሁ አየን
በሠራዊት ጌታ ከተማ በአምላካችን ሀገር
እግዚአብሔር ለዓለም አጸናት
#የዕለቱ ወንጌል፦ ሉቃ 2፥36 - ፍጻሜ
ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ኤልሮኢ፡
…… ✍ አትማረኝ
--------------
በጣና ገዳማት ውስጥ የአቡነ አሳይ ዋሻ አለ በዚህ ዋሻ አንድ ያልተማረ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የማያውቅ ሰው ጸሎት ሲጸልይ አንድ አባት በጀልባ ተሳፍረው ይመጡና ያገኙታል።
ወደ ደሴቷም አረፍ ልበል ብለው ሲገቡ ያ ወጣት ሲጸልይ ይሰሙታል ቀረብ ብለው ቢያደምጡ ይህ ሰው የሚጸልየው "አትማረኝ" እያለ ነው።
እኝህ አባት በጣም ይደነግጡና እንዲህ ያለ ጸሎት አለ ወይ አትማረኝ የሚል ማን ነው ያስተማረህ ሲሉት አንድ መነኩሴ ነው ያስተማሩኝ አላቸው።
እሳቸውም ይህማ ሰይጣን ነው በመነኩሴ ተመስሎ ያስተማረህ እንጂ አትማረኝ ብሎ ጸሎት የለም ብለው "አቡነ ዘበሰማያትን" አስተማሩት። ይኽ ሰው እንደምንም ታግሎ አባታችን ሆይን ከተማረ በኋላ እኝህን አባት ያሰናብታቸዋል።
እሳቸውም በጀልባ ተሳፍረው መንገድ ሲጀምሩ ይኽ ወጣት ወደ ቀደመ በዓቱ ገብቶ መጸለይ ሲጀምር ያን ጸሎት ረሳው። ምን ነበር ያስተማሩኝ ብሎ ቢያስብ ጠፋበት። ከበዓቱም ሮጦ ወጥቶ በጀልባ ተሳፍረው የሚሄዱትን አባት አስቁሞ "ምን ብለው ነው ያስተምሩኝ?" ብሎ ጠየቃቸው እኝህም አባት ሲያዩት ውሃ ላይ ቆሟል፣ በውሃ ላይ ነው ሮጦ የመጣው አትኩረው ቢመለከቱት ውኃው ላይ እንደቆመ ነው።
"በል የእኔ ልጅ እንደቀድሞው አትማረኝ እያልክ ጸልይ" አሉት ይባላል።
ወጣቱ ባለማወቅ በሚጸልየው ጸሎት ውስጥ በቅቶ ነበር። እግዚአብሔር የሰማው ያለውን ሳይሆን የልቦናውን ነው።
የምንጸልየው ጸሎት የተዘበራረቀ ቢሆንም እንኳን እግዚአብሔር እያቃና ይሰማዋል። ስለዚህም ከመጸለይ ወደ ኋላ አንበል እኛ የምንጸልየው ባይገባንም በዙሪያችን ያሉት አጋንንቶች ገብቷቸው ይሸሻሉ።
@aleroe
…… ✍ አትማረኝ
--------------
በጣና ገዳማት ውስጥ የአቡነ አሳይ ዋሻ አለ በዚህ ዋሻ አንድ ያልተማረ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የማያውቅ ሰው ጸሎት ሲጸልይ አንድ አባት በጀልባ ተሳፍረው ይመጡና ያገኙታል።
ወደ ደሴቷም አረፍ ልበል ብለው ሲገቡ ያ ወጣት ሲጸልይ ይሰሙታል ቀረብ ብለው ቢያደምጡ ይህ ሰው የሚጸልየው "አትማረኝ" እያለ ነው።
እኝህ አባት በጣም ይደነግጡና እንዲህ ያለ ጸሎት አለ ወይ አትማረኝ የሚል ማን ነው ያስተማረህ ሲሉት አንድ መነኩሴ ነው ያስተማሩኝ አላቸው።
እሳቸውም ይህማ ሰይጣን ነው በመነኩሴ ተመስሎ ያስተማረህ እንጂ አትማረኝ ብሎ ጸሎት የለም ብለው "አቡነ ዘበሰማያትን" አስተማሩት። ይኽ ሰው እንደምንም ታግሎ አባታችን ሆይን ከተማረ በኋላ እኝህን አባት ያሰናብታቸዋል።
እሳቸውም በጀልባ ተሳፍረው መንገድ ሲጀምሩ ይኽ ወጣት ወደ ቀደመ በዓቱ ገብቶ መጸለይ ሲጀምር ያን ጸሎት ረሳው። ምን ነበር ያስተማሩኝ ብሎ ቢያስብ ጠፋበት። ከበዓቱም ሮጦ ወጥቶ በጀልባ ተሳፍረው የሚሄዱትን አባት አስቁሞ "ምን ብለው ነው ያስተምሩኝ?" ብሎ ጠየቃቸው እኝህም አባት ሲያዩት ውሃ ላይ ቆሟል፣ በውሃ ላይ ነው ሮጦ የመጣው አትኩረው ቢመለከቱት ውኃው ላይ እንደቆመ ነው።
"በል የእኔ ልጅ እንደቀድሞው አትማረኝ እያልክ ጸልይ" አሉት ይባላል።
ወጣቱ ባለማወቅ በሚጸልየው ጸሎት ውስጥ በቅቶ ነበር። እግዚአብሔር የሰማው ያለውን ሳይሆን የልቦናውን ነው።
የምንጸልየው ጸሎት የተዘበራረቀ ቢሆንም እንኳን እግዚአብሔር እያቃና ይሰማዋል። ስለዚህም ከመጸለይ ወደ ኋላ አንበል እኛ የምንጸልየው ባይገባንም በዙሪያችን ያሉት አጋንንቶች ገብቷቸው ይሸሻሉ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
……✍
በዓለም መደሰት ወደ እግዚአብሔር ሊመራችሁ አይችልም ከእርሱ ያርቃችኋል እንጂ። የዓለም ፍቅር ወደ ልባችሁ ከገባም አሳቦቻችሁና አመለካከቶቻችሁ መናጋት ይጀምራሉ ።
በዚህ ጊዜ እናንተ ተስማሚ ነው ብላችሁ ያመናችሁበትን አመለካከት እንዲህ እያላችሁ መጠየቅ ትጀምራላችሁ ፦ ይህንንና ያንን ማድረግ ስሕተቱ ምንድር ነው? እንዲህ ባለው ነገር ብደሰት ኃጢአቱ ወይም ጉዳቱ ምንድር ነው? ከዚህ በኋላ በመመርያዎችና በዋጋቸው የሚደረገው ሰንሰለታማ ክርክር ይጀምራል! ! ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ክርክሮችና ሙግቶች ምክንያት የሚሆነው ለእግዚአብሔር ያላችሁ ፍቅር መቀነስ ነው ።
ስለዚህ ልባችሁን በዓለም ፍላጎቶች ወይም ምኞቶች ውስጥ አታስቀምጡ ደጁ ሰፊ ከሆነ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አትችሉምና [ማቴ 7÷13]
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
@aleroe
……✍
በዓለም መደሰት ወደ እግዚአብሔር ሊመራችሁ አይችልም ከእርሱ ያርቃችኋል እንጂ። የዓለም ፍቅር ወደ ልባችሁ ከገባም አሳቦቻችሁና አመለካከቶቻችሁ መናጋት ይጀምራሉ ።
በዚህ ጊዜ እናንተ ተስማሚ ነው ብላችሁ ያመናችሁበትን አመለካከት እንዲህ እያላችሁ መጠየቅ ትጀምራላችሁ ፦ ይህንንና ያንን ማድረግ ስሕተቱ ምንድር ነው? እንዲህ ባለው ነገር ብደሰት ኃጢአቱ ወይም ጉዳቱ ምንድር ነው? ከዚህ በኋላ በመመርያዎችና በዋጋቸው የሚደረገው ሰንሰለታማ ክርክር ይጀምራል! ! ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ክርክሮችና ሙግቶች ምክንያት የሚሆነው ለእግዚአብሔር ያላችሁ ፍቅር መቀነስ ነው ።
ስለዚህ ልባችሁን በዓለም ፍላጎቶች ወይም ምኞቶች ውስጥ አታስቀምጡ ደጁ ሰፊ ከሆነ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አትችሉምና [ማቴ 7÷13]
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
@aleroe
ኤልሮኢ:
እናመስግነው
እናመስግነው በአንድነት
ቸርነቱ ለማያልቅበት/2/
አዝ.............
