"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
እኅቴን ላኩልኝ
#በዲ/ን ሕሊና በለጠ
√
ምነው ጨላለመች - የሀገሬ ፀሐይ
የሴት ልጅ ደም ፈሶ - ሥርየት አለ ወይ?
√
ዓርቡ የረዘመ - እሑዱ የራቀው
ምን የሚሉት ጾም ነው - ባ'ገሬ የገባው?
√
ምን ክፋት ቢኖርህ - ምንም ያ'ል ብታቄም
ምን ጀብደኛ ብትኾን - ብታደራጅ አቅም
ሴት አሥሮ 'ሚሟገት - ጀግናስ እኔ አላውቅም።
√
መጥቀው እንዲያመጥቁን - ብንሰድ እንዲማሩ
በዕውቀት ተራቀው - ተሠወሩ አሉ።
√
"ከማጀት ላውላት" - ብዬ ነበር ያኔ
"ግድ የሎትም ትማር" - ብለው ወትውተውኝ - ነጥለው ከጎኔ
ትም' ርቱ አልበቃ ቢል - ለጦር ላኳት አሉ - ወዮ ኧረ ወይኔ!
√
እኅትነት ቅኔ - መውደዷም ነው ዕንቁ
ደግሞ ሠወር ስትል - እንኳንስ ሕይወቷ - ድምጿም መናፈቁ።
√
ያገሬ መጋኛ - ጥፊው አያጠፋም
ያገሬ ሰላቢ - ምትሐቱ ዕቃን እንጂ - ሰውን አይሠውርም።
አፍኖ የዋጠሽ - ሲያኝክ ማያሰማ
የየት አገሩ ይኾን - የበላሽ እቴዋ!?
√
ምግቡም ጣዕም የለው - አልበላ አለኝ
አጣፍጣ ታጉርሰኝ - እኅቴን ላኩልኝ።
@aleroe
#በዲ/ን ሕሊና በለጠ
√
ምነው ጨላለመች - የሀገሬ ፀሐይ
የሴት ልጅ ደም ፈሶ - ሥርየት አለ ወይ?
√
ዓርቡ የረዘመ - እሑዱ የራቀው
ምን የሚሉት ጾም ነው - ባ'ገሬ የገባው?
√
ምን ክፋት ቢኖርህ - ምንም ያ'ል ብታቄም
ምን ጀብደኛ ብትኾን - ብታደራጅ አቅም
ሴት አሥሮ 'ሚሟገት - ጀግናስ እኔ አላውቅም።
√
መጥቀው እንዲያመጥቁን - ብንሰድ እንዲማሩ
በዕውቀት ተራቀው - ተሠወሩ አሉ።
√
"ከማጀት ላውላት" - ብዬ ነበር ያኔ
"ግድ የሎትም ትማር" - ብለው ወትውተውኝ - ነጥለው ከጎኔ
ትም' ርቱ አልበቃ ቢል - ለጦር ላኳት አሉ - ወዮ ኧረ ወይኔ!
√
እኅትነት ቅኔ - መውደዷም ነው ዕንቁ
ደግሞ ሠወር ስትል - እንኳንስ ሕይወቷ - ድምጿም መናፈቁ።
√
ያገሬ መጋኛ - ጥፊው አያጠፋም
ያገሬ ሰላቢ - ምትሐቱ ዕቃን እንጂ - ሰውን አይሠውርም።
አፍኖ የዋጠሽ - ሲያኝክ ማያሰማ
የየት አገሩ ይኾን - የበላሽ እቴዋ!?
√
ምግቡም ጣዕም የለው - አልበላ አለኝ
አጣፍጣ ታጉርሰኝ - እኅቴን ላኩልኝ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
የቫላንታይን ቀን በዓል - ድብቅ እውነታ
======================
(ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ)
ስንቶቻችን ይሆን የቫለንታይን ቀን(የፍቅረኞች ቀን ብለን የምናከብረው) የሚከበርበት ምክንያትና መነሻው የምናውቀው? ወይስ ሰው ስለ አከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው? ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ክፍለ ዘመናት በፊት አረማዊ ሮማውያንየካቲት 14 ማታና የካቲት 15 "የተኩላ አዳኙ"ለሚሉት ሉፐርኩስ(Lupercus) ክብር በማለት በጣኦት አምልኮ ያከብሩት ነበር።ሮማውያን ይህ በዓል ሉፐርካልያ
(Lupercalia) ይሉታል።ንጉሥ ቆንጠንጢኖስ ክርስትና የሮማውያን ይፋዊ ሃይማኖት መሆኑ በማወጁ ማነኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተወስኑ ሮማውያን
ሰዎች ግን በዓሉን ማክበር አልተዉም።ይህንን አረማዊ በዓል
ማለትም ሉፐርካልያ የሮማው ጳጳስ ገላስዮስ ክርስትያናዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር አደረጉ።ጳጳስ ገላስዮስ ለካቲት 15 ሲከበር የነበረው በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን በሚል አዲስ ስያሜ የካቲት 14 እንዲከበር አደረጉ።
እንዴት ይህ አረማዊ በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የሚል ስያሜ ተሰጠው?
ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው።ቫላንታይን ጥንታዊው ታዋቂው ሉፐርኩስ ነው።ሉፐርኩስ በግሪካውያን ፓን(pan) ተብሎ ይጠራል።በጥንታውያን አይሁድ
ደግሞ ይህ ፓን ባል(Baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።ባል በመጽሓፍ ቅዱስ ዘፍጥረት 10-9 ላይ ታላቁ አዳኝ ተብሎ
ለተገለጸው ኒምሮድ ሌላኛው መጠርያው ነው።ኒምሮድ የሮማውያን የተኩላ አዳኙ ሉፐርኩስ ነበር።በዚህ መሠረትም
የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የአረማውያን ለኒምሮድ ክብር የሚያከብሩት የጣኦት አምልኮ ነው። ቫለንታይን የሚል ቃል ቫለንቲኑስ(valentinus) ቫለንስ ከሚል
የላቲን ቃል የመጣ ነው።ቀጥተኛ ትርጉሙ ጠንካራ፣ሃይለኛ
ታላቅ ማለት ነው።ዘፍጥረት10-9 ላይ እንደምናነበው " እርሱም
በእግዚአብሔር ፊት አዳኝ ነበረ ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር
ፊት ሃያል አዳኝ እንደ ኒምሮድ ተባለ።" ኒምሮድ የሮማውያን
ጀግና ሃይለኛ ሰው ቫለንታይን ነበር።
ሌላኛው የኒምሮድ ስም ሳንክቱስ(Sancutus) ወይ ሳንታ
(santa) ነው ሳይንት(saint) የሚል የእግሊዝኛ ትርጉምአለው
ማለትም ቅዱስ።የሮማውያን ሉፐርካልያ በመጨረሻ ቅዱስ
ቫለንታይን የሚል ስያሜያዘ ማለት ነው።
ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን በቀዱት አረማዊ የልብ
(heart) ምልክት ይጠቀማሉ።በባቢሎናውያን ባል(bal) ልብ የሚል ፍቺ ነው ያለው።በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት
ለቫለንታይን ቀን(የፍቅረኛሞች ቀንየምንለው) መገለጫ እንጠቀምበታለን።ባል የባቢሎናውያን የጣኦት ጌታ ነበር።በሌላ መንገድም ኒምሮድ ወይም ቅዱስ ቫለንታይን ሳተርን ተብሎ ይጠራል።ሳተርን የሮማ-ባቢሎን ከአባራሮዎቹ ለመሸሽ በምስጥራዊ ቦታ የሚደበቅ ጣኦት ነው።ሳተርን የሚል የላቲን ቃል ሴመቲክ(አይሁድ) ቋንቋ ከሚናገሩ ባቢሎናውያን የተገኝ ነው።መደበቅ፣ራስን መደበቅ የሚል ፍቺ አለው። በጥንታዊ እምነትም ኒምሮድ(ሳተርን) ከአባራሮዎቹ በመሸሽ ወደ ጣልያን እንደተጓዘይነገራል።የአፐኒን ተራራ ስያሜው ወደ ኔምብሮድ ወይም ኒምሮድ ተቀየረ።ይህ ተራራ ኒምሮድ በጣልያን የተሸሸገበት ቦታ ነበር።ሮማም በዚ ተራራ ላይ እንደ ተመሰረተች ይታወቃል።ሮም ፈርሳ እንደገና ከመሰራትዋ 753ዓ/ዓ በፊት ሳቹርንያ (ሳተርን፡ኒምሮድ የተደበቀባት ቦታ) የሚል ስያሜ ነበራት።ኒምሮድ በዚህ ቦታ ተይዞበፈጸመው ወንጀል ተገደለ።በንጉሥ ቆስጠንጦኖስ ጊዜም ክርስትያናዊ ሰማዕት የሚል የውሸት ክብር ተሰጥቶት በሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን
መዘከር ጀመረ።ኒምሮድ፣ባል፣ቫለንታይን፣ታላቁ አዳኝ፣ፋውኑስና ሉፐርክስ 31ኛ፣32ኛና 33ኛና ደረጃ (ዲግሪ) ላይ ያሉ ፍሪማሶኖሪዎች ከሚያመልኩትባፎሜት(የሜንደዝ ፍየል) ጋር የሚስተካከል ነው። እንግዲህ በሰላቢ እጆች (ኢሊሙናቲ) ሴራ ዘመናዊነት ተላብሶ ድብቅ ጣኦት የሚመለክበት የቅዱስ ቫለንታይን ቀን እኛ ደግሞ የፍቅረኛሞች ቀን በማለት እያከበርን ማለትም እያመለክን ነው።አንድ በአል የሚከበርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሊኖረው ግድ ነው።ሆኖም የምናከብረውን በአል የምናከብርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሳናውቅ ከሴሮኞች ድብቅ አላማ ማስፈጸምያ ከመሆን መቆጠብ ይበጃል።
@aleroe
የቫላንታይን ቀን በዓል - ድብቅ እውነታ
======================
(ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ)
ስንቶቻችን ይሆን የቫለንታይን ቀን(የፍቅረኞች ቀን ብለን የምናከብረው) የሚከበርበት ምክንያትና መነሻው የምናውቀው? ወይስ ሰው ስለ አከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው? ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ክፍለ ዘመናት በፊት አረማዊ ሮማውያንየካቲት 14 ማታና የካቲት 15 "የተኩላ አዳኙ"ለሚሉት ሉፐርኩስ(Lupercus) ክብር በማለት በጣኦት አምልኮ ያከብሩት ነበር።ሮማውያን ይህ በዓል ሉፐርካልያ
(Lupercalia) ይሉታል።ንጉሥ ቆንጠንጢኖስ ክርስትና የሮማውያን ይፋዊ ሃይማኖት መሆኑ በማወጁ ማነኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተወስኑ ሮማውያን
ሰዎች ግን በዓሉን ማክበር አልተዉም።ይህንን አረማዊ በዓል
ማለትም ሉፐርካልያ የሮማው ጳጳስ ገላስዮስ ክርስትያናዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር አደረጉ።ጳጳስ ገላስዮስ ለካቲት 15 ሲከበር የነበረው በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን በሚል አዲስ ስያሜ የካቲት 14 እንዲከበር አደረጉ።
እንዴት ይህ አረማዊ በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የሚል ስያሜ ተሰጠው?
ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው።ቫላንታይን ጥንታዊው ታዋቂው ሉፐርኩስ ነው።ሉፐርኩስ በግሪካውያን ፓን(pan) ተብሎ ይጠራል።በጥንታውያን አይሁድ
ደግሞ ይህ ፓን ባል(Baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።ባል በመጽሓፍ ቅዱስ ዘፍጥረት 10-9 ላይ ታላቁ አዳኝ ተብሎ
ለተገለጸው ኒምሮድ ሌላኛው መጠርያው ነው።ኒምሮድ የሮማውያን የተኩላ አዳኙ ሉፐርኩስ ነበር።በዚህ መሠረትም
የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የአረማውያን ለኒምሮድ ክብር የሚያከብሩት የጣኦት አምልኮ ነው። ቫለንታይን የሚል ቃል ቫለንቲኑስ(valentinus) ቫለንስ ከሚል
የላቲን ቃል የመጣ ነው።ቀጥተኛ ትርጉሙ ጠንካራ፣ሃይለኛ
ታላቅ ማለት ነው።ዘፍጥረት10-9 ላይ እንደምናነበው " እርሱም
