Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)
በዜሮ ይባዛል!
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@aleroe
በዜሮ ይባዛል!
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ከዝሙት የዳነችው ብላቴና
ጫማ በመጠገን የሚተዳደር አንድ ሰው ነበር፡፡ ይህም ሰው ደም ግባቷ ያማረ፣ መልከ መልካም፣ የተወደደች፣ የተባረከች መንፈሳዊ ብላቴና ነበረችው፡፡ ውጫዊ ሰውነቷ ፈጽሞ ያማረ እንደሆነ ውስጣዊ ማንነቷም በትሕትና፣ በጸሎትና በጾም ያጌጠ ነው፡፡ ከታላላቁና ከታናናሹ ሁሉ ኃጢአት ርቃ፣ በፍጹም ሐሳቧ በልቧም እመቤታችንን ትወዳት ነበር፡፡ ስሟም ማርያም ይባል ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በእመቤታችን ስዕል ፊት ተቀምጣ “እመቤቴ ሆይ! ይህ ስም ላንቺ ብቻ ነው እንጂ ለእኔ አይገባኝም፡፡ አንቺ የንጹሐን ንጽሕት ነሽና አለች፡፡ በይቅርታሽ ድንግልናዬን ትጠብቂያት ዘንድ፣ የሰይጣንን ተንኮልን ሁሉ በፍቅርሽና በጸሎትሽ ከኔ ታርቂ ዘንድ የምእመናን አለኝታቸው ሆይ! እማጸንሻለሁ” ብላ እመቤታችንን ለመነቻት፡፡
የበጎ ነገር ጠላትና የአዳም ልጆችም ሁሉ ጠላት የሚሆን ሰይጣን ከዓላማዋ ሊያናውጻት ምክንያት አመጣባት፡፡ አንድ ፈረስ ያለው ሰው በመንገድ ሲሄድ ይህቺን ብላቴና አገኛት፡፡ ይህ ባለፈረስ አጅግ ባለ ጸጋና ገንዘቡም የበዛ ነው፡፡ ይህም ሰው ሴት ወዳጅ ስለሆነ ባያት ጊዜ ፈጽሞ ወደዳት፣ በሷም ፍቅር ተነደፈ፡፡
እርሱም ይህን የዝሙት ሐሳቡን እንድታስፈጽምለት አንዲት በጎ ምግባር የሌላትን ባነጋገሯና በሥራዋ የሰውን ልቡና የምታስት፣ ባንደበቷና በልቧ ውስጥ በሚኖር ሰይጣን ማሳትና በሥራዋ የሰውን ነፍስ ወደ ሲኦል የምታወርድ መሠሪት ሴት ወደ ርሷ ላከ፡፡ ያችን ደግ ብላቴና ክፉ በሚሆን ፊቷ ለማታለል ትነጋገራት ዘንድና ታግባባት ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ደግ ብላቴና ነገሯን በሰማች ጊዜ ሐሳቧንና የውስጧን ተንኮል ዐወቀች፡፡ ፊቷንም ታጠቁር ዘንድ ሥራዋንም ትነቅፍ ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ክፉ ሴት በብላቴናዋ መልስ እያዘነችና እየተከዘች ትታት ሄደች፡፡ ከዚህ በኋላ ለፈረሰኛው ሰው ሄዳ የኾነውን ነገረችው፡፡ እርሱም በዚች ብላቴና ፍቅር ምክንያት ልቡ እንደእሳት ተቃጥሎ ነበርና፣ እርሷን የሚያገኝበትን መንገድ ሁለተኛ እንድትመክረው ጠየቃት፡፡ ያቺም የሰይጣን የግብር ልጅ የኾነች ሴት እንዲህ አለችው፡፡ “ የዚያች ብላቴና አባት ድሃ ነው፣ አንተ ግን ባለጸጋ ነህና አስጠርተህ ከገንዘብህ ከፍለህ ስጠው፣ ያን ጊዜ ልጁን ፈጥኖ ያመጣልሃል” አለችው፡፡ እርሱም በክፉ ምክሯ ተመርቶ ያለችውን አደረገ፡፡ አባቷም ያለፍቃዷ ልጁን ይዞ እያዘነች እያለቀሰች ወደ ባለጸጋው ወሰዳት፡፡ ብላቴናዋም ሊታደጋት የሚችል ረዳትና ኃይል እንደሌለ ባወቀች ጊዜ አምላክን ወደ ወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደጸናች ክብርት እመቤታችን ጮኻ ለመነች፡፡ “ ሰውን የምትወጂ እመቤቴ ከእኔ አትራቂ” አለቻት፡፡ “የድኾች አለኝታቸው የምትሆኝ የተቸገሩትን የምታድኛቸው፣ ከዚያ ሰው ያንቺ ኃይል ይጸናል፣ ይበልጣል አድኚኝ እያለች ለመነቻት፡፡ ያም ባለጸጋ ብዙ ለቅሶዋንና ኀዘንዋን በሰማ ጊዜ “ለምን እንዲህ አድርገሽ ታዝኛለሽ፣ ታለቅሺያለሽ ኣላት” እኔስ ከሕጻነቴ ጀምሮ ድንግልናዬን ነፍሴን ለእመቤታችን ተስያለሁ አለችው፡፡ አንተም የድንግልናዬን ብጽዓት አፍርሰህ ብትወስደኝ በፈታሔ ጽቅ ልጀዋ ፊት በምትቆምበት በዕለተ ትንሳኤ ጊዜ ይችው ትፈርድብሃለች” አለችው፡፡
ፈረሰኛው ከዚያች ብላቴና አንደበት የእመቤታችን ስም ሲሰማ ፍጹም ፈርቶ እጀግ አዘነ ሰውነቱም ተንቀጠቀጠ፣ ደነገጠ፡፡ ያም ባለጸጋ ባመረ ቃልና በፍጹም ፍርሃት ልትመነኩሺ ትወጃለሽን አላት፡፡ ማገልገሏን የወደድኩ፣ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንን አገለግላት ዘንድ “ አዎ እወዳለሁ” አለችው፡፡ እኔ ብዙ ገንዘብ ሰጥቼ ወደ መበለታት ገዳም ወስጄ እሰጥሻለሁ፡፡ ዳግመኛም ልብሳቸውንና ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ መበለታት ገዳም ወስዶ ይህችን ብላቴና እንደናንተ ጠብቁዋት፡፡ እኔንም በጸሎታችሁ አትርሱ ብሎ አደራ አስጠበቃቸው፡፡ ዘወትርም ይጎበኛቸው ነበር፡፡ የሚጠብቃቸውንም ያህል ብዙ ገንዘብና ምግባቸውን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ተአምረ ማርያም ተአምር ፹፮
@aleroe
ከዝሙት የዳነችው ብላቴና
ጫማ በመጠገን የሚተዳደር አንድ ሰው ነበር፡፡ ይህም ሰው ደም ግባቷ ያማረ፣ መልከ መልካም፣ የተወደደች፣ የተባረከች መንፈሳዊ ብላቴና ነበረችው፡፡ ውጫዊ ሰውነቷ ፈጽሞ ያማረ እንደሆነ ውስጣዊ ማንነቷም በትሕትና፣ በጸሎትና በጾም ያጌጠ ነው፡፡ ከታላላቁና ከታናናሹ ሁሉ ኃጢአት ርቃ፣ በፍጹም ሐሳቧ በልቧም እመቤታችንን ትወዳት ነበር፡፡ ስሟም ማርያም ይባል ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በእመቤታችን ስዕል ፊት ተቀምጣ “እመቤቴ ሆይ! ይህ ስም ላንቺ ብቻ ነው እንጂ ለእኔ አይገባኝም፡፡ አንቺ የንጹሐን ንጽሕት ነሽና አለች፡፡ በይቅርታሽ ድንግልናዬን ትጠብቂያት ዘንድ፣ የሰይጣንን ተንኮልን ሁሉ በፍቅርሽና በጸሎትሽ ከኔ ታርቂ ዘንድ የምእመናን አለኝታቸው ሆይ! እማጸንሻለሁ” ብላ እመቤታችንን ለመነቻት፡፡
የበጎ ነገር ጠላትና የአዳም ልጆችም ሁሉ ጠላት የሚሆን ሰይጣን ከዓላማዋ ሊያናውጻት ምክንያት አመጣባት፡፡ አንድ ፈረስ ያለው ሰው በመንገድ ሲሄድ ይህቺን ብላቴና አገኛት፡፡ ይህ ባለፈረስ አጅግ ባለ ጸጋና ገንዘቡም የበዛ ነው፡፡ ይህም ሰው ሴት ወዳጅ ስለሆነ ባያት ጊዜ ፈጽሞ ወደዳት፣ በሷም ፍቅር ተነደፈ፡፡
እርሱም ይህን የዝሙት ሐሳቡን እንድታስፈጽምለት አንዲት በጎ ምግባር የሌላትን ባነጋገሯና በሥራዋ የሰውን ልቡና የምታስት፣ ባንደበቷና በልቧ ውስጥ በሚኖር ሰይጣን ማሳትና በሥራዋ የሰውን ነፍስ ወደ ሲኦል የምታወርድ መሠሪት ሴት ወደ ርሷ ላከ፡፡ ያችን ደግ ብላቴና ክፉ በሚሆን ፊቷ ለማታለል ትነጋገራት ዘንድና ታግባባት ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ደግ ብላቴና ነገሯን በሰማች ጊዜ ሐሳቧንና የውስጧን ተንኮል ዐወቀች፡፡ ፊቷንም ታጠቁር ዘንድ ሥራዋንም ትነቅፍ ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ክፉ ሴት በብላቴናዋ መልስ እያዘነችና እየተከዘች ትታት ሄደች፡፡ ከዚህ በኋላ ለፈረሰኛው ሰው ሄዳ የኾነውን ነገረችው፡፡ እርሱም በዚች ብላቴና ፍቅር ምክንያት ልቡ እንደእሳት ተቃጥሎ ነበርና፣ እርሷን የሚያገኝበትን መንገድ ሁለተኛ እንድትመክረው ጠየቃት፡፡ ያቺም የሰይጣን የግብር ልጅ የኾነች ሴት እንዲህ አለችው፡፡ “ የዚያች ብላቴና አባት ድሃ ነው፣ አንተ ግን ባለጸጋ ነህና አስጠርተህ ከገንዘብህ ከፍለህ ስጠው፣ ያን ጊዜ ልጁን ፈጥኖ ያመጣልሃል” አለችው፡፡ እርሱም በክፉ ምክሯ ተመርቶ ያለችውን አደረገ፡፡ አባቷም ያለፍቃዷ ልጁን ይዞ እያዘነች እያለቀሰች ወደ ባለጸጋው ወሰዳት፡፡ ብላቴናዋም ሊታደጋት የሚችል ረዳትና ኃይል እንደሌለ ባወቀች ጊዜ አምላክን ወደ ወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደጸናች ክብርት እመቤታችን ጮኻ ለመነች፡፡ “ ሰውን የምትወጂ እመቤቴ ከእኔ አትራቂ” አለቻት፡፡ “የድኾች አለኝታቸው የምትሆኝ የተቸገሩትን የምታድኛቸው፣ ከዚያ ሰው ያንቺ ኃይል ይጸናል፣ ይበልጣል አድኚኝ እያለች ለመነቻት፡፡ ያም ባለጸጋ ብዙ ለቅሶዋንና ኀዘንዋን በሰማ ጊዜ “ለምን እንዲህ አድርገሽ ታዝኛለሽ፣ ታለቅሺያለሽ ኣላት” እኔስ ከሕጻነቴ ጀምሮ ድንግልናዬን ነፍሴን ለእመቤታችን ተስያለሁ አለችው፡፡ አንተም የድንግልናዬን ብጽዓት አፍርሰህ ብትወስደኝ በፈታሔ ጽቅ ልጀዋ ፊት በምትቆምበት በዕለተ ትንሳኤ ጊዜ ይችው ትፈርድብሃለች” አለችው፡፡
ፈረሰኛው ከዚያች ብላቴና አንደበት የእመቤታችን ስም ሲሰማ ፍጹም ፈርቶ እጀግ አዘነ ሰውነቱም ተንቀጠቀጠ፣ ደነገጠ፡፡ ያም ባለጸጋ ባመረ ቃልና በፍጹም ፍርሃት ልትመነኩሺ ትወጃለሽን አላት፡፡ ማገልገሏን የወደድኩ፣ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንን አገለግላት ዘንድ “ አዎ እወዳለሁ” አለችው፡፡ እኔ ብዙ ገንዘብ ሰጥቼ ወደ መበለታት ገዳም ወስጄ እሰጥሻለሁ፡፡ ዳግመኛም ልብሳቸውንና ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ መበለታት ገዳም ወስዶ ይህችን ብላቴና እንደናንተ ጠብቁዋት፡፡ እኔንም በጸሎታችሁ አትርሱ ብሎ አደራ አስጠበቃቸው፡፡ ዘወትርም ይጎበኛቸው ነበር፡፡ የሚጠብቃቸውንም ያህል ብዙ ገንዘብና ምግባቸውን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ተአምረ ማርያም ተአምር ፹፮
@aleroe
ኤልሮኢ:
የካቲት 27/06/2012 ዓ.ም
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ
መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ
👉 ዲያቆን
📖 ሮሜ. 6፥5 ወእመሰኬ ተመሰልናሁ በሞቱ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 2፥21 ወበእንተ ዝንቱ ተጸዋዕክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 10÷36 ወፈነወ ቃሎ ለደቂቀ እስራኤል ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 21/22፥16