የሰማዩን አምላክ እናመስግነው
ህይወቱን ለሠጠን እናመስግነው
እናመስግን ጌታን እናመስግነው
በአንድነት ሆነን እናመስግነው
ለኛ ያደረገው እናመስግነው
ከቶ እያልቅምና እናመስግነው
አማኑኤል ቸር ነው እናመስግነው
ይድረሰው ምስጋና እናመስግነው
ድንግል ማርያም ስጦታ ናት
በምልጃዋ ለሚማፀናት/2/
አዝ.........
ስሞን ለሚጠሩ ለሚማፀናት
በፍቅሯ ተስበው ለሚማፀናት
ምህረት ያገኛሉ ለሚማፀናት
ወደሶ ተማፅነው ለሚማፀናት
እሩሩ ናትና ለሚማፀናት
ለሚለምናት ለሚማፀናት
ተክለሀይማኖ ሀዋርያ
ፀለየላት ለኢትዬጽያ/2/
አዝ...........
ኢትዬጽያዊው ብርሀን ተክለሀይማኖት
ታላቁ መምህር ተክለሀይማኖት
ቢነገር አያልቅን ተክለሀይማኖት
የተሰጠህ ክብር ተክለሀይማኖት
የተጋህ በፀሎት ተክለሀይማኖት
በ1 እግርህ ቆመህ ተክለሀይማኖት
አባቴ ተክልዬ ተክለሀይማኖት
ልዩነው ፀጋህ ተክለሀይማኖት
ገብረመንፈስ ቅዱስ አባታችን
በረከትህ ይግባ ቤታችን/2/
አዥ.........
የአምላክ ባለሞል ግባ ቤታችን
በፅድቅ ያበራህ ግባ ቤታችን
ቃልኪዳንህ ፀንቶል ግባ ቤታችን
ለተማፀኑህ ግባ ቤታችን
ህይወትህ አብነት ግባ ቤታችን
ሆኖታል ትውልዱ ግባ ቤታችን
በኪዳንህ ያርፋል ግባ ቤታችን
ያለው በመንገዱ ግባ ቤታችን
የልዳው ሠማእት ጊዮርጊስ
ልትባርከን ና በፈረስ/2/
አዝ..........
የእውነት ተጋዳይ ና በፈረስ
የአምላክ ምስክር ና በፈረስ
3 ጊዜ ሞተህ ና በፈረስ
የተሰጠህ ክብር ና በፈረስ
መከራን የታገስክ ና በፈረስ
ለስጋ ሳትሳሳ ና በፈረስ
አድነን ጊዮርጊስ ና በፈረስ
ከዓለም አበሣ ና በፈረስ
የቤሩቱ ኮከብ ጊዮርጊስ
ልትባርከን ና በፈረስ/2/
💚 @aleroe 💚
እናመስግነው
እናመስግነው በአንድነት
ቸርነቱ ለማያልቅበት/2/
አዝ.............
የሰማዩን አምላክ እናመስግነው
ህይወቱን ለሠጠን እናመስግነው
እናመስግን ጌታን እናመስግነው
በአንድነት ሆነን እናመስግነው
ለኛ ያደረገው እናመስግነው
ከቶ እያልቅምና እናመስግነው
አማኑኤል ቸር ነው እናመስግነው
ይድረሰው ምስጋና እናመስግነው
ድንግል ማርያም ስጦታ ናት
በምልጃዋ ለሚማፀናት/2/
አዝ.........
ስሞን ለሚጠሩ ለሚማፀናት
በፍቅሯ ተስበው ለሚማፀናት
ምህረት ያገኛሉ ለሚማፀናት
ወደሶ ተማፅነው ለሚማፀናት
እሩሩ ናትና ለሚማፀናት
ለሚለምናት ለሚማፀናት
ተክለሀይማኖ ሀዋርያ
ፀለየላት ለኢትዬጽያ/2/
አዝ...........
ኢትዬጽያዊው ብርሀን ተክለሀይማኖት
ታላቁ መምህር ተክለሀይማኖት
ቢነገር አያልቅን ተክለሀይማኖት
የተሰጠህ ክብር ተክለሀይማኖት
የተጋህ በፀሎት ተክለሀይማኖት
በ1 እግርህ ቆመህ ተክለሀይማኖት
አባቴ ተክልዬ ተክለሀይማኖት
ልዩነው ፀጋህ ተክለሀይማኖት
ገብረመንፈስ ቅዱስ አባታችን
በረከትህ ይግባ ቤታችን/2/
አዥ.........
የአምላክ ባለሞል ግባ ቤታችን
በፅድቅ ያበራህ ግባ ቤታችን
ቃልኪዳንህ ፀንቶል ግባ ቤታችን
ለተማፀኑህ ግባ ቤታችን
ህይወትህ አብነት ግባ ቤታችን
ሆኖታል ትውልዱ ግባ ቤታችን
በኪዳንህ ያርፋል ግባ ቤታችን
ያለው በመንገዱ ግባ ቤታችን
የልዳው ሠማእት ጊዮርጊስ
ልትባርከን ና በፈረስ/2/
አዝ..........
የእውነት ተጋዳይ ና በፈረስ
የአምላክ ምስክር ና በፈረስ
3 ጊዜ ሞተህ ና በፈረስ
የተሰጠህ ክብር ና በፈረስ
መከራን የታገስክ ና በፈረስ
ለስጋ ሳትሳሳ ና በፈረስ
አድነን ጊዮርጊስ ና በፈረስ
ከዓለም አበሣ ና በፈረስ
የቤሩቱ ኮከብ ጊዮርጊስ
ልትባርከን ና በፈረስ/2/
💚 @aleroe 💚
ኤልሮኢ:(ምክረ አበው)
……✍
አባት ልጁ ከቤት ወጥቶ መኪና እንዳይገጭበት፣ ወድቆ እንዳይሰበርበት፣ ድንገት በአከባቢው የሚያልፉ ከብቶች ገፍተው እንዳይጥሉበት መውጫው በሩን ይዘጋበታል፡፡ ይኼኔ ልጁ በሩ ለምን እንደተዘጋበት አያውቅም፤ ልጅ ነውና፡፡ አባቱ የጠላው መስሎትም ምርር ብሎ ሊያለቅስ
ይችላል፡፡ ማልቀስ ብቻ አይደለም፤ ቂምም ሊይዝበት ይችላል፡፡ አባቱ ግን በሩን የዘጋበት ምክንያት ያውቃል፤ ጠልቶት ሳይሆን ይጐዳበታልና ልጁ ቢያለቅስም አይከፍትለትም፡፡
እውነተኛው አባታችን እግዚአብሔርም አንዳንድ ጊዜ የማይጠቅሙን ይልቁንም ክፉኛ ሊጎዱን የሚችሉ በሮችን ይዘጋብናል፡፡ ከእውቀት ከፍለን የምናውቅ ልጆቹ ነንና አባታችን ለምን እንደዘጋብን ለጊዜው አይታወቀንም፤ ብቻ የከለከለን ይመስለናል፡፡ በመሆኑም ቂም ልንይዝበት ልናማርረውም እንችላለን፡፡ እርሱ ግን ይታገሠናል፤ ለእኛ
የሚያስባት መልካሚቱን በር እርሱ ያውቃታልና ይከፍትልናል፤ በእኛ እይታ መልካም የምትመስለንን ነገር ግን ክፉይቱን በር ይዘጋብናል፡፡
ቅዱስ አባት ሆይ ስለ ከፈትክልን ብቻ ሳይሆን ስለ ዘጋህብንም በር እናመሰግንሃለን ልንለው ይገባል። አሜን!