በእግዚአብሔር ፊት አዳኝ ነበረ ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር
ፊት ሃያል አዳኝ እንደ ኒምሮድ ተባለ።" ኒምሮድ የሮማውያን
ጀግና ሃይለኛ ሰው ቫለንታይን ነበር።
ሌላኛው የኒምሮድ ስም ሳንክቱስ(Sancutus) ወይ ሳንታ
(santa) ነው ሳይንት(saint) የሚል የእግሊዝኛ ትርጉምአለው
ማለትም ቅዱስ።የሮማውያን ሉፐርካልያ በመጨረሻ ቅዱስ
ቫለንታይን የሚል ስያሜያዘ ማለት ነው።
ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን በቀዱት አረማዊ የልብ
(heart) ምልክት ይጠቀማሉ።በባቢሎናውያን ባል(bal) ልብ የሚል ፍቺ ነው ያለው።በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት
ለቫለንታይን ቀን(የፍቅረኛሞች ቀንየምንለው) መገለጫ እንጠቀምበታለን።ባል የባቢሎናውያን የጣኦት ጌታ ነበር።በሌላ መንገድም ኒምሮድ ወይም ቅዱስ ቫለንታይን ሳተርን ተብሎ ይጠራል።ሳተርን የሮማ-ባቢሎን ከአባራሮዎቹ ለመሸሽ በምስጥራዊ ቦታ የሚደበቅ ጣኦት ነው።ሳተርን የሚል የላቲን ቃል ሴመቲክ(አይሁድ) ቋንቋ ከሚናገሩ ባቢሎናውያን የተገኝ ነው።መደበቅ፣ራስን መደበቅ የሚል ፍቺ አለው። በጥንታዊ እምነትም ኒምሮድ(ሳተርን) ከአባራሮዎቹ በመሸሽ ወደ ጣልያን እንደተጓዘይነገራል።የአፐኒን ተራራ ስያሜው ወደ ኔምብሮድ ወይም ኒምሮድ ተቀየረ።ይህ ተራራ ኒምሮድ በጣልያን የተሸሸገበት ቦታ ነበር።ሮማም በዚ ተራራ ላይ እንደ ተመሰረተች ይታወቃል።ሮም ፈርሳ እንደገና ከመሰራትዋ 753ዓ/ዓ በፊት ሳቹርንያ (ሳተርን፡ኒምሮድ የተደበቀባት ቦታ) የሚል ስያሜ ነበራት።ኒምሮድ በዚህ ቦታ ተይዞበፈጸመው ወንጀል ተገደለ።በንጉሥ ቆስጠንጦኖስ ጊዜም ክርስትያናዊ ሰማዕት የሚል የውሸት ክብር ተሰጥቶት በሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን
መዘከር ጀመረ።ኒምሮድ፣ባል፣ቫለንታይን፣ታላቁ አዳኝ፣ፋውኑስና ሉፐርክስ 31ኛ፣32ኛና 33ኛና ደረጃ (ዲግሪ) ላይ ያሉ ፍሪማሶኖሪዎች ከሚያመልኩትባፎሜት(የሜንደዝ ፍየል) ጋር የሚስተካከል ነው። እንግዲህ በሰላቢ እጆች (ኢሊሙናቲ) ሴራ ዘመናዊነት ተላብሶ ድብቅ ጣኦት የሚመለክበት የቅዱስ ቫለንታይን ቀን እኛ ደግሞ የፍቅረኛሞች ቀን በማለት እያከበርን ማለትም እያመለክን ነው።አንድ በአል የሚከበርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሊኖረው ግድ ነው።ሆኖም የምናከብረውን በአል የምናከብርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሳናውቅ ከሴሮኞች ድብቅ አላማ ማስፈጸምያ ከመሆን መቆጠብ ይበጃል።
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
#እንኳን ለዐብይ ፆም በሰላም አደረሰን
☞ፆም ማለት ምን ማለት ነው?
☞የአብይ ስያሜዎች ስንት ናቸው?
☞የአብይ ፆም ለምን ታላቁ ጾም ተበለ?
☞የአብይ ጾም ስንት ክፍሎች አሉት?
☞የአብይ ጾም ለስንት ሳምንት ይፆማል
☞ስለ ዘወረደ ምን ያውቃሉ?
1ኛ. ፆም ማለት ምን ማለት ነው?