----------------
ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 55/56፥1
----------------
ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ ወኵሎ አሚረ አሥርሐኒ ቀትል ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ ዓሚረ በኑኀ ዕለት
ትርጉም
-------------
1:- ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ
2:- አቤቱ፥ ሰው ረግጦኛልና ማረኝ፤ ሁልጊዜም በሰልፍ አስጨንቆኛል
📖 ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል 19 ÷ 16 - 30
📖 ቅዳሴ
ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
የካቲት 27/06/2012 ዓ.ም
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ
መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ
👉 ዲያቆን
📖 ሮሜ. 6፥5 ወእመሰኬ ተመሰልናሁ በሞቱ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 2፥21 ወበእንተ ዝንቱ ተጸዋዕክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 10÷36 ወፈነወ ቃሎ ለደቂቀ እስራኤል ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 21/22፥16
----------------
ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 55/56፥1
----------------
ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ ወኵሎ አሚረ አሥርሐኒ ቀትል ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ ዓሚረ በኑኀ ዕለት
ትርጉም
-------------
1:- ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ
2:- አቤቱ፥ ሰው ረግጦኛልና ማረኝ፤ ሁልጊዜም በሰልፍ አስጨንቆኛል
📖 ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል 19 ÷ 16 - 30
📖 ቅዳሴ
ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ምኩራብ
ምኩራብ የአብይ ጾም ሶስተኛው ሳምንት ነው።
ምኩራብ የአይሁዳውያን ቤተ መቅደስ ሲሆን
ይሄ ሳምንት ምኩራብ የተባለው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ
የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡
ማቴ ፳፩፥፲፪―፲፬ እንዲህ ይላል«ኢየሱስ ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ የሚሸጡትና የሚገዙትንም ኹሉ አወጣ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጪዎችን ወንበሮች ገለበጠና ቤቴ የፀሎት ቤት ትባላለች
ተብሎ ተፅፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችውት አላቸው።በመቅደስም እውሮችና አንካሳዎች ወደ ርሱ ቀረቡና ፈወሳቸው።»
@aleroe
ምኩራብ
ምኩራብ የአብይ ጾም ሶስተኛው ሳምንት ነው።
ምኩራብ የአይሁዳውያን ቤተ መቅደስ ሲሆን
ይሄ ሳምንት ምኩራብ የተባለው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ
የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡
ማቴ ፳፩፥፲፪―፲፬ እንዲህ ይላል«ኢየሱስ ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ የሚሸጡትና የሚገዙትንም ኹሉ አወጣ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጪዎችን ወንበሮች ገለበጠና ቤቴ የፀሎት ቤት ትባላለች
ተብሎ ተፅፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችውት አላቸው።በመቅደስም እውሮችና አንካሳዎች ወደ ርሱ ቀረቡና ፈወሳቸው።»
@aleroe
ኤልሮኢ:
ጌታችን አንጽሖተ ቤተ መቅደስን ኹለት ጊዜ መፈጸሙ በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ አንደኛው በማቴዎስ 21 ላይ የሚገኝ ታሪክ ሲኾን፡ በሆሣዕና ጊዜ በስፋት የሚነሣ ነው፡፡ ሌላኛው በዮሐንስ 2 ላይ የሚገኘው ነው፡፡ በዚህኛው ክፍል ላይ ጌታችን የፈጸመውን የአንጽሖት ግብር በ3 ዋና ዋና ንዑስ ድርጊቶች ከፍለን መማር እንችላለን፡፡
1ኛ. ጌታችን ‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ››፡፡(ዮሐ.2፡13-14)፡፡ በመቅደስ የሚነግዱትንም አየ፡፡
2ኛ. ‹‹የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።›› (ዮሐ.2፡15-16)፡፡
3ኛ. ይህንን ያዩት አይሁድም በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ›› አላቸው፡፡
ልብ በሉ! ማንጻትን የሚያስብ ሰው ኹሉ እነዚህን ሦስት ነገሮች መፈጸም አለበት፡፡ ለአንጽሖት እጅግ አስፈላጊ ነጥቦች ናቸው፡፡
1ኛ. ማየት
የመጀመሪያው፡ ልናነጻው ያሰብነውን ነገር ኼዶ ማየት ነው፡፡ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት ማንጻት አይቻልም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊያነጻ የሚፈልግ ኹሉ፡ ቤተ ክርስቲያንን በደንብ ሊያያት፣ ወደ እርሷ ኼዶ ሊያገኛት፡ ሊያውቃትና ሊረዳት ይገባል፡፡ የዚያን ጊዜ በሬ ሻጮቹ፣ በግ ነጋዴዎቹና ርግብ ሻጮቹ ቁልጭ ብለው ይታዩታል፡፡ ኢትዮጵያንም ሊያነጻ የሚወድ በቅድሚያ ይቅረባት፣ በደንብ ይያት፣ ነጋዴዎቹ የቱጋ እንደ መሸጉ ይለይ፡፡ ራሱንም ሊያነጻ የሚወድ ቢኾን እንኳ፡ ‹‹ካህን›› ወይም ‹‹የንስሐ አባት›› በተባሉ መስታወቶች ራሱን በቅድሚያ በደንብ ማየት አለበት፡፡ ‹‹ራስህን ለካህን አሳይ፥ … ስለ መንጻትህ … መሥዋዕት አቅርብ›› እንዲል፡፡ (ሉቃ.5፡14)፡፡ ካህናት ‹‹አዕይንተ እግዚአብሔር / የእግዚአብሔር ዐይኖች›› ይባላሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ፣ ሀገርም ፣ እኛም በዚህ ዐይን ካልታየን ዕድፋችን አይለይምና መንጻት ከባድ ይኾናል፡፡
2ኛ. ማጽዳት
ጌታችን በመቅደስ ውስጥ የሚሠራውን ካየ በኋላ፡ በቅድሚያ ማጽጃውን ጅራፍ አዘጋጀ፡፡ ከዚያም በሬና በጎችን በጅራፍ አባረረ፤ ጅራፍ የማይችሉትን ርግቦችን ግን ባለቤቶቻቸው እንዲያስወጧቸው አዘዘ፡፡
ለቆሻሻ ኹሉ ማጽጃው አንድ አይደለም፡፡ መጥረጊያ ኹሉን አያጸዳም፡፡ መወልወያም እንዲሁ፡፡ ልብስ በሚታጠብበት የምግብ ዕቃ፣ ዕቃ በሚታጠብበትም ቤት አይታጠብም፡፡ ስለዚህ ለየትኛው ቆሻሻ ምን ዓይነት ማጽጃ እንደሚያስፈልግ በደንብ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የበሬውን ማጽጃ ለርግብ የሚጠቀም አጽጂ፡ በርግጥም አጽጂ ሊባል አይችልም፡፡ በባሕርይዋ ንጽሕት በኾነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሰዎች ምክንያት ጉድለት ቢገኝ፡ ‹‹ይህ የእነ እገሌ ሥራ ነው፡፡ ጳጳሱ እያሉ፣ መምህሩ እያሉ፣ ቄሱ እያሉ… እኔ ምን ቤት ነኝ›› አይባልም፡፡ ጉድለቱን ሥርዐት በሚፈቅደው መልኩ ለማስወገድ መጣር እንጂ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ‹‹የአባታችን ቤት›› ናት፡፡ የአባት ቤት ውስጥ ደግሞ ቆሻሻ ታይቶ አይታለፍም፡፡ ስለዚህ የምንወስደው ኹለተኛ ትምህርት አይቶ እንዳላየ ዝም ማለት ሳይኾን ለተግባር መንቀሳቀስን ነው፡፡
ጠያቂዎች ፣ ጌታችን ነጋዴዎቹን ሲያባርር፡ አይሁድ በጠያቂነት ተቃውመው ተነሥተው ነበር፡፡ በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ሲጠይቁት ነበር፡፡ እርሱም የጠየቁትን ምልክት ነገራቸው፡፡ እነርሱ ግን በሌላ ተረዱት፡፡ ‹‹ቤተ መቅደስ›› ሲል እነርሱ ሲሠራ ዓመታትን ስለ ፈጀው ቤተ መቅደስ ያስቡ ነበር፤ ‹‹እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር››፡፡ (ዮሐ.2፡21)፡፡
ማንጻት ስትጀምሩ፣ መልካም ሥራን ‹ሀ› ብላችሁ ስትወጥኑ ጠያቂና አድካሚ ተቃዋሚ አታጡም፡፡ ጠያቂውን ዝም የሚያሰኝ፣ ተቃዋሚውንም የሚቋቋም ዝግጅት ከሌላችሁ የጸዳው ቤት ተመልሶ መቆሸሹ አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሥራው እያቆሸሹ መልሶ ማጽዳት እንዳይኾን እንዲህ ዓይነት ዝግጅትም ማድረግ ይገባል፡፡ ለሚጠይቁና ለሚቃወሙ ተገቢውን ምላሽ መስጠት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ኹኑ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (1ጴጥ.3፡15)፡፡ ይህ ደግሞ ካለ በቂ ትምህርትና ጸሎት አይኾንም፡፡
የሚገርመው ግን ተቃዋሚዎች ሥራቸው መቃወም ብቻ ስለ ኾነ እንኳን ሳትመልሱ ይቅርና በቂ ምላሽን ብትሰጡም ሊያጣምሙት ይችላሉ፡፡ ስለ ሰውነታችሁ እያወራችሁላቸው ስለ ሕንጻ አወራ ብለው ተቃውሟቸውን ይገፉበታል፡፡ የዚህን ጊዜ ‹‹ውሾች ይጮኻሉ፡ ግመሎቹ ግን ይጓዛሉ›› ብሎ መቀጠል ተገቢ ነው፡፡
@aleroe