@aleroe
……✍
አባት ልጁ ከቤት ወጥቶ መኪና እንዳይገጭበት፣ ወድቆ እንዳይሰበርበት፣ ድንገት በአከባቢው የሚያልፉ ከብቶች ገፍተው እንዳይጥሉበት መውጫው በሩን ይዘጋበታል፡፡ ይኼኔ ልጁ በሩ ለምን እንደተዘጋበት አያውቅም፤ ልጅ ነውና፡፡ አባቱ የጠላው መስሎትም ምርር ብሎ ሊያለቅስ
ይችላል፡፡ ማልቀስ ብቻ አይደለም፤ ቂምም ሊይዝበት ይችላል፡፡ አባቱ ግን በሩን የዘጋበት ምክንያት ያውቃል፤ ጠልቶት ሳይሆን ይጐዳበታልና ልጁ ቢያለቅስም አይከፍትለትም፡፡
እውነተኛው አባታችን እግዚአብሔርም አንዳንድ ጊዜ የማይጠቅሙን ይልቁንም ክፉኛ ሊጎዱን የሚችሉ በሮችን ይዘጋብናል፡፡ ከእውቀት ከፍለን የምናውቅ ልጆቹ ነንና አባታችን ለምን እንደዘጋብን ለጊዜው አይታወቀንም፤ ብቻ የከለከለን ይመስለናል፡፡ በመሆኑም ቂም ልንይዝበት ልናማርረውም እንችላለን፡፡ እርሱ ግን ይታገሠናል፤ ለእኛ
የሚያስባት መልካሚቱን በር እርሱ ያውቃታልና ይከፍትልናል፤ በእኛ እይታ መልካም የምትመስለንን ነገር ግን ክፉይቱን በር ይዘጋብናል፡፡
ቅዱስ አባት ሆይ ስለ ከፈትክልን ብቻ ሳይሆን ስለ ዘጋህብንም በር እናመሰግንሃለን ልንለው ይገባል። አሜን!
@aleroe
ኤልሮኢ፡(ስነ ፅሁፍ)
✍…አንድ አካል
ጳውሎስ እግር ሆኖ በአህዛብ ሀገር፣
ሲሮጥ አይተነዋል ለቃል ሲመሰክር።
እጅ ነበር ጴጥሮስ ሁሉን የሚባርክ፣
ሶስት ሺህ ሰራዊት በአንዴ የሚማርክ።
የዮሀንስ ዓይን ከሩቅ የሚያስተውል፣
ፍጢሙ ላይ ቆሞ ሰማይ የሚያካልል።
ሉቃስም ጣቱ ነው ቃል የሚፃፍበት፣
የፈጣሪው እናት መልኳ የሚሳልበት።
አንደበተ ትሁት ያዕቆብ መምህር፣
ባለፀጋዎቹን ሲወቅስ የማያፍር።
ማቴዎስም መጥቷል ከቀራጭነቱ፣
የፈጣሪ አካል ሆኗል ሰውነቱ።
ቅዱስ ፊሊጶስም እውነተኛ አባት ነህ፣
ታሪክህ ይታወቅ በእኛ በልጆችህ፣
ለህዝበ ኢትዮጵያም ይድረስ በረከትህ።
@aleroe
✍…አንድ አካል
ጳውሎስ እግር ሆኖ በአህዛብ ሀገር፣
ሲሮጥ አይተነዋል ለቃል ሲመሰክር።
እጅ ነበር ጴጥሮስ ሁሉን የሚባርክ፣
ሶስት ሺህ ሰራዊት በአንዴ የሚማርክ።
የዮሀንስ ዓይን ከሩቅ የሚያስተውል፣
ፍጢሙ ላይ ቆሞ ሰማይ የሚያካልል።
ሉቃስም ጣቱ ነው ቃል የሚፃፍበት፣
የፈጣሪው እናት መልኳ የሚሳልበት።
አንደበተ ትሁት ያዕቆብ መምህር፣
ባለፀጋዎቹን ሲወቅስ የማያፍር።
ማቴዎስም መጥቷል ከቀራጭነቱ፣
የፈጣሪ አካል ሆኗል ሰውነቱ።
ቅዱስ ፊሊጶስም እውነተኛ አባት ነህ፣
ታሪክህ ይታወቅ በእኛ በልጆችህ፣
ለህዝበ ኢትዮጵያም ይድረስ በረከትህ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ"
ከእለታት አንድ ቀን አንድ ወጣት የንስሀ አባቱን ለማግኘት ተንስቶ ወደ ቤተክርስቲያን ይሄዳል። ፀሎቱን አድርሶ ግቢ ውስጥ ቁጭ እንዳለ አባ ይመጡና በመስቀል ባርከው ደባብሰው ወደ በአታቸው ይዘውት ይገባሉ። ታድያ ልክ እንደ ገባ የክርስቶስን ስነ ስቅለት የእሾሁን አክሊል ያይና በሀሳብ ወደ ቀራንዮ ይሄዳል። አባ ምነው ልጄ እኔን እዚህ ትተህ አንተ ወደ ቀራንዮ ሄድክ ሲሉት ከሀሳቡ ባህር ወጥቶ ቁጭ አለ።
አባ አየህ ልጄ ምን ሆነ መሰለህ ብለው ጨዋታ ጀመሩለት። "በአንድ ሀገር ትልቅ የባቡር መንገድ ነበር ታድያ የባቡሩ መንገድ ታቹ ባህር ነው በጣም ትላልቅ አዞዎች አሉበት። አንድ ቀን ታድያ ይህ መንገድ ኃይለኛ ዝናብ በመጣሉ ምክንያት ይፈርሳል። አንድ ህፃን ልጅ ይህን ሁኔታ አይቶ ኖሯል ባቡሩ እዛ ቦታ ሳይደርስ ለማስቆም ወሰነና የአደጋ ምልክቶችን ፅፎ በተለያየ ርቀት 2 ቦታዎች ላይ አስቀመጠ። ከዚያም 3ኛው ላይ ባንዲራ ይዞ እራሱ ቆመ ባቡሩም መጣ ልክ የመጀመሪያውን የአደጋ ምልክት ሲያይ ይህ የዱርዬዋች ስራ ነው ብሎ ተበሳጭቶ አለፈ። ሁለተኛውንም እንዲሁ አለፈ። በሶስተኛው ህፃኑ ጋር ደረሰ ጥሩንባውን እያጮኸ ዘወር በል አለው ልጁ ግን በጭራሽ ዘወር ሳይል ባቡሩ እዛው ፈጨው የባቡሩ አሽከርካሪ በጣም ደነገጠ ተሳፋሪዎችም ወረዱ ልጁን ሲያዩት የለም ደቋል። ነገር ግን በእጁ የነበረው ወረቀትና ባንዲራ ወድቆ አገኙት አንስተው ሲያነቡት በዝናቡ ምክንያት ድልድዩ መፍረሱን ነበር የሚያሳየው። እውነትም ጠጋ ብለው ሲያዩ ድልድዩ ፈርሶ አዞዎቹ ብቅ ብቅ ብለው መልአከ ሞት የሚጥልላቻውን ነፍስ የሚጠብቁ ነበር የሚመስሉት። ከዛ ሁሉም በጣም አዘኑ አለቀሱ ለእነርሱ መትረፍ ያ ህፃን ልጅ የከፈለውን መስዋዕትነት ተገነዘቡ አንዱ ስለ ሁላቸው ሞቶ እነርሱን አተረፈ። ይህ ሁሉ ስለ ሰዎች ፍቅር ነው።"
አየህ ልጄ ክርስቶስም ለኛ እንዲህ ነው አሉት ሳያውቁ ሁለቱም በጣም አልቅሰው ነበር በልጁ ታሪክ። "አባቴ እኔ'ኮ ከንቱ ሰው ነኝ እግዚአብሔር እኔን ይቅር ይለኛል?" አላቸው "ልጄ እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነው። ግን መጀመሪያ አንተ ቀዶ ጥገና ያልስፈልግሃል" አሉት። "ምን አይነት ቀዶ ጥገና አባቴ?" "ይሄውልህ ልጄ የእስከ አሁኑን ልብህን ልናክመው ይገባል ዳግመኛ ወደ ቀደሞው መጥፎና ኃጢአት የበዛበት ህይወት እንዳትመለስ። ከዚያ ንስሀ የሚባለውን የህይወት መድኃኒት ትወስድና ትድናለህ" አሉት፡፡ ወጣቱም ሁሉን ተናዞ ንስሀ ገብቶ ተፀፅቶ ትላንትን ዳግም ላያየት ከእውነት ጋር ታርቆ ጤናማ ህይውቱን መኖር ጀመረ።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe
"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ"
ከእለታት አንድ ቀን አንድ ወጣት የንስሀ አባቱን ለማግኘት ተንስቶ ወደ ቤተክርስቲያን ይሄዳል። ፀሎቱን አድርሶ ግቢ ውስጥ ቁጭ እንዳለ አባ ይመጡና በመስቀል ባርከው ደባብሰው ወደ በአታቸው ይዘውት ይገባሉ። ታድያ ልክ እንደ ገባ የክርስቶስን ስነ ስቅለት የእሾሁን አክሊል ያይና በሀሳብ ወደ ቀራንዮ ይሄዳል። አባ ምነው ልጄ እኔን እዚህ ትተህ አንተ ወደ ቀራንዮ ሄድክ ሲሉት ከሀሳቡ ባህር ወጥቶ ቁጭ አለ።
