ኤልሮኢ
#ጥምቀተ_ባሕር
ጥምቀተ ባሕር ዮርዳኖስ ነያ /2ጊዜ/
ሀሌ ሉያ /4ጊዜ/
አዝ - - - -
ጌታችን ሲጠመቅ ባሕር ምን አለችው
አልችለውም ብላ ወደ ኋላ ሸሸች
ብርሃነ መለኮት በወንዙ ሲሞላ
ዮርዳኖስም ሸሸ ሄደ ወደ ኋላ
አዝ - - - - -
አብ በመጣ ጊዜ ደመናውን ጭኖ
መንፈስ ቅዱስ ታየ በርግብ አምሳል ሆኖ
ለልጁ ምስክር ሊሆን ፈለገና
ቃሉን ተናገረ ሆኖ በደመና
አዝ - - - - - -
ጌታችን ሲጠመቅ በ30 ዓመት
ባሕር ኮበለለች ግዑዟ ፍጥረት
ሰማይ ተከፈተ ሆነልን ፀአዳ
ምሥጢረ ሥላሴ ታየ የዛን ለታ
አዝ - - - - - - -
እልል በይ ዮርዳኖስ የጥምቀት መገኛ
የጽድቅ መሰላል የድኅነታችን መገኛ
ቀላያት አብርህት ብዙዎች እያሉ
እንደምን ተመረጥሽ ዮርዳኖስ ከሁሉ
💛 @aleroe 💛
#ጥምቀተ_ባሕር
ጥምቀተ ባሕር ዮርዳኖስ ነያ /2ጊዜ/
ሀሌ ሉያ /4ጊዜ/
አዝ - - - -
ጌታችን ሲጠመቅ ባሕር ምን አለችው
አልችለውም ብላ ወደ ኋላ ሸሸች
ብርሃነ መለኮት በወንዙ ሲሞላ
ዮርዳኖስም ሸሸ ሄደ ወደ ኋላ
አዝ - - - - -
አብ በመጣ ጊዜ ደመናውን ጭኖ
መንፈስ ቅዱስ ታየ በርግብ አምሳል ሆኖ
ለልጁ ምስክር ሊሆን ፈለገና
ቃሉን ተናገረ ሆኖ በደመና
አዝ - - - - - -
ጌታችን ሲጠመቅ በ30 ዓመት
ባሕር ኮበለለች ግዑዟ ፍጥረት
ሰማይ ተከፈተ ሆነልን ፀአዳ
ምሥጢረ ሥላሴ ታየ የዛን ለታ
አዝ - - - - - - -
እልል በይ ዮርዳኖስ የጥምቀት መገኛ
የጽድቅ መሰላል የድኅነታችን መገኛ
ቀላያት አብርህት ብዙዎች እያሉ
እንደምን ተመረጥሽ ዮርዳኖስ ከሁሉ
💛 @aleroe 💛
✝ ፆመ ገሀድ
ገሃድ መገለጥ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና፡ አንድም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡ (ማቴ 3፡13-17)
ይህን በማሰብ የምንጾመው ጾም “የገሃድ ጾም” ይባላል፡፡ ቀኑም በዓለ ጥምቀት ከመዋሉ አንድ ቀን ቀድሞ ማለትም ጥር 10 ቀን ለ 11 አጥቢያ ነው፡፡ስለዚህ ጥር 10 ቀን ከ ሰባቱ አጽዋማት አንዱ የሆነው የገሃድ ጾም ነው ማለት ነው!
❤️@aleroe❤️
ገሃድ መገለጥ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና፡ አንድም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡ (ማቴ 3፡13-17)
ይህን በማሰብ የምንጾመው ጾም “የገሃድ ጾም” ይባላል፡፡ ቀኑም በዓለ ጥምቀት ከመዋሉ አንድ ቀን ቀድሞ ማለትም ጥር 10 ቀን ለ 11 አጥቢያ ነው፡፡ስለዚህ ጥር 10 ቀን ከ ሰባቱ አጽዋማት አንዱ የሆነው የገሃድ ጾም ነው ማለት ነው!
❤️@aleroe❤️
ኤልሮኢ
+++ ልብስህን ማን ወሰደው? +++
በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፡፡ ለራሱም ‹ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ ‹ታርዤ አልብሳችሁኛልና› ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ አየር እየተሰቃየ እኮ ነው!› ብሎ ፈጥኖ የገዛ ልብሱን ከራሱ በማውለቅ ይለብስ ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደያዘ እርቃኑን በጎዳናው ላይ ተቀመጠ፡፡ የከተማውም ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ቅዱስም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፡፡ ያም ባለጠጋ ልብስን ገዝቶ ካለበሰው በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ዕዳውን መክፈል ስላልቻለ እየተንገላታ ወደ ወኅኒ ቤት የሚሄድን አንድ ሰው ተመለከተ፡፡ ቅዱሱም አባት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱሱን ሽጦ የዚያን ሰው ዕዳ በመክፈል ነጻ አደረገው፡፡ ይህንም ፈጽሞ ጉዞውን ሲጀምር ሌላ አንድ ነዳይ ሲለምን ተመልክቶ ዳግመኛ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ሰጥቶ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እርቃኑን ባዩት ጊዜ ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የሚያጽናናን መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን? › ሲሉ ደግመው ጠየቁት፡፡ አባ ሰራብዮንም ‹መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡
ምንጭ :–Paradise of the monks, P 89
ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም ፣ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የበደል ዕዳ የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና!!!