ጌታችን አንጽሖተ ቤተ መቅደስን ኹለት ጊዜ መፈጸሙ በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ አንደኛው በማቴዎስ 21 ላይ የሚገኝ ታሪክ ሲኾን፡ በሆሣዕና ጊዜ በስፋት የሚነሣ ነው፡፡ ሌላኛው በዮሐንስ 2 ላይ የሚገኘው ነው፡፡ በዚህኛው ክፍል ላይ ጌታችን የፈጸመውን የአንጽሖት ግብር በ3 ዋና ዋና ንዑስ ድርጊቶች ከፍለን መማር እንችላለን፡፡
1ኛ. ጌታችን ‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ››፡፡(ዮሐ.2፡13-14)፡፡ በመቅደስ የሚነግዱትንም አየ፡፡
2ኛ. ‹‹የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።›› (ዮሐ.2፡15-16)፡፡
3ኛ. ይህንን ያዩት አይሁድም በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ›› አላቸው፡፡
ልብ በሉ! ማንጻትን የሚያስብ ሰው ኹሉ እነዚህን ሦስት ነገሮች መፈጸም አለበት፡፡ ለአንጽሖት እጅግ አስፈላጊ ነጥቦች ናቸው፡፡
1ኛ. ማየት
የመጀመሪያው፡ ልናነጻው ያሰብነውን ነገር ኼዶ ማየት ነው፡፡ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት ማንጻት አይቻልም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊያነጻ የሚፈልግ ኹሉ፡ ቤተ ክርስቲያንን በደንብ ሊያያት፣ ወደ እርሷ ኼዶ ሊያገኛት፡ ሊያውቃትና ሊረዳት ይገባል፡፡ የዚያን ጊዜ በሬ ሻጮቹ፣ በግ ነጋዴዎቹና ርግብ ሻጮቹ ቁልጭ ብለው ይታዩታል፡፡ ኢትዮጵያንም ሊያነጻ የሚወድ በቅድሚያ ይቅረባት፣ በደንብ ይያት፣ ነጋዴዎቹ የቱጋ እንደ መሸጉ ይለይ፡፡ ራሱንም ሊያነጻ የሚወድ ቢኾን እንኳ፡ ‹‹ካህን›› ወይም ‹‹የንስሐ አባት›› በተባሉ መስታወቶች ራሱን በቅድሚያ በደንብ ማየት አለበት፡፡ ‹‹ራስህን ለካህን አሳይ፥ … ስለ መንጻትህ … መሥዋዕት አቅርብ›› እንዲል፡፡ (ሉቃ.5፡14)፡፡ ካህናት ‹‹አዕይንተ እግዚአብሔር / የእግዚአብሔር ዐይኖች›› ይባላሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ፣ ሀገርም ፣ እኛም በዚህ ዐይን ካልታየን ዕድፋችን አይለይምና መንጻት ከባድ ይኾናል፡፡
2ኛ. ማጽዳት
ጌታችን በመቅደስ ውስጥ የሚሠራውን ካየ በኋላ፡ በቅድሚያ ማጽጃውን ጅራፍ አዘጋጀ፡፡ ከዚያም በሬና በጎችን በጅራፍ አባረረ፤ ጅራፍ የማይችሉትን ርግቦችን ግን ባለቤቶቻቸው እንዲያስወጧቸው አዘዘ፡፡
ለቆሻሻ ኹሉ ማጽጃው አንድ አይደለም፡፡ መጥረጊያ ኹሉን አያጸዳም፡፡ መወልወያም እንዲሁ፡፡ ልብስ በሚታጠብበት የምግብ ዕቃ፣ ዕቃ በሚታጠብበትም ቤት አይታጠብም፡፡ ስለዚህ ለየትኛው ቆሻሻ ምን ዓይነት ማጽጃ እንደሚያስፈልግ በደንብ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የበሬውን ማጽጃ ለርግብ የሚጠቀም አጽጂ፡ በርግጥም አጽጂ ሊባል አይችልም፡፡ በባሕርይዋ ንጽሕት በኾነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሰዎች ምክንያት ጉድለት ቢገኝ፡ ‹‹ይህ የእነ እገሌ ሥራ ነው፡፡ ጳጳሱ እያሉ፣ መምህሩ እያሉ፣ ቄሱ እያሉ… እኔ ምን ቤት ነኝ›› አይባልም፡፡ ጉድለቱን ሥርዐት በሚፈቅደው መልኩ ለማስወገድ መጣር እንጂ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ‹‹የአባታችን ቤት›› ናት፡፡ የአባት ቤት ውስጥ ደግሞ ቆሻሻ ታይቶ አይታለፍም፡፡ ስለዚህ የምንወስደው ኹለተኛ ትምህርት አይቶ እንዳላየ ዝም ማለት ሳይኾን ለተግባር መንቀሳቀስን ነው፡፡
ጠያቂዎች ፣ ጌታችን ነጋዴዎቹን ሲያባርር፡ አይሁድ በጠያቂነት ተቃውመው ተነሥተው ነበር፡፡ በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ሲጠይቁት ነበር፡፡ እርሱም የጠየቁትን ምልክት ነገራቸው፡፡ እነርሱ ግን በሌላ ተረዱት፡፡ ‹‹ቤተ መቅደስ›› ሲል እነርሱ ሲሠራ ዓመታትን ስለ ፈጀው ቤተ መቅደስ ያስቡ ነበር፤ ‹‹እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር››፡፡ (ዮሐ.2፡21)፡፡
ማንጻት ስትጀምሩ፣ መልካም ሥራን ‹ሀ› ብላችሁ ስትወጥኑ ጠያቂና አድካሚ ተቃዋሚ አታጡም፡፡ ጠያቂውን ዝም የሚያሰኝ፣ ተቃዋሚውንም የሚቋቋም ዝግጅት ከሌላችሁ የጸዳው ቤት ተመልሶ መቆሸሹ አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሥራው እያቆሸሹ መልሶ ማጽዳት እንዳይኾን እንዲህ ዓይነት ዝግጅትም ማድረግ ይገባል፡፡ ለሚጠይቁና ለሚቃወሙ ተገቢውን ምላሽ መስጠት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ኹኑ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (1ጴጥ.3፡15)፡፡ ይህ ደግሞ ካለ በቂ ትምህርትና ጸሎት አይኾንም፡፡
የሚገርመው ግን ተቃዋሚዎች ሥራቸው መቃወም ብቻ ስለ ኾነ እንኳን ሳትመልሱ ይቅርና በቂ ምላሽን ብትሰጡም ሊያጣምሙት ይችላሉ፡፡ ስለ ሰውነታችሁ እያወራችሁላቸው ስለ ሕንጻ አወራ ብለው ተቃውሟቸውን ይገፉበታል፡፡ የዚህን ጊዜ ‹‹ውሾች ይጮኻሉ፡ ግመሎቹ ግን ይጓዛሉ›› ብሎ መቀጠል ተገቢ ነው፡፡
@aleroe
ቀኑ መጋቢት 5 ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤
“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው
መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ
ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን
አልተቻላቸውም አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ
የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን
ጽሕሙ አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ
ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ
ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር
ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።“ወዳጄ
ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል #ቃል_ኪዳን_እገባልሃለው_ስምህን_የጠራ_መታሰቢያህን_ያደረገውን_እጣን_ቋጥሮ_ግብር
ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት
መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም “#አቤቱ_ጌታ_ሆይ_የኢትዮጰያን
ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም
ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም
ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ
ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤
ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ
የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ
ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን
ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን መጋቢት 5
ሩጫውን ጨረሰ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
(መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት)
@aleroe
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤
“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው
መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ
ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን
አልተቻላቸውም አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ
የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን
ጽሕሙ አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ
ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ
ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር
ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።“ወዳጄ
ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል #ቃል_ኪዳን_እገባልሃለው_ስምህን_የጠራ_መታሰቢያህን_ያደረገውን_እጣን_ቋጥሮ_ግብር
ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት
መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም “#አቤቱ_ጌታ_ሆይ_የኢትዮጰያን
ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም
ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም
ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ
ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤
ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ
የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ
ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን
ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን መጋቢት 5
ሩጫውን ጨረሰ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
(መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት)
@aleroe
........... ሰበር ዜና
የኢትዬጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በቅዱስ ፓትሪያሪኩ
አማካይነት #ከዛሬ_እስከ_ትንሳኤ ድረስ የሚቆይ ሰደድ እሳት የሆነውን
ወረርሽኝ በሽታ ፈጣሪ እንዲያቆምልን #ፀሎተ_ምህላ አውጃለች ።
@aleroe
የኢትዬጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በቅዱስ ፓትሪያሪኩ
አማካይነት #ከዛሬ_እስከ_ትንሳኤ ድረስ የሚቆይ ሰደድ እሳት የሆነውን
ወረርሽኝ በሽታ ፈጣሪ እንዲያቆምልን #ፀሎተ_ምህላ አውጃለች ።
@aleroe
ማር፣ፌጦ፣ጤና አዳም፣ነጭ ሽንኩርት አንድ ላይ ፈጭታቹ አንድ ማንኪያ ዋጡ የሚል መልክት ሰዉን እያሸበረ ይገኛል።
መልክቱ ከአባቶች የተላከ ነው የሚሉት ነገር አለ። ነገር ግን የተኛቹ አባቶች እንደተላከ ግልፅ የወጣ ነገር የለም።
የተባለውን መተግበር ክፋት የለው
ለምን ? ከተባለ የተጠቀሱት ለሰውነታችን ገንቢ እንጂ ጎጂ አይደለም ነገር ግን እኚ መዳኒት ናቸው የተባሉት ንጥረ ነገሮች ከኮሮና ቫይረስ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም።
#አትሸወዱ #አትሸበሩ
ዛሬ የሀይማኖት አባቶች መግለጫ በሰጡበት ወቅት በጥሞና ጤና ሚኒስትር የሚለውን ተከታተሉ ማለታቸው ይታወሳል ስለዚህም አባቶቻችን ያሉትን ጤና ሚንስትርን እንከታተል።
ሆኖም ኮሮና ቫይረስ ለመከላከል #እጅን_መታጠብ አንደኛው እና #ዋነኛው_መንገድ ነው።
#እጃችሁን_ታጠቡ
#ፀልዩ
#ስገዱ
@aleroe
መልክቱ ከአባቶች የተላከ ነው የሚሉት ነገር አለ። ነገር ግን የተኛቹ አባቶች እንደተላከ ግልፅ የወጣ ነገር የለም።
የተባለውን መተግበር ክፋት የለው
ለምን ? ከተባለ የተጠቀሱት ለሰውነታችን ገንቢ እንጂ ጎጂ አይደለም ነገር ግን እኚ መዳኒት ናቸው የተባሉት ንጥረ ነገሮች ከኮሮና ቫይረስ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም።
#አትሸወዱ #አትሸበሩ
ዛሬ የሀይማኖት አባቶች መግለጫ በሰጡበት ወቅት በጥሞና ጤና ሚኒስትር የሚለውን ተከታተሉ ማለታቸው ይታወሳል ስለዚህም አባቶቻችን ያሉትን ጤና ሚንስትርን እንከታተል።
ሆኖም ኮሮና ቫይረስ ለመከላከል #እጅን_መታጠብ አንደኛው እና #ዋነኛው_መንገድ ነው።
#እጃችሁን_ታጠቡ
#ፀልዩ
#ስገዱ
@aleroe
ኤልሮኢ:
መፃጉዕ
መፃጉዕ የአብይ ፆም አራተኛው ሳምንት ነው። በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችንድውያንንስለመፈወሱየሚታሰብበት ሳምንት ነው።በዮሐ ፭፥፪―፲፩ እንዲህ ተፅፎ እናገኛለን«በኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቅያ ነበረች አምስት መመላለሻም ነበረባት በእነዚህ ውስጥ የውሀውን መንቀሳቀስ እየጠበቁ በሽተኛዎችና እውሮች አንካሳዎችም ሰውነታቸውም የሰለለ ብዙ ህዝብ ይተኙ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቅያቱ ወርዶ ውሀውን ያናውጥ ነበርና እንግዲህ ከውሀው መናወጥ በኋላ መጀመርያ የገባው ከማናቸውም ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር በዚያም ከሰላሳ ስምንት አመት ዠምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበር።እየሱስ ይህ ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ እስከ አሁንብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበር አውቆ ልትድን ትወዳለህ አለው። ድውዩም ጌታ ሆይ ውሀው በተናወጠ ጊዜ መጠመቅያቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።እየሱስም ተነስና አልጋህ ተሸከም ሂድ አለው።ያም ቀን ሰንበት ነበር።»
ፈጣሪ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን።
@aleroe
መፃጉዕ
መፃጉዕ የአብይ ፆም አራተኛው ሳምንት ነው። በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችንድውያንንስለመፈወሱየሚታሰብበት ሳምንት ነው።በዮሐ ፭፥፪―፲፩ እንዲህ ተፅፎ እናገኛለን«በኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቅያ ነበረች አምስት መመላለሻም ነበረባት በእነዚህ ውስጥ የውሀውን መንቀሳቀስ እየጠበቁ በሽተኛዎችና እውሮች አንካሳዎችም ሰውነታቸውም የሰለለ ብዙ ህዝብ ይተኙ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቅያቱ ወርዶ ውሀውን ያናውጥ ነበርና እንግዲህ ከውሀው መናወጥ በኋላ መጀመርያ የገባው ከማናቸውም ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር በዚያም ከሰላሳ ስምንት አመት ዠምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበር።እየሱስ ይህ ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ እስከ አሁንብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበር አውቆ ልትድን ትወዳለህ አለው። ድውዩም ጌታ ሆይ ውሀው በተናወጠ ጊዜ መጠመቅያቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።እየሱስም ተነስና አልጋህ ተሸከም ሂድ አለው።ያም ቀን ሰንበት ነበር።»
ፈጣሪ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን።
@aleroe
ኤልሮኢ:
እኔ መፃጉ ነኝ
ለብዙ ዓመት በአልጋ ላይ የነበርኩ፣
በሥጋ በሽታ በህመም የደከምኩ፣
በአጭር ተቀጭቼ ሳላአብብ የረገፍኩ፣
ፈውሴን የሚናፍቅ ወገን ያልነበረኝ፣
ውሃው ሲነዋወጥ ጠልቆ የሚያወጣኝ፣
ከርታታ ባይተዋር ውዳቂ ነበርኩኝ።
ከለዕታት አንድ ቀን በዚያ ሲያልፍ ጌታዬ፣
ሊፈውሰኝ ወዶ ገብቶ ከጎጆዬ፣
በቃሉ አድኖኝ ቆሜ ሄድኩኝ በዕግሬ፣
አይሁዳዊ እነቴ እንዳይቀር የዘሬ፣
ምስጋና ለማቅረብ ባይታደል ልቤ፣
ተንኮል በኔ ነግሶ ክፋትን ደርቤ፣
ሰንበትን በመሻር የማረኝ ይሄ ነው በማለት፣
ብድሩን ስከፍለው ጥፊን መለስኩለት፣
የወዳጄ ጠላት እኔ መፃጉ ነኝ፣
በሁዳዴ ፆም ውስጥ የምታስታውሱኝ።
@aleroe
እኔ መፃጉ ነኝ
ለብዙ ዓመት በአልጋ ላይ የነበርኩ፣
በሥጋ በሽታ በህመም የደከምኩ፣
በአጭር ተቀጭቼ ሳላአብብ የረገፍኩ፣
ፈውሴን የሚናፍቅ ወገን ያልነበረኝ፣
ውሃው ሲነዋወጥ ጠልቆ የሚያወጣኝ፣
ከርታታ ባይተዋር ውዳቂ ነበርኩኝ።
ከለዕታት አንድ ቀን በዚያ ሲያልፍ ጌታዬ፣
ሊፈውሰኝ ወዶ ገብቶ ከጎጆዬ፣
በቃሉ አድኖኝ ቆሜ ሄድኩኝ በዕግሬ፣
አይሁዳዊ እነቴ እንዳይቀር የዘሬ፣
ምስጋና ለማቅረብ ባይታደል ልቤ፣
ተንኮል በኔ ነግሶ ክፋትን ደርቤ፣
ሰንበትን በመሻር የማረኝ ይሄ ነው በማለት፣
ብድሩን ስከፍለው ጥፊን መለስኩለት፣
የወዳጄ ጠላት እኔ መፃጉ ነኝ፣
በሁዳዴ ፆም ውስጥ የምታስታውሱኝ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
መጋቢት 12/07/12
#መዝሙር_ዘደብረ_ዘይት
"እንዘ ይነብር"
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1 ተሰሎ 4÷13-ፍ.ም
ን/ዲ 2ጴጥ 3÷7-15
ን/ካ ግብ፡ሐዋ24÷1-22
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 49÷3
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ
#ትርጒም፦
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ማቴ ፳፬፥፩ -፴፮
ቅዳሴ፦ ዘአትናቴዎስ
@aleroe
መጋቢት 12/07/12
#መዝሙር_ዘደብረ_ዘይት
"እንዘ ይነብር"
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1 ተሰሎ 4÷13-ፍ.ም
ን/ዲ 2ጴጥ 3÷7-15
ን/ካ ግብ፡ሐዋ24÷1-22
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 49÷3
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ
#ትርጒም፦
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ማቴ ፳፬፥፩ -፴፮
ቅዳሴ፦ ዘአትናቴዎስ
@aleroe
ኤልሮኢ:
ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ
ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ
መጣሁ ከደጅሽ ሱባዔ ገባሁ
ማን አፍሮ ያውቃል በአንቺ ለምኖ
በኪዳንኪ ተማህጸኖ
ለነፍሴ ዕረፍቷ ታዛ መጠጊያ
ካንቺ ተገኝቷል የሞቴ መውጊያ
በሰላምታሽ ድምፅ ተባርኳል ቤቴ
የጌታዬ እናት ለእኔም እናቴ
ማርያም ኵኒ ለሕይወትየ ጸወኖ
እስመ ተማሕጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
ቀንን ስናፍቅ በሌሊት ሆኜ
አላተረፍኩም በሰው ታምኜ
ቁልፉ ልጅሽ ነው ለቋጠሮዬ
አሳስሰሽልኝ አልፏል ስቃዬ
ኪዳነምሕረት ኵኒ ለልቡናዬ ብርሃኖ