አባ አየህ ልጄ ምን ሆነ መሰለህ ብለው ጨዋታ ጀመሩለት። "በአንድ ሀገር ትልቅ የባቡር መንገድ ነበር ታድያ የባቡሩ መንገድ ታቹ ባህር ነው በጣም ትላልቅ አዞዎች አሉበት። አንድ ቀን ታድያ ይህ መንገድ ኃይለኛ ዝናብ በመጣሉ ምክንያት ይፈርሳል። አንድ ህፃን ልጅ ይህን ሁኔታ አይቶ ኖሯል ባቡሩ እዛ ቦታ ሳይደርስ ለማስቆም ወሰነና የአደጋ ምልክቶችን ፅፎ በተለያየ ርቀት 2 ቦታዎች ላይ አስቀመጠ። ከዚያም 3ኛው ላይ ባንዲራ ይዞ እራሱ ቆመ ባቡሩም መጣ ልክ የመጀመሪያውን የአደጋ ምልክት ሲያይ ይህ የዱርዬዋች ስራ ነው ብሎ ተበሳጭቶ አለፈ። ሁለተኛውንም እንዲሁ አለፈ። በሶስተኛው ህፃኑ ጋር ደረሰ ጥሩንባውን እያጮኸ ዘወር በል አለው ልጁ ግን በጭራሽ ዘወር ሳይል ባቡሩ እዛው ፈጨው የባቡሩ አሽከርካሪ በጣም ደነገጠ ተሳፋሪዎችም ወረዱ ልጁን ሲያዩት የለም ደቋል። ነገር ግን በእጁ የነበረው ወረቀትና ባንዲራ ወድቆ አገኙት አንስተው ሲያነቡት በዝናቡ ምክንያት ድልድዩ መፍረሱን ነበር የሚያሳየው። እውነትም ጠጋ ብለው ሲያዩ ድልድዩ ፈርሶ አዞዎቹ ብቅ ብቅ ብለው መልአከ ሞት የሚጥልላቻውን ነፍስ የሚጠብቁ ነበር የሚመስሉት። ከዛ ሁሉም በጣም አዘኑ አለቀሱ ለእነርሱ መትረፍ ያ ህፃን ልጅ የከፈለውን መስዋዕትነት ተገነዘቡ አንዱ ስለ ሁላቸው ሞቶ እነርሱን አተረፈ። ይህ ሁሉ ስለ ሰዎች ፍቅር ነው።"
አየህ ልጄ ክርስቶስም ለኛ እንዲህ ነው አሉት ሳያውቁ ሁለቱም በጣም አልቅሰው ነበር በልጁ ታሪክ። "አባቴ እኔ'ኮ ከንቱ ሰው ነኝ እግዚአብሔር እኔን ይቅር ይለኛል?" አላቸው "ልጄ እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነው። ግን መጀመሪያ አንተ ቀዶ ጥገና ያልስፈልግሃል" አሉት። "ምን አይነት ቀዶ ጥገና አባቴ?" "ይሄውልህ ልጄ የእስከ አሁኑን ልብህን ልናክመው ይገባል ዳግመኛ ወደ ቀደሞው መጥፎና ኃጢአት የበዛበት ህይወት እንዳትመለስ። ከዚያ ንስሀ የሚባለውን የህይወት መድኃኒት ትወስድና ትድናለህ" አሉት፡፡ ወጣቱም ሁሉን ተናዞ ንስሀ ገብቶ ተፀፅቶ ትላንትን ዳግም ላያየት ከእውነት ጋር ታርቆ ጤናማ ህይውቱን መኖር ጀመረ።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe
ኤልሮኢ:
✞ #ኪዳነ_ምህረት_እመቤት ✞
ኪዳነ ምህረት እመቤት/2/
ነይልን /2/ ካለንበት
ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪሽ/2/
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ/2/
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላሽ/2/
ከፀጥታ ወደብ ከፍቅር አውድማ/2/
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዓሊለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ/2/
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ/2/
ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይውረድ ከሰማያት/2/
ዕንባችን ይታበስ በአንቺ አማላጅነት
የፅዮን ዝማሬ ተሞላ ነፍሳችን/2/
ነዪ/3/ እንበል እነደ አባቶቻችን/2/
ፍጥረታት ሊድኑ በአማላጅነትሽ/2/
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሸ
ትውልድ ይህን አምኖ ብፅዕት ይልሻል/2/
እናቴ መመኪያዬ ምርኩዜ ሆነሻል/2/
የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም/2/
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሻለሽ/2/
ከሐዘን ከመከራ ታሳርፊዋለሽ/2/
@aleroe
✞ #ኪዳነ_ምህረት_እመቤት ✞
ኪዳነ ምህረት እመቤት/2/
ነይልን /2/ ካለንበት
ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪሽ/2/
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ/2/
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላሽ/2/
ከፀጥታ ወደብ ከፍቅር አውድማ/2/
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዓሊለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ/2/
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ/2/
ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይውረድ ከሰማያት/2/
ዕንባችን ይታበስ በአንቺ አማላጅነት
የፅዮን ዝማሬ ተሞላ ነፍሳችን/2/
ነዪ/3/ እንበል እነደ አባቶቻችን/2/
ፍጥረታት ሊድኑ በአማላጅነትሽ/2/
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሸ
ትውልድ ይህን አምኖ ብፅዕት ይልሻል/2/
እናቴ መመኪያዬ ምርኩዜ ሆነሻል/2/
የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም/2/
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሻለሽ/2/
ከሐዘን ከመከራ ታሳርፊዋለሽ/2/
@aleroe
ኤልሮኢ:
የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም!!
የበደሉንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሳይሆን ፍቅርን ማስተማር ነው። ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህን ኃጢአት አትግለጥ፡፡
የባልጀራህን ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡
ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱ ልክ በእሳት ፊት እንደ ወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡
ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹሕ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደ ተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ቃላቶችህ የተመጠኑና ጤናማዎች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅና ንትርክ ከመግባት ራስህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe
የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም!!
የበደሉንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሳይሆን ፍቅርን ማስተማር ነው። ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህን ኃጢአት አትግለጥ፡፡
የባልጀራህን ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡
ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱ ልክ በእሳት ፊት እንደ ወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡
ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹሕ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደ ተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ቃላቶችህ የተመጠኑና ጤናማዎች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅና ንትርክ ከመግባት ራስህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe
ኤልሮኢ(ስነፅሁፍ)
🖌……ቅን ከሆንን
ፍቅር ካለ፣
ኅብረት ካለ፣
መደጋገፍ ከታከለ፣
እርስ በእርስ ከተዋደድን፣
ሁላችንም ከተሳሰብን፣
አምላክችን ከእኛ ጋር ነው፣
ምንፈልገው በእጃችን ነው።
ሀዋርያት እንደሰሩት፣
ተደጋግፈው እንደኖሩት ፣
በኛ መሀል ፍቅር ካለ፣
መተሳሰብ ካልጎደለ፣
ማን ተጋፍቶን ማን ደርሶብን፤
መሀላችን ማን ገብቶብን፤
የአምላክን ቃል ከፈፀምን፤
ለሰው ሁሉ ቅን ከሆንን።
@aleroe
🖌……ቅን ከሆንን
ፍቅር ካለ፣
ኅብረት ካለ፣
መደጋገፍ ከታከለ፣
እርስ በእርስ ከተዋደድን፣
ሁላችንም ከተሳሰብን፣
አምላክችን ከእኛ ጋር ነው፣
ምንፈልገው በእጃችን ነው።
ሀዋርያት እንደሰሩት፣
ተደጋግፈው እንደኖሩት ፣
በኛ መሀል ፍቅር ካለ፣
መተሳሰብ ካልጎደለ፣
ማን ተጋፍቶን ማን ደርሶብን፤
መሀላችን ማን ገብቶብን፤
የአምላክን ቃል ከፈፀምን፤
ለሰው ሁሉ ቅን ከሆንን።
@aleroe
ኤልሮኢ:
# አጅቡት በዕልልታ
አጅቡት በእልልታ ሲመጣ ሙሽራው
ፍጹም የሚያስደስት የሠርጉ እለት ነው
ዘመዶቹ ሁሉ ተቀበሉት ውጡ
የሙሽራው መምጫ አሁን ነው ሰዓቱ
እልል እንበል/2/ እንዘምር በእልልታ
ይህን ላደረገ ለሠራዊት ጌታ
ሁሉንም በጊዜው ይፈጽማልና
ይኸው አበቃቸው ለዚህ መልካም ዜና
ሙሽሪት ተደሰች ዝምታው ምንድነው
የዳግም ልደትሽ የሠርግሽ እለት ነው
አዳም ጐንሽ ቆሞ ሔዋን ሆይ ሲልሽ
መንፈሳዊ ሐሴት ይሙላ በልብሽ
አዝ ---
እህት ወንድሞቿ እናትና አባቷ
ተነሡ ዘምሩ ለልጃችሁ ደስታ
መሄዷ ነውና ወደ ቤቷ ዛሬ
ወደ አዲስ ጐጆዋ ሽኙአት በዝማሬ
አዝ ---
ቤተሰቦችሽን ሁሉንም ትተሽ
መሄድሽ ነውና ወደ መኖሪያሽ
ከአማኑኤል ጋራ ባልሽን ይዘሽ
ተነሽ ሙሽራዬ ደርሰዋል ሰዓትሽ
ከድንግልም ጋራ ሚስትህን ይዘህ
ተነሥ ወንድሜ ሆይ ደርስዋል ሰዓትህ
💚 @aleroe 💚
# አጅቡት በዕልልታ
አጅቡት በእልልታ ሲመጣ ሙሽራው
ፍጹም የሚያስደስት የሠርጉ እለት ነው
ዘመዶቹ ሁሉ ተቀበሉት ውጡ
የሙሽራው መምጫ አሁን ነው ሰዓቱ
እልል እንበል/2/ እንዘምር በእልልታ
ይህን ላደረገ ለሠራዊት ጌታ
ሁሉንም በጊዜው ይፈጽማልና
ይኸው አበቃቸው ለዚህ መልካም ዜና
ሙሽሪት ተደሰች ዝምታው ምንድነው
የዳግም ልደትሽ የሠርግሽ እለት ነው
አዳም ጐንሽ ቆሞ ሔዋን ሆይ ሲልሽ
መንፈሳዊ ሐሴት ይሙላ በልብሽ
አዝ ---
እህት ወንድሞቿ እናትና አባቷ
ተነሡ ዘምሩ ለልጃችሁ ደስታ
መሄዷ ነውና ወደ ቤቷ ዛሬ
ወደ አዲስ ጐጆዋ ሽኙአት በዝማሬ
አዝ ---
ቤተሰቦችሽን ሁሉንም ትተሽ
መሄድሽ ነውና ወደ መኖሪያሽ
ከአማኑኤል ጋራ ባልሽን ይዘሽ
ተነሽ ሙሽራዬ ደርሰዋል ሰዓትሽ
ከድንግልም ጋራ ሚስትህን ይዘህ
ተነሥ ወንድሜ ሆይ ደርስዋል ሰዓትህ
💚 @aleroe 💚
ኤልሮኢ፡
😕😕 ይታሰብበት ⁉️📝
በዘወትር ፀሎታችን "አቡነ ዘበሰማያት" ላይ ሰዎች የራሳቸውን አባባል እያስገቡ ነውና ይታሰብበት ባይ ነኝ
👉ለምሳሌ "እኛ የበደሉንን ይቅር እንል ዘንድ ……" ይህ ምን ማለት ነው ? ማስፈራራት ወይስ እሱ ባለቤቱን ማረም ? ደሞስ ፈጣሪ ይሳሳታል እንዴ? ይህን ፀሎት እኮ በእኛ ማስተካከያ መደገፍ የለበትም። ምክንያቱም ይህን ፀሎት ስንፀልይ ይቅር ብለን መምጣት እንዳለብን መርሳት የለብንም።(ማቴ 5÷23-26)
ልክ እንደዚሁ "ፀጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ " የሚለውን 3ት ጊዜ ፀጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ንፅህት ሆይ ደስ ይበልሽ የሚለውስ ከየት መጣ ? ስለዚህ ልናስብበት ይገባል !!!!! ሁሉም ሰው እየተነሳ የኔ የሚለውን የመሰለውንና ደስ ያለውን የሚያስገባ ከሆነ ፀሎቱ መሰረቱን እያጣ ይሄዳል ይሄ ብቻ ሳይሆን በየቦታው የተለያየ ይሆንና በጉባኤ በህብረት ለመፀለይ አስቸጋሪ ይሆናል ።
ስለዚህ ልንጠነቀቅ ይገባል እላለው።
……✍ ተፃፈ በተስፋቤል
@aleroe
😕😕 ይታሰብበት ⁉️📝
በዘወትር ፀሎታችን "አቡነ ዘበሰማያት" ላይ ሰዎች የራሳቸውን አባባል እያስገቡ ነውና ይታሰብበት ባይ ነኝ
👉ለምሳሌ "እኛ የበደሉንን ይቅር እንል ዘንድ ……" ይህ ምን ማለት ነው ? ማስፈራራት ወይስ እሱ ባለቤቱን ማረም ? ደሞስ ፈጣሪ ይሳሳታል እንዴ? ይህን ፀሎት እኮ በእኛ ማስተካከያ መደገፍ የለበትም። ምክንያቱም ይህን ፀሎት ስንፀልይ ይቅር ብለን መምጣት እንዳለብን መርሳት የለብንም።(ማቴ 5÷23-26)
ልክ እንደዚሁ "ፀጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ " የሚለውን 3ት ጊዜ ፀጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ንፅህት ሆይ ደስ ይበልሽ የሚለውስ ከየት መጣ ? ስለዚህ ልናስብበት ይገባል !!!!! ሁሉም ሰው እየተነሳ የኔ የሚለውን የመሰለውንና ደስ ያለውን የሚያስገባ ከሆነ ፀሎቱ መሰረቱን እያጣ ይሄዳል ይሄ ብቻ ሳይሆን በየቦታው የተለያየ ይሆንና በጉባኤ በህብረት ለመፀለይ አስቸጋሪ ይሆናል ።
ስለዚህ ልንጠነቀቅ ይገባል እላለው።
……✍ ተፃፈ በተስፋቤል
@aleroe
ኤልሮኢ:
#እውነተኛ ወዳጅ
እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፡፡ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡
አንተ ሆይ! እስኪ ራስህን መርምር፡፡ ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቈጣህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው?
ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቈጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሦ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና፡፡
ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፡፡ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡
┈┈ • ┈┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈•┈┈┈
@aleroe
#እውነተኛ ወዳጅ
እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፡፡ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡
አንተ ሆይ! እስኪ ራስህን መርምር፡፡ ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቈጣህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው?
ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቈጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሦ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና፡፡
ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፡፡ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡
┈┈ • ┈┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈•┈┈┈
@aleroe
ኤልሮኢ:(መዝሙር)
#ፍቅርህ_ማረከኝ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወቴ በዘመኔ/፪/
እግዚአብሔር ለኔ መድኃኒቴ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወ ቴ በዘመኔ
ተገዝቻለው በወርቅ ደምህ አለምን ትቼ ላገለግልህ ሞትህ ህይወቴ ለኔ ሆኖኛል ባንተ መከራ ሸክሜ ርቋል በክብር ቆሜ እዘምራለሁ እንደ አቅሜ አገንሀለሁ
ምድርና ሰማይ እልል ይበሉ መሳይ የለህም ለቅድስና አቀርባለሁኝ ላንተ ምስጋና ጣቴ በገናን ይደረድራል
በቀን በሌሊት ያመሰግናል
ክብርህን አይተው ጠላቶች ፈሩ
በጌትነትህ ወድቀው ተገዙ እንዲህ ነህ አምላክ እንዲህ ነህ ጌታሁሉን በፍቅር የምትረታ በአንተ ተመካነን በፈጣሪያችን አዳኝ በሆንከው በንጉሳችነን
@aleroe
#ፍቅርህ_ማረከኝ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወቴ በዘመኔ/፪/
እግዚአብሔር ለኔ መድኃኒቴ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወ ቴ በዘመኔ
ተገዝቻለው በወርቅ ደምህ አለምን ትቼ ላገለግልህ ሞትህ ህይወቴ ለኔ ሆኖኛል ባንተ መከራ ሸክሜ ርቋል በክብር ቆሜ እዘምራለሁ እንደ አቅሜ አገንሀለሁ
ምድርና ሰማይ እልል ይበሉ መሳይ የለህም ለቅድስና አቀርባለሁኝ ላንተ ምስጋና ጣቴ በገናን ይደረድራል
በቀን በሌሊት ያመሰግናል
ክብርህን አይተው ጠላቶች ፈሩ
በጌትነትህ ወድቀው ተገዙ እንዲህ ነህ አምላክ እንዲህ ነህ ጌታሁሉን በፍቅር የምትረታ በአንተ ተመካነን በፈጣሪያችን አዳኝ በሆንከው በንጉሳችነን
@aleroe
ኤልሮኢ:
...........የሀጢያት ትንሽ ..............
ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡
ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡
🖌……ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
...........የሀጢያት ትንሽ ..............
ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡
ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡
🖌……ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)
#መጎዳቴን_አይቶ
መጎዳቴን አይቶ
ሊቀይር ታሪኬን
ካለሁበት መጥቶ
ሊሞላው ጓዳዬን
መዳን ትወዳለህ ?
ብሎ ቢጠይቀኝ
የሰለለ አካሌን
በአይኔ እያማተርኩኝ
እወዳለሁ ! አልኩት
መፈወስን ሽቼ
የመጥምቁ አምላክ
መሆኑን ሰምቼ፡፡
የጫማውን ጠፍር
መፍታት የተሳነው
ዛሬ ሽባ እግሮቼን
መፈወስ ተቻለው፡፡
ዳንኩኝ በጸበሉ
በእጁ ተጠምቄ
ለምስክር በቃው
በምልጃው ደምቄ፡፡
ከረዳኢ ሃዱሽ
_______________
@aleroe
#መጎዳቴን_አይቶ
መጎዳቴን አይቶ
ሊቀይር ታሪኬን
ካለሁበት መጥቶ
ሊሞላው ጓዳዬን
መዳን ትወዳለህ ?
ብሎ ቢጠይቀኝ
የሰለለ አካሌን
በአይኔ እያማተርኩኝ
እወዳለሁ ! አልኩት
መፈወስን ሽቼ
የመጥምቁ አምላክ
መሆኑን ሰምቼ፡፡
የጫማውን ጠፍር
መፍታት የተሳነው
ዛሬ ሽባ እግሮቼን
መፈወስ ተቻለው፡፡
ዳንኩኝ በጸበሉ
በእጁ ተጠምቄ
ለምስክር በቃው
በምልጃው ደምቄ፡፡
ከረዳኢ ሃዱሽ
_______________
@aleroe
ኤልሮኢ:
#ዝምታ
#ብፁዕ_አቡነ_ሽኖዳ ......
ዝምታ በመጀመሪያ ደረጃው ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው የአንደበት ስህተትን መግታት ማለት ነው፦ " በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።" ምሳ. 10 ፥ 19። ቅዱስ አርሳኔዎስም እንድህ ብሏል ፦ " ብዙ ጊዜ እናገርና እፀፀታለሁ ስለ ዝምታየ ግን ፈጽሞ ተፀፅቼ አላውቅም ።"
በሌላ በኩል ዝምታ ማለት እግዚአብሔር ይሠራ ዘንድ የሰውን ጥረት ማቆም ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር እንድህ ብሏል፦ .." እግዚአብሔር ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ ። እግዚአብሔር ስለእናንተ ይዋጋል እናንተም ዝም ትላላችሁ .." ዘጸ. 14፥ 13-14።
አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰው ለራሱ የማይበቀልና ክፉን በክፉ የማይቃወም ከሆነ ዝምታ እርጋታ ይሆናል።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም .1ኛ ጴጥ. 2፥23። በአይሁድ ሸንጎ ፣ በሐና ፣ በቀያፍ ወይም በጲላጦስ ፊት ሲከሱት ዝም ነው ያለው።
ዝምታ ውስጥ ግን ኃይል ስለነበረ አገረ ገዥው ጲላጦስ ".. እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኜሁበትም ።" ( ዮሐ . 18 ፥ 38) በማለት ተናግሯል።
ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ ለፀሎት ለተመስጦ እድሉን ያደላል።
ብዙ የሚያወራ ሰው ለመፀለይም ሆነ ለውስጣዊ መንፈሳዊ ድርጊት ዕድል አይኖረውም።
አንድ ቅዱስ ሰው".. ብዙ የሚናገር ሰው ውስጡ ባዶ መሆኑን ይገልጣል ።" ብሎ መናገሩ ትክክል ነው። ይህም ማለት ውስጣዊ መንፈሳዊ ሥራ የለውም ማለት ነው።
ቅዱስ አርሳኔዎስ ስለዝምታውና ስለ ምናኔው በተጠየቀ ጊዜ ".. በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ከእግዚአብሔርና ከሰዎች ጋር መሆን አልችልም ።" ብሎ መልሷል።
አንድ ታላቅ መንፈሳዊ አባት የተናገሩት ቃል ምንኛ ድንቅ ነው ፦ " .. ልብህ ይናገር ዘንድ አንደበትህን ዝም አሰኜው እግዚአብሔር ይናገር ዘንድ ልብህን ዝም አሰኜው ።"
የዝምታ አይነቶች ብዙ ቢሆኑም ከነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹ #የአንደበት_ዝምታና_የስሜት_ዝምታ ናቸው። ሰው ስሜቱን ባተሌ እስካላደረገ ድረስ ፀሎቹንና ተመስጦዎቹን ያግዱበት ዘንድ መጥፎ አሳቦችን ያመጡበታል ። ስለሆነም በመንፈሳዊ መንገድ ዝምታውን መጠበቅ የሚወድ ሰው አይኖቹን ፣ ጆሮዎቹንና ስሜቶቹን ሁሉ መጠበቅ አለበት ።
ዝምታ ለሰው መስከንንና እርጋታን አስተምሯል ከጫጫታ፣ ከሁካታ፣ ለመጸለይ አስቸጋሪ ከሚሆኑበትና ሕሊናውን ከሚረብሽበት ብዛት ካላቸው አሳቦች ያርቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ የሚሻው ብቼኝነትንና ጥቂት ጓደኞችን ነው።
ምንጭ፦ መንፈሳዊ ቃላትና ጥቅሞቻቸው ፤ #አያሌው_ዘኢየሱስ እንደተረጎመው ።
የብፁ አባታችን ብራኬ ይደርብን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
@aleroe
#ዝምታ
#ብፁዕ_አቡነ_ሽኖዳ ......