✝✝@aleroe✝✝
+++ ልብስህን ማን ወሰደው? +++
በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፡፡ ለራሱም ‹ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ ‹ታርዤ አልብሳችሁኛልና› ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ አየር እየተሰቃየ እኮ ነው!› ብሎ ፈጥኖ የገዛ ልብሱን ከራሱ በማውለቅ ይለብስ ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደያዘ እርቃኑን በጎዳናው ላይ ተቀመጠ፡፡ የከተማውም ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ቅዱስም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፡፡ ያም ባለጠጋ ልብስን ገዝቶ ካለበሰው በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ዕዳውን መክፈል ስላልቻለ እየተንገላታ ወደ ወኅኒ ቤት የሚሄድን አንድ ሰው ተመለከተ፡፡ ቅዱሱም አባት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱሱን ሽጦ የዚያን ሰው ዕዳ በመክፈል ነጻ አደረገው፡፡ ይህንም ፈጽሞ ጉዞውን ሲጀምር ሌላ አንድ ነዳይ ሲለምን ተመልክቶ ዳግመኛ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ሰጥቶ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እርቃኑን ባዩት ጊዜ ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የሚያጽናናን መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን? › ሲሉ ደግመው ጠየቁት፡፡ አባ ሰራብዮንም ‹መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡
ምንጭ :–Paradise of the monks, P 89
ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም ፣ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የበደል ዕዳ የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና!!!
✝✝@aleroe✝✝
ኤልሮኢ
✝ ኦ-ክርስቶስ
ኦ ክርስስ ኦ አምላክ ብሩህ ነህ/2/
ልቦናዬን አብራው በጥዑም ቃልህ/2/
አዝ-----
የታቦር ደመና------ክርስቶስ
የሲና ልምላሜ--------ክርስቶስ
ምነው ሙሴን በሆንኩ---ክርስቶስ
እንዳይህ ቀድሜ---- ክርስቶስ
የዮርዳኖስ ውሃ------ክርስቶስ
በላዬ ሲፈላ =ክርስቶስ
የሐንስን በሆንኩ እንዳይህ በተድላ
አዝ--------
ነበልባል ሐመልማል-----ክርስቶስ
ተዋህዶ ሲና------ክርስቶስ
ሙሴ ከሩቅ ሆኖ---ክርስቶስ
ተመልክቷልና-----ክርስቶስ
በቀረበ ጌዜም----ክርስቶስ
ነገሩን ሲረዳ---ክርስቶስ
ለእሥራኤል ሾምከው ሁሉ እንዳይጎዳ
አዝ-----
ሙሴ በበትሩ---ክርስቶስ
ኤርትራን ሲመታ---ክርስቶስ
ተሻገሩ እሥራኤል---ክርስቶስ
በብዙ ደስታ----ክርስቶስ
ያልተደሰቱማ----ክርስቶስ
የፈርኦን ሠራዊት---ክርስቶስ
እየተሰጠሙ ቀሩ ወደ ኀላ
አዝ------
ትንቢቱ ጸደቀ---ክርስቶስ
የኢሳይያስ------ክርስቶስ
ድንግልም ወለደች----ክርስቶስ
በመንፈስ ቅዱስ-----ክርስቶስ
ምነው ባደረገኝ----ክርስቶስ
እንደ ሰሎሜ------ክርስቶስ
ጌታዬ ሲወለድ ለማመስገን ቆሜ
አዝ------
ሐዋርያት ሁሉ-----ክርስቶስ
ዞረው ያስተማሩት---ክርስቶስ
ወንጌልህ ብርሃን ነው----ክርስቶስ
የዓለም መድሃኒት-----ክርስቶስ
ዮሐንስ እንዳለው-----ክርስቶስ
ጥምቀት ለንሰሐ------ክርስቶስ
እጠመቀዋለሁ የጎንህን ውሃ
አዝ------
ሚካኤል በቀኝህ-----ክርስቶስ
ገብርኤል በግራ-----ክርስቶስ
ቅውማን የሆኑት-----ክርስቶስ
ሁሉም በየተራ------ክርስቶስ
ሱራፌል ኪሩቤል----ክርስቶስ
ዐይናቸው የበዛ------ክርስቶስ
ያመሰግኑሃል አንተን የዓለም ቤዛ
💚 @aleroe ❤
✝ ኦ-ክርስቶስ
ኦ ክርስስ ኦ አምላክ ብሩህ ነህ/2/
ልቦናዬን አብራው በጥዑም ቃልህ/2/
አዝ-----
የታቦር ደመና------ክርስቶስ
የሲና ልምላሜ--------ክርስቶስ
ምነው ሙሴን በሆንኩ---ክርስቶስ
እንዳይህ ቀድሜ---- ክርስቶስ
የዮርዳኖስ ውሃ------ክርስቶስ
በላዬ ሲፈላ =ክርስቶስ
የሐንስን በሆንኩ እንዳይህ በተድላ
አዝ--------
ነበልባል ሐመልማል-----ክርስቶስ
ተዋህዶ ሲና------ክርስቶስ
ሙሴ ከሩቅ ሆኖ---ክርስቶስ
ተመልክቷልና-----ክርስቶስ
በቀረበ ጌዜም----ክርስቶስ
ነገሩን ሲረዳ---ክርስቶስ
ለእሥራኤል ሾምከው ሁሉ እንዳይጎዳ
አዝ-----
ሙሴ በበትሩ---ክርስቶስ
ኤርትራን ሲመታ---ክርስቶስ
ተሻገሩ እሥራኤል---ክርስቶስ
በብዙ ደስታ----ክርስቶስ
ያልተደሰቱማ----ክርስቶስ
የፈርኦን ሠራዊት---ክርስቶስ
እየተሰጠሙ ቀሩ ወደ ኀላ
አዝ------
ትንቢቱ ጸደቀ---ክርስቶስ
የኢሳይያስ------ክርስቶስ
ድንግልም ወለደች----ክርስቶስ
በመንፈስ ቅዱስ-----ክርስቶስ
ምነው ባደረገኝ----ክርስቶስ
እንደ ሰሎሜ------ክርስቶስ
ጌታዬ ሲወለድ ለማመስገን ቆሜ
አዝ------
ሐዋርያት ሁሉ-----ክርስቶስ
ዞረው ያስተማሩት---ክርስቶስ
ወንጌልህ ብርሃን ነው----ክርስቶስ
የዓለም መድሃኒት-----ክርስቶስ
ዮሐንስ እንዳለው-----ክርስቶስ
ጥምቀት ለንሰሐ------ክርስቶስ
እጠመቀዋለሁ የጎንህን ውሃ
አዝ------
ሚካኤል በቀኝህ-----ክርስቶስ
ገብርኤል በግራ-----ክርስቶስ
ቅውማን የሆኑት-----ክርስቶስ
ሁሉም በየተራ------ክርስቶስ
ሱራፌል ኪሩቤል----ክርስቶስ
ዐይናቸው የበዛ------ክርስቶስ
ያመሰግኑሃል አንተን የዓለም ቤዛ
💚 @aleroe ❤
ኤልሮኢ
ሞገድ ሲመታኝ
ሞገድ ሲመታኝ ማእበሉ
ማን ያድነዋል ሁሉም ሲሉ
በሰላም አለፍኩ በፀጥታ
ሁሉተችሎ ባንተጌታ
ባንተስ ቁስል ተፈወስኩኝ
ጌታ በፍቅርህ ተማረኩኝ
ሞቴን ሽረኀው ባንተሞት /2/
ይኀው አቆምከኝ በሂወት /2/
ደጅህ ሲጠና ስማፀንክ
መቼ ጨከነጌታ ልብ
እንደቀራጩ አጎነበስኩ
ምህረት ፀጋህን ከጂህ ለበስኩ
ዘውትር እልል ብልብዘምር
ስለገባኝ ነው ያንተፍቅር
ጌታ ምጠራው ስምህን/2/
ለውጠኀው ነው ታሪኬን/2/
አይኖች አያዩ ካንተበቀር
የምትወደድ ምትፈቀር
ዘመድ ወገኔ ሆነህኛል
እኔን የሚችል የት ይገኛል
💚@aleroe💚
ሞገድ ሲመታኝ
ሞገድ ሲመታኝ ማእበሉ
ማን ያድነዋል ሁሉም ሲሉ
በሰላም አለፍኩ በፀጥታ
ሁሉተችሎ ባንተጌታ
ባንተስ ቁስል ተፈወስኩኝ
ጌታ በፍቅርህ ተማረኩኝ