እስመ ተማህጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
ጉልበቴ ዝሎ ቀልዬ ሳለሁ
በኪዳን ጥላሽ ተስፋ አግኝቻለሁ
ደጅሽ መጥቼ ኃይሌ ታደሰ
ያሳዳጆቼ ምክር ፈረሰ
ወላዲተ አምላክ ኵኒ ለእርቃንዬ ክዳኑ
እስመ ተማህጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
የዝናቡ ምንጭ ፈጣን ደመና
ከሴቶች ሁሉ ክብርሽ ገናና
አንድያ ልጅሽ ወይን አድርጎኛል
ከትላንት ይልቅ ዛሬ ባርኮኛል
@aleroe
ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ
ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ
መጣሁ ከደጅሽ ሱባዔ ገባሁ
ማን አፍሮ ያውቃል በአንቺ ለምኖ
በኪዳንኪ ተማህጸኖ
ለነፍሴ ዕረፍቷ ታዛ መጠጊያ
ካንቺ ተገኝቷል የሞቴ መውጊያ
በሰላምታሽ ድምፅ ተባርኳል ቤቴ
የጌታዬ እናት ለእኔም እናቴ
ማርያም ኵኒ ለሕይወትየ ጸወኖ
እስመ ተማሕጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
ቀንን ስናፍቅ በሌሊት ሆኜ
አላተረፍኩም በሰው ታምኜ
ቁልፉ ልጅሽ ነው ለቋጠሮዬ
አሳስሰሽልኝ አልፏል ስቃዬ
ኪዳነምሕረት ኵኒ ለልቡናዬ ብርሃኖ
እስመ ተማህጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
ጉልበቴ ዝሎ ቀልዬ ሳለሁ
በኪዳን ጥላሽ ተስፋ አግኝቻለሁ
ደጅሽ መጥቼ ኃይሌ ታደሰ
ያሳዳጆቼ ምክር ፈረሰ
ወላዲተ አምላክ ኵኒ ለእርቃንዬ ክዳኑ
እስመ ተማህጸንኩ አንሰ ተማሕጸኖ
በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ ንሰግድ ለኪ
የዝናቡ ምንጭ ፈጣን ደመና
ከሴቶች ሁሉ ክብርሽ ገናና
አንድያ ልጅሽ ወይን አድርጎኛል
ከትላንት ይልቅ ዛሬ ባርኮኛል
@aleroe
ኤልሮኢ:
መጋቢት 13/07/12
#መዝሙር_ዘደብረ_ዘይት
"እንዘ ይነብር"
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነብ
መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1 ተሰሎ 4÷13-ፍ.ም
ን/ዲ 2ጴጥ 3÷7-15
ን/ካ ግብ፡ሐዋ24÷1-22
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 49÷3
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ
#ትርጒም፦
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ማቴ ፳፬፥፩ -፴፮
ቅዳሴ፦ ዘአትናቴዎስ
@aleroe
መጋቢት 13/07/12
#መዝሙር_ዘደብረ_ዘይት
"እንዘ ይነብር"
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነብ
መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1 ተሰሎ 4÷13-ፍ.ም
ን/ዲ 2ጴጥ 3÷7-15
ን/ካ ግብ፡ሐዋ24÷1-22
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 49÷3
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ
#ትርጒም፦
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ማቴ ፳፬፥፩ -፴፮
ቅዳሴ፦ ዘአትናቴዎስ
@aleroe
ኤልሮኢ:
ደብረ ዘይት
ደብረ ዘይት የዐብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት
ደብረ ዘይት ማለት ቃሉ “ደብር” ሲል ተራራ ሲሆን “ዘይት” ሲል የወይራ ዛፍን ያመለከታል። ባጠቃላይ ደብረ ዘይት የወይራ ዛፍ (የዘይት ዛፍ) የበዛበት ተራራ ማለት ነው። ቦታው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ከጎለጎታ (ቀራንዮ) ተራራ በስተምስራቅ በግምት ፪ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ታላቅ ተራራ ነው። በሁለቱ ተራሮች መካከል ጌቴሴማኒ የሚባለው ለምለም ስፍራ ይኸውም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመቃብር ስፍራ ይገኛል።
የደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ የሚያድርበት፣ የሚያስተምርበት፣ ውሎ የሚያርፍበት ሥፍራ ነው። ሉቃ ፳፩፥ ፴፯፣ ሉቃ ፳፪፥ ፴፱፣ ዮሐ ፰፥ ፩ ከዚሁ ተራራ ላይ ነው ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው። ኋላም በዳግም ምጽአት እዚሁ ተራራ ላይ ነው ለፍርድ የሚመጣው። /ሐዋ ፩፥፲፫/። "
" በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም ምፅአቱ ) ይሰበካል። ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸ ክፉም ላደረጉ የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል። ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል። " እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል " ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ። እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። "
@aleroe
ደብረ ዘይት
ደብረ ዘይት የዐብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት
ደብረ ዘይት ማለት ቃሉ “ደብር” ሲል ተራራ ሲሆን “ዘይት” ሲል የወይራ ዛፍን ያመለከታል። ባጠቃላይ ደብረ ዘይት የወይራ ዛፍ (የዘይት ዛፍ) የበዛበት ተራራ ማለት ነው። ቦታው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ከጎለጎታ (ቀራንዮ) ተራራ በስተምስራቅ በግምት ፪ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ታላቅ ተራራ ነው። በሁለቱ ተራሮች መካከል ጌቴሴማኒ የሚባለው ለምለም ስፍራ ይኸውም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመቃብር ስፍራ ይገኛል።
የደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ የሚያድርበት፣ የሚያስተምርበት፣ ውሎ የሚያርፍበት ሥፍራ ነው። ሉቃ ፳፩፥ ፴፯፣ ሉቃ ፳፪፥ ፴፱፣ ዮሐ ፰፥ ፩ ከዚሁ ተራራ ላይ ነው ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው። ኋላም በዳግም ምጽአት እዚሁ ተራራ ላይ ነው ለፍርድ የሚመጣው። /ሐዋ ፩፥፲፫/። "
" በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም ምፅአቱ ) ይሰበካል። ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸ ክፉም ላደረጉ የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል። ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል። " እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል " ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ። እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። "
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
እ .. ረ .. ስ .. ቸ .. ዋ .. ለ .. ሁ ..!!
አንድ ምስኪን ሴት ወደ አንድ መንፈሳዊ አባት ዘንድ ቀርባ "እግዚአብሔር ሁሌም ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ሁኔታ ግራ የተጋቡት እኚህ አባትም በሁኔታው ተበሳጭተው ጥለዋት ይሄዳሉ። ከዚያን ቀን በኋላ እቺ ሴት እየደጋገመች በመምጣት "እግዚአብሔር ማታ ማታ እየመጣ ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ጭቅጭቅ የተሰላቹት እኚህ አባትም እንደለመደችው አንድ ቀን መጥታ ስታናግራቸው እንዲህ አሏት "እውነት አንቺን እለት እለት እየመጣ ፈጣሪ የሚያናግርሽ ከሆነ አምንሽ ዘንድ አንድ የቤት ስራ ልስጥሽ" አሏት ትኩር ብለው እየተመለከቷት! ሴትዬይቱም የሚሏትን ሁሉ ለማድረግ ቃል ገባች! እኚህ አባትም ከዚች ሴት ጭቅጭቅ ይገላግለኛል ያሉትን ጥያቄ አቀረቡላት እንዲህ በማለት "እውነት አንቺን እግዚአብሔር የሚያናግርሽ ከሆነ እስቲ ዛሬ ማታ አንድ ጥያቄ ጠይቂልኝ" አሏት። ሴትየዋም በእርጋታ "ምን ልጠይቅልዎ አባቴ?" አለቻቸው። "ለረጅም አመት ልተወው ያልቻልኩት የዛሬ ወር ገደማ ግን ንስሐ ገብቼ የተውኩት አንድ ኃጢአት እሰራ ነበር። ያ በፊት እሰራው የነበረ አሁን ግን ንሰሐ ገብቼ የተውኩት ኃጢአት ምን እንደነበረ ጠይቀሽ ንገሪኝ። እሱን ከነገረሽ እውነትም ላንቺ እግዚአብሔር እንደሚናገር አምናለሁ" አሏት። ሴትዬይቱም ወደቤቷ ሄደች።
ተመልሳ እንደማትመጣ ግን ገምተው ነበር አባ ነገር ግን በበነጋው ያቺ ሴት መጥታ አባን አስጠራቻቸው። አባም ሴትየዬቱን ሲያዩ በጣም ተገርመው ወደሷ በመሄድ በፌዝ መልክ "እህስ ልጄ እግዚአብሔርን ንስሀ ገብቼ ያቆምኩት ሀጢያት ምን እንደነበር ጠየቅሺው?" አሏት ሳቅ እያሉ "አዎን አባ" አለቻቸው ሴትየዋ አንገቷን እንዳቀረቀረች "እህሳ ምን አለሽ?" አሏት አባ በመጓጓት "እረስቸዋለሁ አለኝ" አለቻቸው፡፡ እኚህ መንፈሳዊ አባት ባልገመቱት የእግዚአብሔር ምላሽ ልባቸው ተነክቶ ስቅስቅ ብለው እያለቀሱ ወደደረታቸው አስጠግተው አቀፏት!……… ይባላል።
ታዲያ ከዚ ምን እንማር???