ዝምታ በመጀመሪያ ደረጃው ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው የአንደበት ስህተትን መግታት ማለት ነው፦ " በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።" ምሳ. 10 ፥ 19። ቅዱስ አርሳኔዎስም እንድህ ብሏል ፦ " ብዙ ጊዜ እናገርና እፀፀታለሁ ስለ ዝምታየ ግን ፈጽሞ ተፀፅቼ አላውቅም ።"
በሌላ በኩል ዝምታ ማለት እግዚአብሔር ይሠራ ዘንድ የሰውን ጥረት ማቆም ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር እንድህ ብሏል፦ .." እግዚአብሔር ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ ። እግዚአብሔር ስለእናንተ ይዋጋል እናንተም ዝም ትላላችሁ .." ዘጸ. 14፥ 13-14።
አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰው ለራሱ የማይበቀልና ክፉን በክፉ የማይቃወም ከሆነ ዝምታ እርጋታ ይሆናል።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም .1ኛ ጴጥ. 2፥23። በአይሁድ ሸንጎ ፣ በሐና ፣ በቀያፍ ወይም በጲላጦስ ፊት ሲከሱት ዝም ነው ያለው።
ዝምታ ውስጥ ግን ኃይል ስለነበረ አገረ ገዥው ጲላጦስ ".. እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኜሁበትም ።" ( ዮሐ . 18 ፥ 38) በማለት ተናግሯል።
ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ ለፀሎት ለተመስጦ እድሉን ያደላል።
ብዙ የሚያወራ ሰው ለመፀለይም ሆነ ለውስጣዊ መንፈሳዊ ድርጊት ዕድል አይኖረውም።
አንድ ቅዱስ ሰው".. ብዙ የሚናገር ሰው ውስጡ ባዶ መሆኑን ይገልጣል ።" ብሎ መናገሩ ትክክል ነው። ይህም ማለት ውስጣዊ መንፈሳዊ ሥራ የለውም ማለት ነው።
ቅዱስ አርሳኔዎስ ስለዝምታውና ስለ ምናኔው በተጠየቀ ጊዜ ".. በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ከእግዚአብሔርና ከሰዎች ጋር መሆን አልችልም ።" ብሎ መልሷል።
አንድ ታላቅ መንፈሳዊ አባት የተናገሩት ቃል ምንኛ ድንቅ ነው ፦ " .. ልብህ ይናገር ዘንድ አንደበትህን ዝም አሰኜው እግዚአብሔር ይናገር ዘንድ ልብህን ዝም አሰኜው ።"
የዝምታ አይነቶች ብዙ ቢሆኑም ከነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹ #የአንደበት_ዝምታና_የስሜት_ዝምታ ናቸው። ሰው ስሜቱን ባተሌ እስካላደረገ ድረስ ፀሎቹንና ተመስጦዎቹን ያግዱበት ዘንድ መጥፎ አሳቦችን ያመጡበታል ። ስለሆነም በመንፈሳዊ መንገድ ዝምታውን መጠበቅ የሚወድ ሰው አይኖቹን ፣ ጆሮዎቹንና ስሜቶቹን ሁሉ መጠበቅ አለበት ።
ዝምታ ለሰው መስከንንና እርጋታን አስተምሯል ከጫጫታ፣ ከሁካታ፣ ለመጸለይ አስቸጋሪ ከሚሆኑበትና ሕሊናውን ከሚረብሽበት ብዛት ካላቸው አሳቦች ያርቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ የሚሻው ብቼኝነትንና ጥቂት ጓደኞችን ነው።
ምንጭ፦ መንፈሳዊ ቃላትና ጥቅሞቻቸው ፤ #አያሌው_ዘኢየሱስ እንደተረጎመው ።
የብፁ አባታችን ብራኬ ይደርብን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
@aleroe
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)
#ናፈቀኝ ....
የማለዳ ተመስጦ ... ውዳሴ ማርያም መድገሜ
በልጅነት ልመጣልህ .. ጧት ማታ መፍገምገሜ
ዛሬ ግን ናፍቆት ሆነብኝ .. ተዘረረብኝ አቅሜ
እንቅልፌ ሰላም አጣ .... እባብ ሆነብኝ ሕልሜ ።
.
"እግዚኦ" ሲባል ሰምቼ .. ሳልነሳ ከትራሴ
ድንጋጤ ወረረኝ .. ከእግሬ ጥፍር እስከራሴ
ሰዓታቱን እየሰማሁ ... ተቀሰቀሰ መንፈሴ
ትዝዝ አለኝ ማኅሌቱ ... ስትዋብበት ነፍሴ
የእናቴ ስም ናፈቀኝ ...... የሕርያቆስ ቅዳሴ
.
እራሴንም ስላጣሁት ..... ከቤትህ በመራቄ
እንደ ሎጥ ሚስት መሰልኩኝ ፤ አደባባይ ደርቄ
.
የመዝሙረ-ዳዊት ጸሎት .. አነከተኝ በትዝታ
ነፍሴን ስላስጠማኋት ... አነባችብኝ አብዝታ
እሪሪሪ ብላ አለቀሰች ... በስጋ ወንጭፍ ተገዝታ
.
ናፈቀኝ ትምህርቱ ... የቅዱስ ያሬድ ጸጋ
ቁጥር ዜማ መጮሄ .... አንደበቴ እስኪዘጋ
ዛሬ ላለው ማንነቴ .. ምን ይሆን የ'ኔ ዋጋ ??
.
በከበሮ በጽናጽል ... መዘመሩ ማሸብሸቡ
ጃኖ ለብሶ በመሰለፍ ... ማመርገዱ መወረቡ
የትውስታ ስለት ይዘው ፤ ወደ ልቤ ሰርገው ገቡ
.
አምላኬንም ሳመሰግን .. ወደ ሰማይ አንጋጥጬ
እንዲህ ዛሬ ልቀብረው .. በልቤ ውስጥ ረግጬ
አገልግሎቴ ናፈቀኝ ... ከሁሉ በላይ አስበልጬ
ኮርስ ስማር ትዝ አለኝ ... በዛፉ ስር ተቀምጬ
.
አንገቴ ላይ የታሰረው .. ለምን ነበር ማኅተቤ
ዛሬ ለምን አታለልኩት .. በምክንያት ተንተብትቤ ?
.
ምኑ ነው የሆነብኝ .. ለቤተ መቅደስ እንቅፋት ?
ትዳር ለምን መሰለኝ .. ሜዳ ሆኖ ተዳፋት ?
ልቤ ከብዶ እስከመቼ .. እኖራለሁ በጥፋት ?
ነፍሴንስ ምንበወጣት ... በ'ሳት ጅራፍ ላስገርፋት
.
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ሰው መስዬ ሲመግቡኝ .. ባ'ይኔ ብሌን አይቻለሁ
ታዲያ ግን ምን ዋጋ አለው .. ማንበብ እንደሁ ትቻለሁ
.
እውነት ነው አይካድም .. አውደ ምኅረት መቀመጤ
ወንጌሉንም እየሰማሁ .... ሳላስበው መመሰጤ
ትዝ ይለኛል አጀንዳዬ ... ከንፈሮቼንም መምጠጤ
.
ጽዋ ቢሉ ዝክረ ሰንበት .. እንዳያልፈን ስንጣራ
ዓርብ ጸሎት ስንሰለፍ .. ነጭ ለብሰን በጋራ
ከትንሹም ከትልቁም ... ስለድኅነት ስናወራ
"ጉዞ" ብለን በባዶ እግር .. ሳንደክም በተራራ
ነጭ ለብሰን ጧፍ ይዘን .. እንደ ኮከብ ስናበራ
አዎ! አስታውሳለሁ ... ስልሳ ፍሬ ስናፈራ
.
ጾም ጸሎቱ ትዝ ይለኛል .. በላያችን ስናጌጠው
በስግደት ተሽቀዳድመን ... ሳጥናኤን ስናመልጠው
ብዙ ነበር በንስሐው ... በቁርባኑ የሚገልጠው
.
ጌታ ሆይ!
ተመልሶ ይላክልኝ ... መንፈሳዊ ጀግንነቴ
በመቅደስህ ዋጋ ይክፈል .. የናቡቴ ልጅነቴ
"እሺ" ብሎ እንዳልሰራው .. አይሁንብኝ ማንነቴ
.
ቀራኒዮ አይረሳኝ ... ችንካር ያለው መስቀሉ
በክቡር ደም ተነክሮ .. ቀይ ሆኖ መንቀልቀሉ
.
እመ ብርሐን በልደቷ .. ትመልሰኝ ወደ ጥንቱ
የቅዱሳን ጥበቃቸው .... አይለየኝ በረከቱ
ናፈቀኝ
ሰነፍ ልቤ እየገዛኝ .. በሞት ሰይፍ በጫጨቀኝ
ይቅር በለኝ አምላኬ! ... ከመቅደስህ አታርቀኝ
በግራ መቆም መረረኝ ፤ አሰልፈኝ በልጅህ ቀኝ
አብርሃምን ላክና ... መልስህን ቶሎ አሳውቀኝ
በራሴ አይን ስደናበር.. መታዘብህ አስጨነቀኝ
የምኅረት ቃል አንደበትህ ፤ ፅኑ ፍቅርህ ናፈቀኝ።
#ሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
___________________
@aleroe
#ናፈቀኝ ....
የማለዳ ተመስጦ ... ውዳሴ ማርያም መድገሜ
በልጅነት ልመጣልህ .. ጧት ማታ መፍገምገሜ
ዛሬ ግን ናፍቆት ሆነብኝ .. ተዘረረብኝ አቅሜ
እንቅልፌ ሰላም አጣ .... እባብ ሆነብኝ ሕልሜ ።
.
"እግዚኦ" ሲባል ሰምቼ .. ሳልነሳ ከትራሴ
ድንጋጤ ወረረኝ .. ከእግሬ ጥፍር እስከራሴ
ሰዓታቱን እየሰማሁ ... ተቀሰቀሰ መንፈሴ
ትዝዝ አለኝ ማኅሌቱ ... ስትዋብበት ነፍሴ
የእናቴ ስም ናፈቀኝ ...... የሕርያቆስ ቅዳሴ
.