ሞቴን ሽረኀው ባንተሞት /2/
ይኀው አቆምከኝ በሂወት /2/
ደጅህ ሲጠና ስማፀንክ
መቼ ጨከነጌታ ልብ
እንደቀራጩ አጎነበስኩ
ምህረት ፀጋህን ከጂህ ለበስኩ
ዘውትር እልል ብልብዘምር
ስለገባኝ ነው ያንተፍቅር
ጌታ ምጠራው ስምህን/2/
ለውጠኀው ነው ታሪኬን/2/
አይኖች አያዩ ካንተበቀር
የምትወደድ ምትፈቀር
ዘመድ ወገኔ ሆነህኛል
እኔን የሚችል የት ይገኛል
💚@aleroe💚
ኤልሮኢ
#ወዳጄ ሆይ!
የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡
አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
#ወዳጄ ሆይ!
የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡
አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
ኤልሮኢ
"ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡"
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
"ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡"
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
ኤልሮኢ
ጥር 19/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር እሙነ ኮነ ልደቱ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን 2ቆሮ 1÷13_ፍ.ም
ን/ዲ 1ዮሐ 2÷22_ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ13÷20_28
#የዕለቱ_ምስባክ
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ
ግበሩ በዓለ በትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ መዝ ፻፲፯፥፳፯
#ትርጉም
ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠን
በሚያስተነትኑበት በደስታ በዓልን አድርጉ
እስከ መሠዊያው ቀንድ ድረስ
#የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ 2÷42-ፍ.ም
#ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ጥር 19/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር እሙነ ኮነ ልደቱ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን 2ቆሮ 1÷13_ፍ.ም
ን/ዲ 1ዮሐ 2÷22_ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ13÷20_28
#የዕለቱ_ምስባክ
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ
ግበሩ በዓለ በትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ መዝ ፻፲፯፥፳፯
#ትርጉም
ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠን
በሚያስተነትኑበት በደስታ በዓልን አድርጉ
እስከ መሠዊያው ቀንድ ድረስ
#የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ 2÷42-ፍ.ም
#ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ኤልሮኢ
✞ በማህፀን ቅኔ
በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ
በተራራማው ሀገር በኤፈሬምከተማ
ዩሀንስ ይናገር በረሀ ያደገው
ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው
የናቱማህፀን የቅኔርስቱነች
ድንግል ያምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች
በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ
ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ
በድንግል ማህፀን ስላየጌታውን
ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን
ትንቢቱ ሲፈፀም በሆድዋሲነግስ
ሰገደላምላኩ የስድስትወር ፅንስ
ጀመረስብከቱን ገና ሳይወለድ
ተፈጥሮ መችቻለ ነብዩን ለማገድ
አፉ ተከፈተ በታለቅ ምስጋና
በናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና
የዩሀንስ እናት አሰልሳቤት ገረማት
ልጃዋ በማህፀን ቅኔ ሲቀኝባት
ድምፅን ከፍ አረገች ሀገር እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ ለመዝሙር ለዜማ
✞ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ✞
❤ @aleroe ❤
✞ በማህፀን ቅኔ
በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ
በተራራማው ሀገር በኤፈሬምከተማ
ዩሀንስ ይናገር በረሀ ያደገው
ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው
የናቱማህፀን የቅኔርስቱነች
ድንግል ያምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች
በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ
ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ
በድንግል ማህፀን ስላየጌታውን
ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን
ትንቢቱ ሲፈፀም በሆድዋሲነግስ
ሰገደላምላኩ የስድስትወር ፅንስ
ጀመረስብከቱን ገና ሳይወለድ
ተፈጥሮ መችቻለ ነብዩን ለማገድ
አፉ ተከፈተ በታለቅ ምስጋና
በናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና
የዩሀንስ እናት አሰልሳቤት ገረማት
ልጃዋ በማህፀን ቅኔ ሲቀኝባት
ድምፅን ከፍ አረገች ሀገር እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ ለመዝሙር ለዜማ
✞ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ✞
❤ @aleroe ❤
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)
✥ሞት ሆይ ተጠየቅ✥
💐ሞት ሆይ ተጠየቅ ኤልያስን ያስነጠቀውን ሄኖክን ከሞት የሰወረውን ሞትን በሞቱ የገደለውን በትንሣኤው ለትንሳኤያችን በኩር የሆነውን ጌታ የጸነሰችውን ለሞትህ ሞት የሆነውን ጌታ የወለደችውን ድንግል ትቀርባት ዘንድ እንዴት ደፈርክ?