የሰው ልጅ ሙሉ ይቅርታ የለውም። ዛሬ ምን ፍሪዳ አርዶ ቢታረቅህ፣ ምን በልቅሶ ታጅበህ እየተንፈራፈርክ ይቅር በለኝ ብትለው "ይቅር ብየሀለሁ" ይልህና የሆነ ቀን ስታስቀይመው ይቅር ያለውን በደልህን እየቆጠረ ሲወቅስህ ይውላል እግዚአብሔር ግን ይቅር ካለህ በቃ ረሳው ፍቅር ነዋ፤ ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔርን በኛ መጠን መትረን ንስሐ በገባንበት ኃጢአት ዘወትር የምናለቅስ? ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔር እንደኛ ቂመኛ መስሎን በፍቅር ሂፆጱ ያጠበውን ኃጢአታችንን እያስታወስን ዘወትር በፀፀት እሾህ ራሳችንን የምንገርፍ? ይቅርታ ከመለመን እኮ ይቅር ማለት ይከብዳል! ምሬሀለሁ ከማለት ማረኝ እያሉ እግር ስር መደፋት ቤት በቀለለ! በህይወታችን የገፋንና ያቆሰለንን ሰው በደል ከመርሳትኮ ሺህ ጊዜ ፍሪዳ እያረዱ "እንታረቅ" ማለቱ እጅግ ቀላል ነውኮ ...! ለዚያም ነው መሰል ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሎት አስተምረን ባሉት ጊዜ "እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል አንተም ይቅር በለን" ብላችሁ ፀልዩ ያለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ የይቅርታ ዘመን ያድርግልን የይቅርታ ልብ ይስጠን
@aleroe
እ .. ረ .. ስ .. ቸ .. ዋ .. ለ .. ሁ ..!!
አንድ ምስኪን ሴት ወደ አንድ መንፈሳዊ አባት ዘንድ ቀርባ "እግዚአብሔር ሁሌም ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ሁኔታ ግራ የተጋቡት እኚህ አባትም በሁኔታው ተበሳጭተው ጥለዋት ይሄዳሉ። ከዚያን ቀን በኋላ እቺ ሴት እየደጋገመች በመምጣት "እግዚአብሔር ማታ ማታ እየመጣ ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ጭቅጭቅ የተሰላቹት እኚህ አባትም እንደለመደችው አንድ ቀን መጥታ ስታናግራቸው እንዲህ አሏት "እውነት አንቺን እለት እለት እየመጣ ፈጣሪ የሚያናግርሽ ከሆነ አምንሽ ዘንድ አንድ የቤት ስራ ልስጥሽ" አሏት ትኩር ብለው እየተመለከቷት! ሴትዬይቱም የሚሏትን ሁሉ ለማድረግ ቃል ገባች! እኚህ አባትም ከዚች ሴት ጭቅጭቅ ይገላግለኛል ያሉትን ጥያቄ አቀረቡላት እንዲህ በማለት "እውነት አንቺን እግዚአብሔር የሚያናግርሽ ከሆነ እስቲ ዛሬ ማታ አንድ ጥያቄ ጠይቂልኝ" አሏት። ሴትየዋም በእርጋታ "ምን ልጠይቅልዎ አባቴ?" አለቻቸው። "ለረጅም አመት ልተወው ያልቻልኩት የዛሬ ወር ገደማ ግን ንስሐ ገብቼ የተውኩት አንድ ኃጢአት እሰራ ነበር። ያ በፊት እሰራው የነበረ አሁን ግን ንሰሐ ገብቼ የተውኩት ኃጢአት ምን እንደነበረ ጠይቀሽ ንገሪኝ። እሱን ከነገረሽ እውነትም ላንቺ እግዚአብሔር እንደሚናገር አምናለሁ" አሏት። ሴትዬይቱም ወደቤቷ ሄደች።
ተመልሳ እንደማትመጣ ግን ገምተው ነበር አባ ነገር ግን በበነጋው ያቺ ሴት መጥታ አባን አስጠራቻቸው። አባም ሴትየዬቱን ሲያዩ በጣም ተገርመው ወደሷ በመሄድ በፌዝ መልክ "እህስ ልጄ እግዚአብሔርን ንስሀ ገብቼ ያቆምኩት ሀጢያት ምን እንደነበር ጠየቅሺው?" አሏት ሳቅ እያሉ "አዎን አባ" አለቻቸው ሴትየዋ አንገቷን እንዳቀረቀረች "እህሳ ምን አለሽ?" አሏት አባ በመጓጓት "እረስቸዋለሁ አለኝ" አለቻቸው፡፡ እኚህ መንፈሳዊ አባት ባልገመቱት የእግዚአብሔር ምላሽ ልባቸው ተነክቶ ስቅስቅ ብለው እያለቀሱ ወደደረታቸው አስጠግተው አቀፏት!……… ይባላል።
ታዲያ ከዚ ምን እንማር???
የሰው ልጅ ሙሉ ይቅርታ የለውም። ዛሬ ምን ፍሪዳ አርዶ ቢታረቅህ፣ ምን በልቅሶ ታጅበህ እየተንፈራፈርክ ይቅር በለኝ ብትለው "ይቅር ብየሀለሁ" ይልህና የሆነ ቀን ስታስቀይመው ይቅር ያለውን በደልህን እየቆጠረ ሲወቅስህ ይውላል እግዚአብሔር ግን ይቅር ካለህ በቃ ረሳው ፍቅር ነዋ፤ ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔርን በኛ መጠን መትረን ንስሐ በገባንበት ኃጢአት ዘወትር የምናለቅስ? ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔር እንደኛ ቂመኛ መስሎን በፍቅር ሂፆጱ ያጠበውን ኃጢአታችንን እያስታወስን ዘወትር በፀፀት እሾህ ራሳችንን የምንገርፍ? ይቅርታ ከመለመን እኮ ይቅር ማለት ይከብዳል! ምሬሀለሁ ከማለት ማረኝ እያሉ እግር ስር መደፋት ቤት በቀለለ! በህይወታችን የገፋንና ያቆሰለንን ሰው በደል ከመርሳትኮ ሺህ ጊዜ ፍሪዳ እያረዱ "እንታረቅ" ማለቱ እጅግ ቀላል ነውኮ ...! ለዚያም ነው መሰል ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሎት አስተምረን ባሉት ጊዜ "እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል አንተም ይቅር በለን" ብላችሁ ፀልዩ ያለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ የይቅርታ ዘመን ያድርግልን የይቅርታ ልብ ይስጠን
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
~~~ የጽዋ ማኅበር ~~~
✔ይህ አይነቱ ትውፊታዊ ሥራዓት አጀማመሩ መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ ተጠብቆ የኖረ ምእመናን በየተራ ምግብና መጠጥ አዘጋጅተው ከችግርኞች ጋር የሚሳተፉበት ሥርአት ነው።
✔ በጌታ በእመቤታችን:በቅዱሳን መላእክት : በጻድቃን በሰማእታት ስም በመታሰቢያ እለታቸው ይፈፀማል ።
✔የፅዋ ማህበር ስህተት አይደለም ይህ ማለት ግን አንድ አንድ ምዕመናን በፅዋ ማህበር ስም የሚያደርጉት ነገር ልክ ነው ማለትም አይደለም ለምሳሌ፦
ስካር፣መሰዳደብ፣በዘፈን መጨፈር ማህበሩን በፃድቃን ስም አዘጋጅቶ አንድ የተቸገረ ሰው ሳይጠሩ ሳያበሉ እርስ በራስ መገባበዝ . . . . ብዙ መጥቀስ እንችላለነን ይህ የቀደምት ሀዋርያቶችን ህብረጥ የሚጥስ ተግባር ነውና ክርስቲያኖች ሆነን እንዲህ የምናደርግ ካለን ከድርጊቱ መቆጠብ አለብን ! ትውፊቱን መጠበቅ አለብን ! እኛ በመሳሳታችን ሌላ ምዕመናንን እያሳሳትን ነውና ከዚህ ድርጊት እንቆጠብ !
✔የፅዋ ማህበር የመጀመሪያዎቹ ክርስትያኖች ሕይወት የሚያስታውስ ነው።
ይህ አብሮ መብላትና መጠጣት የአንድነት የፍቅር ማእድ አጋፔ (Agape)ከሀዋርያት ዘመን ጀምሮ የነበረ ነው። በዚህም በረከት ይገኝበታል ።
★ምሳ 10:7 የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው የኅጥኣን ስም ግን ይጠፋል።
★ሐዋ 2:44" ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፣ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ ፣ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉ ነበር።
★ዕብ 10:25 በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥መሰብሰባችንን አንተው እርስ በእርሳችን እንመካከር እንጂ፤ይልቁንም ቁኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።"
★ሐዋ 4:32 ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው፥ገንዘባቸውም ሁሉ በአንድነት ነበር እንጂ ካለው አንድ ነገር ስንኳ የራሱ እንደ ሆነ ማንም አልተናገረም።"
★ቆላ 2:5 በስጋ ምንም እኳን ብርቅ በመንፈስ ከናንተ ጋር ነኝና፥ ስርአታችሁንም በክርስቶስም ያለውን የእምነታችሁን ጽናት እያየሁ ደስ ይለኛል።"
★ቆላ 4:16 ይህችም መልእክት በእናንተ ዘንድ ከተነበበች በኋላ፥በሎዶቅያ ሰዎች ማህበር ደግሞ እድትነበብ አድርጉ። ከሎዶቅያም የምትገኘውን መልእክት እናንተ ደግሞ አንብቡ።
@aleroe
~~~ የጽዋ ማኅበር ~~~
✔ይህ አይነቱ ትውፊታዊ ሥራዓት አጀማመሩ መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ ተጠብቆ የኖረ ምእመናን በየተራ ምግብና መጠጥ አዘጋጅተው ከችግርኞች ጋር የሚሳተፉበት ሥርአት ነው።
✔ በጌታ በእመቤታችን:በቅዱሳን መላእክት : በጻድቃን በሰማእታት ስም በመታሰቢያ እለታቸው ይፈፀማል ።
✔የፅዋ ማህበር ስህተት አይደለም ይህ ማለት ግን አንድ አንድ ምዕመናን በፅዋ ማህበር ስም የሚያደርጉት ነገር ልክ ነው ማለትም አይደለም ለምሳሌ፦
ስካር፣መሰዳደብ፣በዘፈን መጨፈር ማህበሩን በፃድቃን ስም አዘጋጅቶ አንድ የተቸገረ ሰው ሳይጠሩ ሳያበሉ እርስ በራስ መገባበዝ . . . . ብዙ መጥቀስ እንችላለነን ይህ የቀደምት ሀዋርያቶችን ህብረጥ የሚጥስ ተግባር ነውና ክርስቲያኖች ሆነን እንዲህ የምናደርግ ካለን ከድርጊቱ መቆጠብ አለብን ! ትውፊቱን መጠበቅ አለብን ! እኛ በመሳሳታችን ሌላ ምዕመናንን እያሳሳትን ነውና ከዚህ ድርጊት እንቆጠብ !