እራሴንም ስላጣሁት ..... ከቤትህ በመራቄ
እንደ ሎጥ ሚስት መሰልኩኝ ፤ አደባባይ ደርቄ
.
የመዝሙረ-ዳዊት ጸሎት .. አነከተኝ በትዝታ
ነፍሴን ስላስጠማኋት ... አነባችብኝ አብዝታ
እሪሪሪ ብላ አለቀሰች ... በስጋ ወንጭፍ ተገዝታ
.
ናፈቀኝ ትምህርቱ ... የቅዱስ ያሬድ ጸጋ
ቁጥር ዜማ መጮሄ .... አንደበቴ እስኪዘጋ
ዛሬ ላለው ማንነቴ .. ምን ይሆን የ'ኔ ዋጋ ??
.
በከበሮ በጽናጽል ... መዘመሩ ማሸብሸቡ
ጃኖ ለብሶ በመሰለፍ ... ማመርገዱ መወረቡ
የትውስታ ስለት ይዘው ፤ ወደ ልቤ ሰርገው ገቡ
.
አምላኬንም ሳመሰግን .. ወደ ሰማይ አንጋጥጬ
እንዲህ ዛሬ ልቀብረው .. በልቤ ውስጥ ረግጬ
አገልግሎቴ ናፈቀኝ ... ከሁሉ በላይ አስበልጬ
ኮርስ ስማር ትዝ አለኝ ... በዛፉ ስር ተቀምጬ
.
አንገቴ ላይ የታሰረው .. ለምን ነበር ማኅተቤ
ዛሬ ለምን አታለልኩት .. በምክንያት ተንተብትቤ ?
.
ምኑ ነው የሆነብኝ .. ለቤተ መቅደስ እንቅፋት ?
ትዳር ለምን መሰለኝ .. ሜዳ ሆኖ ተዳፋት ?
ልቤ ከብዶ እስከመቼ .. እኖራለሁ በጥፋት ?
ነፍሴንስ ምንበወጣት ... በ'ሳት ጅራፍ ላስገርፋት
.
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ሰው መስዬ ሲመግቡኝ .. ባ'ይኔ ብሌን አይቻለሁ
ታዲያ ግን ምን ዋጋ አለው .. ማንበብ እንደሁ ትቻለሁ
.
እውነት ነው አይካድም .. አውደ ምኅረት መቀመጤ
ወንጌሉንም እየሰማሁ .... ሳላስበው መመሰጤ
ትዝ ይለኛል አጀንዳዬ ... ከንፈሮቼንም መምጠጤ
.
ጽዋ ቢሉ ዝክረ ሰንበት .. እንዳያልፈን ስንጣራ
ዓርብ ጸሎት ስንሰለፍ .. ነጭ ለብሰን በጋራ
ከትንሹም ከትልቁም ... ስለድኅነት ስናወራ
"ጉዞ" ብለን በባዶ እግር .. ሳንደክም በተራራ
ነጭ ለብሰን ጧፍ ይዘን .. እንደ ኮከብ ስናበራ
አዎ! አስታውሳለሁ ... ስልሳ ፍሬ ስናፈራ
.
ጾም ጸሎቱ ትዝ ይለኛል .. በላያችን ስናጌጠው
በስግደት ተሽቀዳድመን ... ሳጥናኤን ስናመልጠው
ብዙ ነበር በንስሐው ... በቁርባኑ የሚገልጠው
.
ጌታ ሆይ!
ተመልሶ ይላክልኝ ... መንፈሳዊ ጀግንነቴ
በመቅደስህ ዋጋ ይክፈል .. የናቡቴ ልጅነቴ
"እሺ" ብሎ እንዳልሰራው .. አይሁንብኝ ማንነቴ
.
ቀራኒዮ አይረሳኝ ... ችንካር ያለው መስቀሉ
በክቡር ደም ተነክሮ .. ቀይ ሆኖ መንቀልቀሉ
.
እመ ብርሐን በልደቷ .. ትመልሰኝ ወደ ጥንቱ
የቅዱሳን ጥበቃቸው .... አይለየኝ በረከቱ
ናፈቀኝ
ሰነፍ ልቤ እየገዛኝ .. በሞት ሰይፍ በጫጨቀኝ
ይቅር በለኝ አምላኬ! ... ከመቅደስህ አታርቀኝ
በግራ መቆም መረረኝ ፤ አሰልፈኝ በልጅህ ቀኝ
አብርሃምን ላክና ... መልስህን ቶሎ አሳውቀኝ
በራሴ አይን ስደናበር.. መታዘብህ አስጨነቀኝ
የምኅረት ቃል አንደበትህ ፤ ፅኑ ፍቅርህ ናፈቀኝ።
#ሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
___________________
@aleroe
ኤልሮኢ:
ስምህ በሁሉ
ስምህ በሁሉ ተመሰገነ
ከክብር በላይ ክብርህ ገነነ
አንተን ማወደስ ያስደስተናል
ስምህን ማክበር ክብራችን ሆኗል(፪)
አምላክ ተመስገን በሰማያት
ስምህ ይወደስ በፍጥረታት
ከህፃናት አፍ ምስጋና ይውጣ
አንተን ማመስገን ይሁን የኛ ዕጣ(፪)
አዝ = = = = = =
በምግብ እጦት ብንሰቃይም
ማህሌትህን አናቋርጥም
የመከራ ዶፍ ቢወርድብንም
እንዘምራለን ለአምላካችን ስም(፪)
አዝ = = = = = =
ሰማዩ ዝናብ ደመና ቢያጣም
ፍቅርህ በእኛ ውስጥ አላቋረጠም
ቸርነትህን እንጠብቃለን
ከአንተ ደጅ ጌታ የት እንሄዳለን(፪)
#ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
@aleroe
ስምህ በሁሉ
ስምህ በሁሉ ተመሰገነ
ከክብር በላይ ክብርህ ገነነ
አንተን ማወደስ ያስደስተናል
ስምህን ማክበር ክብራችን ሆኗል(፪)
አምላክ ተመስገን በሰማያት
ስምህ ይወደስ በፍጥረታት
ከህፃናት አፍ ምስጋና ይውጣ
አንተን ማመስገን ይሁን የኛ ዕጣ(፪)
አዝ = = = = = =
በምግብ እጦት ብንሰቃይም
ማህሌትህን አናቋርጥም
የመከራ ዶፍ ቢወርድብንም
እንዘምራለን ለአምላካችን ስም(፪)
አዝ = = = = = =
ሰማዩ ዝናብ ደመና ቢያጣም
ፍቅርህ በእኛ ውስጥ አላቋረጠም
ቸርነትህን እንጠብቃለን
ከአንተ ደጅ ጌታ የት እንሄዳለን(፪)
#ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
@aleroe
ኤልሮኢ:
አብይ ጾም -የካቲት 25 /06/2011 ሰኞ
ደብረ ዘይት- መጋቢት 22/07/2011 እሁድ
ሆሣዕና- ሚያዚያ 13/08/2011 እሁድ
ስቅለት - ሚያዚያ 18/ 08/2011 አርብ
ትንሳኤ- ሚያዚያ 20/08/2011 አሁድ
እርክበ ካህናት - ግንቦት 14/09/2011 እሮብ
ዕርገት - ግንቦት 29/09/2011 ሀሙስ
ጰራቅሊጦስ - ሰኔ 9/10/2011 እሁድ
ጾመ ሀዋርያት - ሰኔ 10/10/11 ሰኞ
ጾመ ድህነት - ሰኔ 12/10/11እሮብ
@aleroe
አብይ ጾም -የካቲት 25 /06/2011 ሰኞ
ደብረ ዘይት- መጋቢት 22/07/2011 እሁድ
ሆሣዕና- ሚያዚያ 13/08/2011 እሁድ
ስቅለት - ሚያዚያ 18/ 08/2011 አርብ
ትንሳኤ- ሚያዚያ 20/08/2011 አሁድ
እርክበ ካህናት - ግንቦት 14/09/2011 እሮብ
ዕርገት - ግንቦት 29/09/2011 ሀሙስ
ጰራቅሊጦስ - ሰኔ 9/10/2011 እሁድ
ጾመ ሀዋርያት - ሰኔ 10/10/11 ሰኞ
ጾመ ድህነት - ሰኔ 12/10/11እሮብ
@aleroe