🌹ሞት ሆይ ተጠየቅ ለሕያው እግዚአብሔር መቅደስ የሆነችውን ንጉሡ ከነ ሠራዊቱ(መላእክቱ) የከተመባትን ከተማ በላይ ሳይጎድል በታችም ሳይጨመር የተወለደባትን ቅድስት ትይዛት ዘንድ እንዴት ደፈርክ?
ሞት ሆይ ተጠየቅ ሰማይ ዙፋኑ ምድር መከየደ እግሩ የሆነለትን በሁሉ ያለ ሁሉን የሚወስን የሚወስነው ምንም ነገር የሌለን የተሸከመችን ድንግል ትቀርባት ዘንድ ምን አስቻለህ?
🌷 ሞት ሆይ ተጠየቅ ወለተ ኢያኢሮስን እንቅፍ ከሚመስል ሞት ተነሺ ብሎ ያስነሳትን አልአዛርን ናብሎ ከሞቱ የጠራውን ከመገንዙ ፈቶ ይመላለስ ዘንድ ያስቻለውን የሲኦል ደጆች በቃሉ የሚሩድለት ጌታ የተገኘባት ድንግልን ትቀርብ ዘንድ ምን አጸናህ?
🍀ሞት ሆይ ተጠይቅ? እርሱስ ለእርሱም መልስ የለውምና ከሊቁ ጋር እንዲህ እያልን እናድንቅ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባል የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል!
እንኳን የእመቤታችንን ዕረፍት ለምናስብበት በዓል አደረሳችሁ!
✞
ባሮክ(ኢብሎጊቶስ)
@aleroe
✥ሞት ሆይ ተጠየቅ✥
💐ሞት ሆይ ተጠየቅ ኤልያስን ያስነጠቀውን ሄኖክን ከሞት የሰወረውን ሞትን በሞቱ የገደለውን በትንሣኤው ለትንሳኤያችን በኩር የሆነውን ጌታ የጸነሰችውን ለሞትህ ሞት የሆነውን ጌታ የወለደችውን ድንግል ትቀርባት ዘንድ እንዴት ደፈርክ?
🌹ሞት ሆይ ተጠየቅ ለሕያው እግዚአብሔር መቅደስ የሆነችውን ንጉሡ ከነ ሠራዊቱ(መላእክቱ) የከተመባትን ከተማ በላይ ሳይጎድል በታችም ሳይጨመር የተወለደባትን ቅድስት ትይዛት ዘንድ እንዴት ደፈርክ?
ሞት ሆይ ተጠየቅ ሰማይ ዙፋኑ ምድር መከየደ እግሩ የሆነለትን በሁሉ ያለ ሁሉን የሚወስን የሚወስነው ምንም ነገር የሌለን የተሸከመችን ድንግል ትቀርባት ዘንድ ምን አስቻለህ?
🌷 ሞት ሆይ ተጠየቅ ወለተ ኢያኢሮስን እንቅፍ ከሚመስል ሞት ተነሺ ብሎ ያስነሳትን አልአዛርን ናብሎ ከሞቱ የጠራውን ከመገንዙ ፈቶ ይመላለስ ዘንድ ያስቻለውን የሲኦል ደጆች በቃሉ የሚሩድለት ጌታ የተገኘባት ድንግልን ትቀርብ ዘንድ ምን አጸናህ?
🍀ሞት ሆይ ተጠይቅ? እርሱስ ለእርሱም መልስ የለውምና ከሊቁ ጋር እንዲህ እያልን እናድንቅ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባል የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል!
እንኳን የእመቤታችንን ዕረፍት ለምናስብበት በዓል አደረሳችሁ!
✞
ባሮክ(ኢብሎጊቶስ)
@aleroe
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)
// አትጥፊ ጨረቃ //
🌙🌑
የዘመኑ ትውልድ ከእንቅልፉ እስኪነቃ
ማዬቱን እስኪያምን የአለምን ጠበቃ
ምስክር ነሽ አንች አትግቢ ጨረቃ
ይዩሽ የማያምኑ ማየት ያልታደሉ
የጨረቃ ግርዶሽ ተከሰተ ላሉ
ከእውነት ተደብቀው ጥምቀትን የጠሉ
ታምር በጨረቃ ይዩልን የት አሉ
አየሽ ጨረቃዬ ማየት ያልታደለ ማሰተዋል ያቃተው
እውነት ግን ታምር ነው? ሲል ማመን ላቃተው
ህሌናውን ጋርዶት ሰው መሆን ለማያምነው
የጥምቀትን ሚስጥር ተረድቶ እስኪነቃ
ምስክር ነሽ እና አንች የኛ ድንቡልቃ
በፈጠረሽ አምላክ አትጥፊ ጨረቃ!!