✔የፅዋ ማህበር የመጀመሪያዎቹ ክርስትያኖች ሕይወት የሚያስታውስ ነው።
ይህ አብሮ መብላትና መጠጣት የአንድነት የፍቅር ማእድ አጋፔ (Agape)ከሀዋርያት ዘመን ጀምሮ የነበረ ነው። በዚህም በረከት ይገኝበታል ።
★ምሳ 10:7 የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው የኅጥኣን ስም ግን ይጠፋል።
★ሐዋ 2:44" ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፣ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ ፣ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉ ነበር።
★ዕብ 10:25 በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥መሰብሰባችንን አንተው እርስ በእርሳችን እንመካከር እንጂ፤ይልቁንም ቁኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።"
★ሐዋ 4:32 ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው፥ገንዘባቸውም ሁሉ በአንድነት ነበር እንጂ ካለው አንድ ነገር ስንኳ የራሱ እንደ ሆነ ማንም አልተናገረም።"
★ቆላ 2:5 በስጋ ምንም እኳን ብርቅ በመንፈስ ከናንተ ጋር ነኝና፥ ስርአታችሁንም በክርስቶስም ያለውን የእምነታችሁን ጽናት እያየሁ ደስ ይለኛል።"
★ቆላ 4:16 ይህችም መልእክት በእናንተ ዘንድ ከተነበበች በኋላ፥በሎዶቅያ ሰዎች ማህበር ደግሞ እድትነበብ አድርጉ። ከሎዶቅያም የምትገኘውን መልእክት እናንተ ደግሞ አንብቡ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
በመንግስትህ አስበኝ
በመንግሥትህ አስበኝ/2/
በበደሌ ብዛት /2/ አይተህ አትጣለኝ/2/
ሳስበው በደሌ ብዙ ነው/2/
በጨለማ ነፍሴን በላት ውድማ/2/
ሆዴ ባባ አፈሳለሁ እንባ/2/
እርቃኔን ቀረሁኝ ተገፈፈ ልብሴ
መድረሻው ጠፋብኝ ተጨነቀች ነፍሴ
የብርሃን ጸዳሌ ከዓይኔ ተገፈፈ
ከፊትህ ለመቆም ጉልበቴ ታጠፈ
አልቻልኩም ደግፈኝ እንድቆም/2/
ለገነት የበቃ ያቀማኛ ሽፍታ
እኔንም ደግፈኝ አውጣኝ የዚያን ለታ/2/
@aleroe
በመንግስትህ አስበኝ
በመንግሥትህ አስበኝ/2/
በበደሌ ብዛት /2/ አይተህ አትጣለኝ/2/
ሳስበው በደሌ ብዙ ነው/2/
በጨለማ ነፍሴን በላት ውድማ/2/
ሆዴ ባባ አፈሳለሁ እንባ/2/
እርቃኔን ቀረሁኝ ተገፈፈ ልብሴ
መድረሻው ጠፋብኝ ተጨነቀች ነፍሴ
የብርሃን ጸዳሌ ከዓይኔ ተገፈፈ
ከፊትህ ለመቆም ጉልበቴ ታጠፈ
አልቻልኩም ደግፈኝ እንድቆም/2/
ለገነት የበቃ ያቀማኛ ሽፍታ
እኔንም ደግፈኝ አውጣኝ የዚያን ለታ/2/
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
🕊መልክአ_ኢትዮጵያ🕊
#የቅድስት_ድንግል_ማርያም_የአሥራት_ሀገር ፤
#የብዙ_ቅዱሳኑ_መጠጊያ ፤
#ሀገረ_እግዚአብሔር_ቅድስት_ኢትዮጵያ ።
+++
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ኢትዮጵያ !
ሀገሩ ለተክለ ሃይማኖት ሐዋርያ፤
ህዝብኪ ይዜምሩ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ።
የሃይማኖት ድር የዉበት መለያ፤
ቀደምት ባለ ታሪክ የዓለም አርአያ።
........🕊
ሰላም ለአይንትኪ እለ ርእያ ፈጣሪ፤
ታምረ ኩሉ ገባሪ።
ማዳን ፍቅሩን ላዩ፤
ከጸሎት ላልዘገዩ።
........🕊
ሰላም ለአእዛንኪ እለ ሰምዓ ፈጣሪ፤
በከመ ኮነ እግዚአብሔር መሐሪ፤
ቅዳሴው ሰዓታቱ፤ ላደመጡ ማኅሌቱ።
.......🕊
ሰላም ለአፉኪ ዘነበበ ወንጌሉ፤
እንዘ ይፌጽም ቃሉ፤
ሃሌሉያን ለለመደ፤
አኰቴትን ለወደደ፤
ቅኔ ዜማን ላወረደ።
.......🕊
ሰላም ለገጽኪ ለለብሰ ልምላሜ፤
መልዓ ምሥጢር ወትርጓሜ፤
ለማይሽረው ዘመን እድሜ፤
የመልከኛ ሥያሜ፤
ለሆነው የውበት ፍጻሜ።
......🕊
ሰላም ለሀዳፍኪ እለ ሰፋ ሀበ እግዚአብሔር ህያው፤
ጸሎቱ እና ሙያው፤
ውዳሴ ነውና ግብሩ፤
ጌታሽ ነውና ክብሩ።
.......🕊
ሰላም ለከርስኪ ዘአስረጸ ማዬ፤
ለጸሙ ሰብ ዘአስተዬ፤
ቅዱሱ ጸበል ለፈቀበት፤
የቅዱሳኑ አጽም ላረፈበት፤
ፈዋሹ እምነት ለተገኘበት።
.......🕊
ሰላም ለዘባንኪ እምዘባነ አለም ዘተሌለዬ፤
ጸዊረ ተሰዓቱ ቅዱሳን በሰቢከ ወንጌል ዘአብ፤
እንግዳን መቀበል ላልደከሙ፤
መካናትሽን ለተሸከሙ።
.......🕊
ሰላም ለወልድኪ ያሬድ ማኅሌታይ፤
ወጣእመ ዜማ ቀዳማይ፤
ግዕዝ እዝል ወአራራይ።
ምድርሽን በዝማሬ ላራሰ፤
የአፉን ቅኔ ላፈሰሰ።
......🕊
ሰላም ለወልድኪ አባ ተክለ ሃይማኖት ፤
ዘሖረ በሰናይ ፍኖት፤
እንደ መላእክቱ በክንፍ ለበረረ፤
ባከበረው ንጉስ ለከበረ፤
ጣዖታትን ለሰበረ።
.......🕊
ሰላም ለወልድኪ አባ ዜና ማርቆስ፤
ሐዋርያሁ ለክርስቶስ፤
እምዘመደ ተክለ ሃይማኖት ባህታዊ፤
ጥሪው ሰማያዊ፤
መንገዱ ሰላማዊ።
......🕊
ሰላም ለወለትኪ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ፤
እንበለ መጠን ዘበስዓ እበያ ወክብራ፤
ለተመሰገነች በጽድቅ ሥራ፤
እጅ ላልሰጠች ለዓለም ምርኮ፤
ለጸናች በአምልኮ።
......🕊
ሰላም ለመካንኪ ግሸን ደብረ ከርቤ፤
ለይዜምሩ ካህናት በፍሥሐ ወበይባቤ፤
ፍኖተ ብርሃን ይእቲ፤
መንበረ መስቀሉ ዛቲ፤
መግቢያ በሯ አሐቲ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ መካነ ቅዱሳን ዝቋላ፤
እንተ ጸለዬ በአንቲ ገበረ መንፈስ ቅዱስ በማዕከላ፤
የቅዱሳኑ መፍለቂያ፤
የሰዓታቱ መድመቂያ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ እንተ ተሰይመት ጻድቃኔ፤
በአት ይእቲ ለመናኔ፤
የድውያኑ መፈወሻ፤
የሀዘንተኞች ጭንቅ መርሻ፤
የዲያቢሎስ ድል መንሻ።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ላሊበላ፤
መካነ ትብስእት ወተድላ፤
የጸጋው ዘይት ሲፈላ፤
የተቀባው ልጅሽ፤
ላነጸው መቅደስ በደጅሽ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ መርጦ ለማርያም፤
ደብረ ምሕረት ወሰላም፤
ለማይቋረጥባት እንጣኑ፤
ለሚጸልዩባት ቅዱሳኑ፤
ለፈለቁባት ምሁራኑ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ዮሐንስ ሸንኮራ፤
እምነ ውስቴታ ደናግል ዘይዜምራ፤
ጸበሉ እውራንን የሚያበራ፤
የዮሐንስ ገዳም የመጥምቁ፤
የዘካርያስ ልጅ የጻድቁ።
........ 🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ጽዮን አክሱም፤
እንተ ሀለወ ባቲ ታቦተ ጥንታዊት ወቅድም፤
ለጽዮን መኖሪያ ለከበረችው፤
ዳጎንን ለሰበረችው፤
ዳዊትን ካባ ላስጣለችው።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ ዋልድባ ሰላማዊት፤
አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት፤
የአባ ሳሙኤል ገዳማቸው፤
ለሚተረክባት ገድላቸው፤
ላከበራት ጸሎታቸው።
.....🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ አሰቦት ቅድስት፤
መካነ ቡሩካን ውድስት፤
ጸሎት ላልራቃት ጠዋት ማታ፤
ለቀደሳት ጌታ።
......🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ፤
እንተ አእረፈ ባቲ ለተክለ ሃይማኖት አጽሙ፤
ቅዱሱ ደብር መታሰቢያ፤
የመናንያን መሰብሰቢያ፤
የባለ ቅኔው ማሸብሸቢያ።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ መካነ ሰላም ደብረ ዳሞ፤
ይጸልዩ ባቲ አበው ቅዱሳን በአርምሞ፤
አረጋዊ በዘንዶ፤
በገደል ላይ ተረማምዶ፤
ለገደማት ጌታ ፈቅዶ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ ምስራቀ ፀሐይ ዘደብረ ዘይት፤
መካነ ሕይዎት አማናዊት፤
ላሳደገችን በውብ ቋንቋ፤
ላስያዘችኝ የዜማ ቃል።
......🕊
ሰላም ለአቡኪ ወልደ ማርያም፤
ንጉሰ ነገስት ስቡህ በአርያም፤
ጠላትሽን ለተዋጋ፤
ለብርታሽ ክንዱን ለዘረጋ፤
ቅጥርሽን በእሳት ለዘጋ።
........🕊
ሰላም ለእምኪ እመ ብዙኃን፤
ዛቲ ይእቲ ተድላ ብዙኃን፤
በአሥራት ለተሰጠሻት፤
በየዘመን ለጠራሻት፤
ስለ ፍቅሯ እናት ላልሻት።
#መልክአ_ኢትዮጵያ።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ አስራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን
አስቢያት።
+።+።+።+
-ሰለ እናትህ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም:
-ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
-ስለ ቅዱስ ያሬድ
-ስለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
-ስለ ቅድስት አርሴማ
-ስለ ዜና ማርቆስ
-ስለ አባ ኪሮስ
-ስለ አቡነ ሀብተማርያም
-ስለ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት
-ስለ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ:
-ስለ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ
-ስለ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብለህ ኢትዮጵያን ማራት ይቅር በላት። አሜን
@aleroe
🕊መልክአ_ኢትዮጵያ🕊
#የቅድስት_ድንግል_ማርያም_የአሥራት_ሀገር ፤
#የብዙ_ቅዱሳኑ_መጠጊያ ፤
#ሀገረ_እግዚአብሔር_ቅድስት_ኢትዮጵያ ።
+++
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ኢትዮጵያ !