#ይሄንን ጽሑፍ ሌሎች ክርስቲያን እህት ወንድሞቻጅን እንዲደርስ👉 Share ያድርጉ...
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe @aleroe @aleroe
@aleroe @aleroe @aleroe
@aleroe @aleroe @aleroe
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
// አትጥፊ ጨረቃ //
🌙🌑
የዘመኑ ትውልድ ከእንቅልፉ እስኪነቃ
ማዬቱን እስኪያምን የአለምን ጠበቃ
ምስክር ነሽ አንች አትግቢ ጨረቃ
ይዩሽ የማያምኑ ማየት ያልታደሉ
የጨረቃ ግርዶሽ ተከሰተ ላሉ
ከእውነት ተደብቀው ጥምቀትን የጠሉ
ታምር በጨረቃ ይዩልን የት አሉ
አየሽ ጨረቃዬ ማየት ያልታደለ ማሰተዋል ያቃተው
እውነት ግን ታምር ነው? ሲል ማመን ላቃተው
ህሌናውን ጋርዶት ሰው መሆን ለማያምነው
የጥምቀትን ሚስጥር ተረድቶ እስኪነቃ
ምስክር ነሽ እና አንች የኛ ድንቡልቃ
በፈጠረሽ አምላክ አትጥፊ ጨረቃ!!
#ይሄንን ጽሑፍ ሌሎች ክርስቲያን እህት ወንድሞቻጅን እንዲደርስ👉 Share ያድርጉ...
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@aleroe @aleroe @aleroe
@aleroe @aleroe @aleroe
@aleroe @aleroe @aleroe
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
ኤልሮኢ፡
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሕዱ አምላክ አሜን
✝✝አስተርእዮ ማርያም✝✝
ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኩሉ"
ሞት ለሚሞት ሰው ይገባዋል
የማርያም ሞት ግን በጣም ያስደንቃል
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሃን ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ታላቅ አመታዊ በዓል ( ለአስተርእዮ ማርያም) በሰላም በጤና አደረሳችሁ:: አደረሰን!
✞ አስተርእዮ ማለት? መታየት መገለጽ ነው
እመቤታችን ጥር ሃያ አንድ ቀን ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይቶ በደመና ተነጥቃ ወደ ገነት በመግባት ለጻድቃን ሰዎችና ለመላእክት በሰማይና በምድር ተገልጣ ጸጋና ክብሯ የተገለጸበት እለት በመሆኑ በዓሉ አስተርእዮ ማርያም ይባላል::
✞ ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድ የእመቤታችንን ሞት አስደናቂ መሆኑን እንዲህ ሲል ገልጦታል
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኩሉ"
ሞት ለማናቸወም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል
የእመቤታችን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንና እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት አመት በቤተ መቅደስ አስራ ሁለት አመት ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰላሣ ሦስት አመት ከሦስት ወር በዮሀንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ አስራ አራት አመት ከዘጠኝ ወር በጠቅላላው ስልሣ አራት አመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች::
እመቤታችን ጥር ሃያ አንድ ቀን ዕረፍት በሆነበት ዕለት ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለማሳረፍ ወደ ጌቴሰማኒ መካነ ዕረፍት /የመቃብር ቦታ/ ይዘዋት ሲሆዱ አይሁድ በቅንዓት መንፈስ ተነሳስተው ቀድሞ ልጇን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ አረገ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል እያለ በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጇ ተነሳች አረገች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለም ኑ ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት ብለው ተማክረው መጥተው ከመካከላቸው ታውፋኒያ የተባለው ጎበዝ አይሁዳዊ ተመረጦ ሄደ::
የእመቤታችንን ሥጋ የተሸከሙትን አልጋ ያዘ የአልጋውንም ጥራዝ በያዘ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁለት እጁን ሰለቆረጣቸው ከአልጋው ጫፍ ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ ታውፋንያ በፈጸመው ድርጊት ተጸጽቶ ወደ እመቤታችን ስለተማጸነ በኀቡዕ ተአምር የተቆረጡ እጆቹን እንደቀድሞ አድርጋ ፈውሳዋለች::
{ስንክሳር ዘጥር}
✞ ለበቁ ቅዱሳን ተአምሯን የገለጸች እመቤታችን ለእኛም ለልጆቿ ከልጇ ከወዳጇ በአማላጅነቷ ምሕረትን ይቅርታው ታሰጠን::አሜን!
ለተጨነቁ በስደት ላሉ በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ትፈውስልን የእናታችን የአዛኝቷ ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይሁን አሜን::
➕➕@aleroe➕➕
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሕዱ አምላክ አሜን
✝✝አስተርእዮ ማርያም✝✝
ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኩሉ"
ሞት ለሚሞት ሰው ይገባዋል
የማርያም ሞት ግን በጣም ያስደንቃል
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሃን ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ታላቅ አመታዊ በዓል ( ለአስተርእዮ ማርያም) በሰላም በጤና አደረሳችሁ:: አደረሰን!
✞ አስተርእዮ ማለት? መታየት መገለጽ ነው
እመቤታችን ጥር ሃያ አንድ ቀን ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይቶ በደመና ተነጥቃ ወደ ገነት በመግባት ለጻድቃን ሰዎችና ለመላእክት በሰማይና በምድር ተገልጣ ጸጋና ክብሯ የተገለጸበት እለት በመሆኑ በዓሉ አስተርእዮ ማርያም ይባላል::
✞ ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድ የእመቤታችንን ሞት አስደናቂ መሆኑን እንዲህ ሲል ገልጦታል
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኩሉ"
ሞት ለማናቸወም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል
የእመቤታችን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንና እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት አመት በቤተ መቅደስ አስራ ሁለት አመት ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰላሣ ሦስት አመት ከሦስት ወር በዮሀንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ አስራ አራት አመት ከዘጠኝ ወር በጠቅላላው ስልሣ አራት አመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች::
እመቤታችን ጥር ሃያ አንድ ቀን ዕረፍት በሆነበት ዕለት ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለማሳረፍ ወደ ጌቴሰማኒ መካነ ዕረፍት /የመቃብር ቦታ/ ይዘዋት ሲሆዱ አይሁድ በቅንዓት መንፈስ ተነሳስተው ቀድሞ ልጇን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ አረገ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል እያለ በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጇ ተነሳች አረገች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለም ኑ ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት ብለው ተማክረው መጥተው ከመካከላቸው ታውፋኒያ የተባለው ጎበዝ አይሁዳዊ ተመረጦ ሄደ::
የእመቤታችንን ሥጋ የተሸከሙትን አልጋ ያዘ የአልጋውንም ጥራዝ በያዘ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁለት እጁን ሰለቆረጣቸው ከአልጋው ጫፍ ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ ታውፋንያ በፈጸመው ድርጊት ተጸጽቶ ወደ እመቤታችን ስለተማጸነ በኀቡዕ ተአምር የተቆረጡ እጆቹን እንደቀድሞ አድርጋ ፈውሳዋለች::
{ስንክሳር ዘጥር}
✞ ለበቁ ቅዱሳን ተአምሯን የገለጸች እመቤታችን ለእኛም ለልጆቿ ከልጇ ከወዳጇ በአማላጅነቷ ምሕረትን ይቅርታው ታሰጠን::አሜን!
ለተጨነቁ በስደት ላሉ በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ትፈውስልን የእናታችን የአዛኝቷ ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይሁን አሜን::
➕➕@aleroe➕➕
ኤልሮኢ:
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል ይገባል(2)
የድንግል አሟሟት እጅጉን ይደንቃል(2)
ለልጇ ስትነግር ሞት እንደምትፈራ(2)
ወሰዷት በሃሴት መላእክተ ሐራ(2)
ጭንቀቱ ሳይገጥማት ሳታስብ ድንገት(2)
እንደ እንቅልፍ ወሰዳት ያ መልአከ ሞት(2)
አዝ ///
ይገርማል ይደንቃል የድንግል ፍልሰታ(2)
በምስጋና አረገች ከልጇ ተጠርታ
በይባቤ አረገች ከልጇ ተጠርታ
እያሸበሸቡ መላእክተ ሰማይ(2)
ወስደው አቀረቧት ከልጇ መንበር ላይ(2)
አዝ //
ሱባኤ እንደገቡ እንደ ሐዋርያት(2)
እኔም ከቤት ወጣሁ አንቺኑ በመሻት(2)
ትንሳኤሽን በክብር እንዳሳየሻቸው(2)
እኔንም ለዚህ አብቂኝ ብርሃንሽን እንዳየው(2)
💚@aleroe💚
💛@aleroe💛
❤@aleroe❤
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል ይገባል(2)
የድንግል አሟሟት እጅጉን ይደንቃል(2)
ለልጇ ስትነግር ሞት እንደምትፈራ(2)
ወሰዷት በሃሴት መላእክተ ሐራ(2)
ጭንቀቱ ሳይገጥማት ሳታስብ ድንገት(2)
እንደ እንቅልፍ ወሰዳት ያ መልአከ ሞት(2)
አዝ ///
ይገርማል ይደንቃል የድንግል ፍልሰታ(2)
በምስጋና አረገች ከልጇ ተጠርታ
በይባቤ አረገች ከልጇ ተጠርታ
እያሸበሸቡ መላእክተ ሰማይ(2)
ወስደው አቀረቧት ከልጇ መንበር ላይ(2)
አዝ //
ሱባኤ እንደገቡ እንደ ሐዋርያት(2)
እኔም ከቤት ወጣሁ አንቺኑ በመሻት(2)
ትንሳኤሽን በክብር እንዳሳየሻቸው(2)
እኔንም ለዚህ አብቂኝ ብርሃንሽን እንዳየው(2)
💚@aleroe💚
💛@aleroe💛
❤@aleroe❤
ኤልሮኢ:
# መልአከ ሰላምነ
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ኡራኤል/2/
ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለመድኃኔዓለም/2/
ትርጉም ፦
አንተ የሰላም መልአክ ሊቀ መላእክት ዑራኤል (2)
ለምን ስለኛ ፀልይልን አሳርግ ፀሎታችንን በመንበሩ ፊት ለመድሃኒአለም (2)
💚@aleroe❤
# መልአከ ሰላምነ
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ኡራኤል/2/
ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለመድኃኔዓለም/2/
ትርጉም ፦
አንተ የሰላም መልአክ ሊቀ መላእክት ዑራኤል (2)
ለምን ስለኛ ፀልይልን አሳርግ ፀሎታችንን በመንበሩ ፊት ለመድሃኒአለም (2)
💚@aleroe❤
ኤልሮኢ፡
✍.....ትህትና በአባቶች ሕይወትና ትምህርት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል። ቅዱስ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል ስለ ትህትና ማስተማር እፈልጋለሁ። ደግሞ እፈራለሁ። ስለ እግዚአብሔር ለመናገር እንደሚፈራ ሰው እመስላለሁ። ምክንያቱም ትህትና መለኮት ሰው ሆኖ በምድር ሲገለጥ የተጠቀለለበት መጎናጸፊ ነውና። ሰው ሆኖ በአጭር ደረት በጠባብ ቁመት የመገለጡም ምሥጢር እጅግ አስደናቂ በሆነ በትህትናው ነው። ይሄ ሁኔታው ያስደነቀው ነቢዩ ኢሳይያስ "ያልተጠባበቅነውን የጽድቅ ሥራህን ባደረግህ ጊዜ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ" ኢሳ. 64፥4 ብሏል። ሰይጣን ትሁት ሰው ሲያይ የሚፈራው በትሁት ሰው ውስጥ የፈጠረውንና በትህትና ያሸነፈውን እግዚአብሔር ስለሚያየው ነው።
@aleroe
✍.....ትህትና በአባቶች ሕይወትና ትምህርት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል። ቅዱስ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል ስለ ትህትና ማስተማር እፈልጋለሁ። ደግሞ እፈራለሁ። ስለ እግዚአብሔር ለመናገር እንደሚፈራ ሰው እመስላለሁ። ምክንያቱም ትህትና መለኮት ሰው ሆኖ በምድር ሲገለጥ የተጠቀለለበት መጎናጸፊ ነውና። ሰው ሆኖ በአጭር ደረት በጠባብ ቁመት የመገለጡም ምሥጢር እጅግ አስደናቂ በሆነ በትህትናው ነው። ይሄ ሁኔታው ያስደነቀው ነቢዩ ኢሳይያስ "ያልተጠባበቅነውን የጽድቅ ሥራህን ባደረግህ ጊዜ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ" ኢሳ. 64፥4 ብሏል። ሰይጣን ትሁት ሰው ሲያይ የሚፈራው በትሁት ሰው ውስጥ የፈጠረውንና በትህትና ያሸነፈውን እግዚአብሔር ስለሚያየው ነው።
@aleroe
ኤልሮኢ፡(ስነፅሁፍ)
… ✍ምንም አይምሰልህ
የምትሰራው ስራ ሰውን ካልበደለ፣
ክፋትና ተንኮል በልብህ ከሌለ።
ጠንቅቀህ ከፈፀምክ ማድረግ ያለብህን፣
ማንንም ካልጎዳህ ካመንክ አምላክህን።
ላንተ ጥቅም ብለህ ካልገፋህ ሌላውን፣
ይቅርታ ከለመንክ አምነህ ጥፋትህን።
የምታውቀው ታሪክ የምታውቀው ነገር፣
እንዳልሆነ ሆኖ ሲወራ ሲነገር።
የለብህምና ዝም ብሎ መስማት፣
ቀስ ብለህ ብትሞክር ለመስጠት እርማት።
ከእኛ ሌላ አዋቂ ፍፁም የለም ባዮች ፣
የወሬ አንበሳ የተግባር አንካሶች፣
የነገር ሱሰኛ የወሬ ጥመኞች።
ምንም እንደማታውቅ አድርገው ቢቆጡርህ፣
እውቀቱ ካንተ ጋር ታዲያ ምን ቸገረህ፣
አምላክ ካንተ ጋር ነው ምንም አይምሰልህ።
@aleroe
… ✍ምንም አይምሰልህ
የምትሰራው ስራ ሰውን ካልበደለ፣
ክፋትና ተንኮል በልብህ ከሌለ።
ጠንቅቀህ ከፈፀምክ ማድረግ ያለብህን፣
ማንንም ካልጎዳህ ካመንክ አምላክህን።
ላንተ ጥቅም ብለህ ካልገፋህ ሌላውን፣
ይቅርታ ከለመንክ አምነህ ጥፋትህን።
የምታውቀው ታሪክ የምታውቀው ነገር፣
እንዳልሆነ ሆኖ ሲወራ ሲነገር።
የለብህምና ዝም ብሎ መስማት፣
ቀስ ብለህ ብትሞክር ለመስጠት እርማት።
ከእኛ ሌላ አዋቂ ፍፁም የለም ባዮች ፣
የወሬ አንበሳ የተግባር አንካሶች፣
የነገር ሱሰኛ የወሬ ጥመኞች።
ምንም እንደማታውቅ አድርገው ቢቆጡርህ፣
እውቀቱ ካንተ ጋር ታዲያ ምን ቸገረህ፣
አምላክ ካንተ ጋር ነው ምንም አይምሰልህ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
ጥር 26/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር ተወልደ ኢየሱስ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 1÷1_12
ን/ዲ 1ጴጥ 1÷13_22
ን/ካ ግብ፡ሐዋ10÷1_11
#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ 47፥8
በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ
በሀገረ እግዚአ ኃያላን በሀገረ አምላክነ
እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም::
#ትርጉም፦
እንደሰማን እንዲሁ አየን
በሠራዊት ጌታ ከተማ በአምላካችን ሀገር
እግዚአብሔር ለዓለም አጸናት
#የዕለቱ ወንጌል፦ ሉቃ 2፥36 - ፍጻሜ
ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ጥር 26/05/11 ዓ.ም.