ሀገሩ ለተክለ ሃይማኖት ሐዋርያ፤
ህዝብኪ ይዜምሩ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ።
የሃይማኖት ድር የዉበት መለያ፤
ቀደምት ባለ ታሪክ የዓለም አርአያ።
........🕊
ሰላም ለአይንትኪ እለ ርእያ ፈጣሪ፤
ታምረ ኩሉ ገባሪ።
ማዳን ፍቅሩን ላዩ፤
ከጸሎት ላልዘገዩ።
........🕊
ሰላም ለአእዛንኪ እለ ሰምዓ ፈጣሪ፤
በከመ ኮነ እግዚአብሔር መሐሪ፤
ቅዳሴው ሰዓታቱ፤ ላደመጡ ማኅሌቱ።
.......🕊
ሰላም ለአፉኪ ዘነበበ ወንጌሉ፤
እንዘ ይፌጽም ቃሉ፤
ሃሌሉያን ለለመደ፤
አኰቴትን ለወደደ፤
ቅኔ ዜማን ላወረደ።
.......🕊
ሰላም ለገጽኪ ለለብሰ ልምላሜ፤
መልዓ ምሥጢር ወትርጓሜ፤
ለማይሽረው ዘመን እድሜ፤
የመልከኛ ሥያሜ፤
ለሆነው የውበት ፍጻሜ።
......🕊
ሰላም ለሀዳፍኪ እለ ሰፋ ሀበ እግዚአብሔር ህያው፤
ጸሎቱ እና ሙያው፤
ውዳሴ ነውና ግብሩ፤
ጌታሽ ነውና ክብሩ።
.......🕊
ሰላም ለከርስኪ ዘአስረጸ ማዬ፤
ለጸሙ ሰብ ዘአስተዬ፤
ቅዱሱ ጸበል ለፈቀበት፤
የቅዱሳኑ አጽም ላረፈበት፤
ፈዋሹ እምነት ለተገኘበት።
.......🕊
ሰላም ለዘባንኪ እምዘባነ አለም ዘተሌለዬ፤
ጸዊረ ተሰዓቱ ቅዱሳን በሰቢከ ወንጌል ዘአብ፤
እንግዳን መቀበል ላልደከሙ፤
መካናትሽን ለተሸከሙ።
.......🕊
ሰላም ለወልድኪ ያሬድ ማኅሌታይ፤
ወጣእመ ዜማ ቀዳማይ፤
ግዕዝ እዝል ወአራራይ።
ምድርሽን በዝማሬ ላራሰ፤
የአፉን ቅኔ ላፈሰሰ።
......🕊
ሰላም ለወልድኪ አባ ተክለ ሃይማኖት ፤
ዘሖረ በሰናይ ፍኖት፤
እንደ መላእክቱ በክንፍ ለበረረ፤
ባከበረው ንጉስ ለከበረ፤
ጣዖታትን ለሰበረ።
.......🕊
ሰላም ለወልድኪ አባ ዜና ማርቆስ፤
ሐዋርያሁ ለክርስቶስ፤
እምዘመደ ተክለ ሃይማኖት ባህታዊ፤
ጥሪው ሰማያዊ፤
መንገዱ ሰላማዊ።
......🕊
ሰላም ለወለትኪ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ፤
እንበለ መጠን ዘበስዓ እበያ ወክብራ፤
ለተመሰገነች በጽድቅ ሥራ፤
እጅ ላልሰጠች ለዓለም ምርኮ፤
ለጸናች በአምልኮ።
......🕊
ሰላም ለመካንኪ ግሸን ደብረ ከርቤ፤
ለይዜምሩ ካህናት በፍሥሐ ወበይባቤ፤
ፍኖተ ብርሃን ይእቲ፤
መንበረ መስቀሉ ዛቲ፤
መግቢያ በሯ አሐቲ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ መካነ ቅዱሳን ዝቋላ፤
እንተ ጸለዬ በአንቲ ገበረ መንፈስ ቅዱስ በማዕከላ፤
የቅዱሳኑ መፍለቂያ፤
የሰዓታቱ መድመቂያ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ እንተ ተሰይመት ጻድቃኔ፤
በአት ይእቲ ለመናኔ፤
የድውያኑ መፈወሻ፤
የሀዘንተኞች ጭንቅ መርሻ፤
የዲያቢሎስ ድል መንሻ።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ላሊበላ፤
መካነ ትብስእት ወተድላ፤
የጸጋው ዘይት ሲፈላ፤
የተቀባው ልጅሽ፤
ላነጸው መቅደስ በደጅሽ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ መርጦ ለማርያም፤
ደብረ ምሕረት ወሰላም፤
ለማይቋረጥባት እንጣኑ፤
ለሚጸልዩባት ቅዱሳኑ፤
ለፈለቁባት ምሁራኑ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ዮሐንስ ሸንኮራ፤
እምነ ውስቴታ ደናግል ዘይዜምራ፤
ጸበሉ እውራንን የሚያበራ፤
የዮሐንስ ገዳም የመጥምቁ፤
የዘካርያስ ልጅ የጻድቁ።
........ 🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ጽዮን አክሱም፤
እንተ ሀለወ ባቲ ታቦተ ጥንታዊት ወቅድም፤
ለጽዮን መኖሪያ ለከበረችው፤
ዳጎንን ለሰበረችው፤
ዳዊትን ካባ ላስጣለችው።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ ዋልድባ ሰላማዊት፤
አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት፤
የአባ ሳሙኤል ገዳማቸው፤
ለሚተረክባት ገድላቸው፤
ላከበራት ጸሎታቸው።
.....🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ አሰቦት ቅድስት፤
መካነ ቡሩካን ውድስት፤
ጸሎት ላልራቃት ጠዋት ማታ፤
ለቀደሳት ጌታ።
......🕊
ሰላም ለመካንኪ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ፤
እንተ አእረፈ ባቲ ለተክለ ሃይማኖት አጽሙ፤
ቅዱሱ ደብር መታሰቢያ፤
የመናንያን መሰብሰቢያ፤
የባለ ቅኔው ማሸብሸቢያ።
.......🕊
ሰላም ለመካንኪ መካነ ሰላም ደብረ ዳሞ፤
ይጸልዩ ባቲ አበው ቅዱሳን በአርምሞ፤
አረጋዊ በዘንዶ፤
በገደል ላይ ተረማምዶ፤
ለገደማት ጌታ ፈቅዶ።
........🕊
ሰላም ለመካንኪ ምስራቀ ፀሐይ ዘደብረ ዘይት፤
መካነ ሕይዎት አማናዊት፤
ላሳደገችን በውብ ቋንቋ፤
ላስያዘችኝ የዜማ ቃል።
......🕊
ሰላም ለአቡኪ ወልደ ማርያም፤
ንጉሰ ነገስት ስቡህ በአርያም፤
ጠላትሽን ለተዋጋ፤
ለብርታሽ ክንዱን ለዘረጋ፤
ቅጥርሽን በእሳት ለዘጋ።
........🕊
ሰላም ለእምኪ እመ ብዙኃን፤
ዛቲ ይእቲ ተድላ ብዙኃን፤
በአሥራት ለተሰጠሻት፤
በየዘመን ለጠራሻት፤
ስለ ፍቅሯ እናት ላልሻት።
#መልክአ_ኢትዮጵያ።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ አስራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን
አስቢያት።
+።+።+።+
-ሰለ እናትህ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም:
-ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
-ስለ ቅዱስ ያሬድ
-ስለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
-ስለ ቅድስት አርሴማ
-ስለ ዜና ማርቆስ
-ስለ አባ ኪሮስ
-ስለ አቡነ ሀብተማርያም
-ስለ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት
-ስለ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ:
-ስለ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ
-ስለ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብለህ ኢትዮጵያን ማራት ይቅር በላት። አሜን
@aleroe