መዝሙር ተወልደ ኢየሱስ
#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 1÷1_12
ን/ዲ 1ጴጥ 1÷13_22
ን/ካ ግብ፡ሐዋ10÷1_11
#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ 47፥8
በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ
በሀገረ እግዚአ ኃያላን በሀገረ አምላክነ
እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም::
#ትርጉም፦
እንደሰማን እንዲሁ አየን
በሠራዊት ጌታ ከተማ በአምላካችን ሀገር
እግዚአብሔር ለዓለም አጸናት
#የዕለቱ ወንጌል፦ ሉቃ 2፥36 - ፍጻሜ
ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
👉 @aleroe
ኤልሮኢ፡
…… ✍ አትማረኝ
--------------
በጣና ገዳማት ውስጥ የአቡነ አሳይ ዋሻ አለ በዚህ ዋሻ አንድ ያልተማረ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የማያውቅ ሰው ጸሎት ሲጸልይ አንድ አባት በጀልባ ተሳፍረው ይመጡና ያገኙታል።
ወደ ደሴቷም አረፍ ልበል ብለው ሲገቡ ያ ወጣት ሲጸልይ ይሰሙታል ቀረብ ብለው ቢያደምጡ ይህ ሰው የሚጸልየው "አትማረኝ" እያለ ነው።
እኝህ አባት በጣም ይደነግጡና እንዲህ ያለ ጸሎት አለ ወይ አትማረኝ የሚል ማን ነው ያስተማረህ ሲሉት አንድ መነኩሴ ነው ያስተማሩኝ አላቸው።
እሳቸውም ይህማ ሰይጣን ነው በመነኩሴ ተመስሎ ያስተማረህ እንጂ አትማረኝ ብሎ ጸሎት የለም ብለው "አቡነ ዘበሰማያትን" አስተማሩት። ይኽ ሰው እንደምንም ታግሎ አባታችን ሆይን ከተማረ በኋላ እኝህን አባት ያሰናብታቸዋል።
እሳቸውም በጀልባ ተሳፍረው መንገድ ሲጀምሩ ይኽ ወጣት ወደ ቀደመ በዓቱ ገብቶ መጸለይ ሲጀምር ያን ጸሎት ረሳው። ምን ነበር ያስተማሩኝ ብሎ ቢያስብ ጠፋበት። ከበዓቱም ሮጦ ወጥቶ በጀልባ ተሳፍረው የሚሄዱትን አባት አስቁሞ "ምን ብለው ነው ያስተምሩኝ?" ብሎ ጠየቃቸው እኝህም አባት ሲያዩት ውሃ ላይ ቆሟል፣ በውሃ ላይ ነው ሮጦ የመጣው አትኩረው ቢመለከቱት ውኃው ላይ እንደቆመ ነው።
"በል የእኔ ልጅ እንደቀድሞው አትማረኝ እያልክ ጸልይ" አሉት ይባላል።
ወጣቱ ባለማወቅ በሚጸልየው ጸሎት ውስጥ በቅቶ ነበር። እግዚአብሔር የሰማው ያለውን ሳይሆን የልቦናውን ነው።
የምንጸልየው ጸሎት የተዘበራረቀ ቢሆንም እንኳን እግዚአብሔር እያቃና ይሰማዋል። ስለዚህም ከመጸለይ ወደ ኋላ አንበል እኛ የምንጸልየው ባይገባንም በዙሪያችን ያሉት አጋንንቶች ገብቷቸው ይሸሻሉ።
@aleroe
…… ✍ አትማረኝ
--------------
በጣና ገዳማት ውስጥ የአቡነ አሳይ ዋሻ አለ በዚህ ዋሻ አንድ ያልተማረ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የማያውቅ ሰው ጸሎት ሲጸልይ አንድ አባት በጀልባ ተሳፍረው ይመጡና ያገኙታል።
ወደ ደሴቷም አረፍ ልበል ብለው ሲገቡ ያ ወጣት ሲጸልይ ይሰሙታል ቀረብ ብለው ቢያደምጡ ይህ ሰው የሚጸልየው "አትማረኝ" እያለ ነው።
እኝህ አባት በጣም ይደነግጡና እንዲህ ያለ ጸሎት አለ ወይ አትማረኝ የሚል ማን ነው ያስተማረህ ሲሉት አንድ መነኩሴ ነው ያስተማሩኝ አላቸው።
እሳቸውም ይህማ ሰይጣን ነው በመነኩሴ ተመስሎ ያስተማረህ እንጂ አትማረኝ ብሎ ጸሎት የለም ብለው "አቡነ ዘበሰማያትን" አስተማሩት። ይኽ ሰው እንደምንም ታግሎ አባታችን ሆይን ከተማረ በኋላ እኝህን አባት ያሰናብታቸዋል።
እሳቸውም በጀልባ ተሳፍረው መንገድ ሲጀምሩ ይኽ ወጣት ወደ ቀደመ በዓቱ ገብቶ መጸለይ ሲጀምር ያን ጸሎት ረሳው። ምን ነበር ያስተማሩኝ ብሎ ቢያስብ ጠፋበት። ከበዓቱም ሮጦ ወጥቶ በጀልባ ተሳፍረው የሚሄዱትን አባት አስቁሞ "ምን ብለው ነው ያስተምሩኝ?" ብሎ ጠየቃቸው እኝህም አባት ሲያዩት ውሃ ላይ ቆሟል፣ በውሃ ላይ ነው ሮጦ የመጣው አትኩረው ቢመለከቱት ውኃው ላይ እንደቆመ ነው።
"በል የእኔ ልጅ እንደቀድሞው አትማረኝ እያልክ ጸልይ" አሉት ይባላል።
ወጣቱ ባለማወቅ በሚጸልየው ጸሎት ውስጥ በቅቶ ነበር። እግዚአብሔር የሰማው ያለውን ሳይሆን የልቦናውን ነው።
የምንጸልየው ጸሎት የተዘበራረቀ ቢሆንም እንኳን እግዚአብሔር እያቃና ይሰማዋል። ስለዚህም ከመጸለይ ወደ ኋላ አንበል እኛ የምንጸልየው ባይገባንም በዙሪያችን ያሉት አጋንንቶች ገብቷቸው ይሸሻሉ።
@aleroe