ፆመ ፦ ተወ " ታቀበ"ታረመ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ነው።
ፍቹም ምግብን መተው ' መከልከል' መጠበቅ ማለት ነው።
ፆም ማለት ሰውነት ከሚያስፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል መወሰን ማለት
ነው። ወይም ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጎመጀውን ነገር መተው ማለት
ነው ።
ፆም ከሃይማኖት ጋር ዝምድና ስላለው ሃይማኖት ባለበት ሁሉ ፆም አለ።
ፆም በብሉይ እና ኪዳን ከፍተኛ ቦታ አለው ።
ነብያት ከእግዚአብሄር ጋር በሚገናኙበት ወራት እህል ውሃ በአፋቸው አይገባም
ነበር።//ዘፀ ፴፬÷፳፰//34*28//
በሐፂያት ብዛት የታዘዘውን የእግዚአብሔርን መዓት የሚመልሰው ሕዝቡ በፆም
ሲለምኑት ሲማልዱት ነበር። //ዮሐ ፪÷፯_፲// 2*7-20//
በሐዲስ ኪዳንም ፆም ሰው ሰራሽ ህግ ሳይሆን እራሱ መድኃኒታችን በመዋዕለ
ስጋዌው የስራ መጀመሪያ አድርጎ የሰራው ህግ ነው።//፬÷፪// 4*2//
ይህ ብቻ ሳይሆን በቁራኝነት አብሮ የሚኖር መንፈስ እርኩስ ሰይጣን እንኳን
በፆም እሚወገድ መሆኑን መድኃኒታችን ተናግሯል።// ማቴ ፲፯÷፳፩//
17*21/ሐ
ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የታዘዙ ሐዋሪያትም ከመንፈስ ቅዱስ በየጊዜው
ትዕዛዝ እሚቀበሉበት በፆም እና በፆለት ላይ እንዳሉ ነበር።// የሐዋ
፲፫÷፪//13*2//
ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናት ቀሳውስት የሚሾሙት በፆምና
በፆለት ነበር።//የሐዋ፲፫÷፫//13*3//
ፆምስ በታወቀው እለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ መከልከል ነው።
ፆም ማለት፦ጥለላት ማባልዕትን ፈፅሞ መተው ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ
ከሌላውም ክፉ ነገር ሁሉ መጠበቅ ፣መገዛት፣ መቆጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ
በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ይቅር በለኝ በማለት ቅድመ
እግዚአብሔር በመንበርከክ ምህረት በአምላክ ለመቀበል መዘጋጀት ነው።
ፆም ቁስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ሀይለ ፍትወትን የምታደክም የበጎ ምግባር
ሁሉ መጀመሪያ ከእግዚአብሔር ፀጋን የምትሰጥ ፣የወንጌል ስራ መጀመሪያ፣
የፅሙዳን ክብራቸው፣ የደናግል እና የንፅህና ጌጣቸው
፣የንፅህና መገለጫ፣ የጸሎት ምክንያት እናት፣ የእንባ መገናኛ መፍለቂያ፣
አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ስራ ሁሉ የምትነቃቃ፣ ሰውነትን
በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትህትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ
መድኃኒት ነፍስ ናት።
ከህገ ልቦና ከነበሩ አበው አንስቶ በዘመነ ኦሪት እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ
በተለያዩ ጊዜያት የነበሩ ቀደምት አበው ነቢያት፣ ነገስታት፣ካህናት በፆምና
በጸሎት ፅሙድ ሁነው እግዚአብሔር አምላካቸው ከክፉ ነገር እንዲሰውራቸው
በይቅርታ እንዲጎበኛቸው ሀይልንም እንዲያጎናፅፋቸው ተማፅነው ሀሳባቸውን
ፈፅሞላቸዋል።
በሀድስ ኪዳን ፆም ስለ ፅድቅ ተብሎ መከናወን ያለበት አብይ ተግባር ነው። //
ማቴ፭÷፮// 5*6//
ስጋዊ ጥቅምን ለማግኘት ተድላ ስጋን በመሻት ሳይሆን ዘላለማዊ መንግስት
ለመውረስ ስለ ፅድቅ ተብሎ የሚፈፀም ነው።
ፆም እንደምን ነው ቢሉ የስጋ ምግባር ነው።
ምፅዋት የገንዘብ ግብር እንደሆነች:አንድም ምፅዋት ስጋን መገበር ነው።
ምፅዋት ገንዘብ መገበር እንደሆነች። ~~~ስለዚህ የሚፆም ሰው በፈቃደ
ስጋው ላይ ድልን ይቀዳጃል።
በእምነት ሁኖ የለመነውን እግዚአብሔር ይሰጠዋል። ሰማያዊ የሆነውን
ምስጢር ለማየት ከአለማዊ ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል።
በአለም እየኖረ ከአለሙ ይለያል። ከአለም አይደለምና//
ዮሐ፲፭÷፲፱//15*19 //
2ኛ.
ዐቢይ ጾምም ቤተክርስቲያናችን እንድንጾም ካወጀችልን ጾም አንዱ ነው፡፡
ዐቢይ ጾምየተለያዩ ስሞች አሉት፡፡ አንደኛ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም በመሆኑ እንዲሁም ዐቢይ
እግዚአብሔር ወዓቢይ ኀይሉ ዓቢይ እግዚአብሔር ወብዙኃ አኰቴቱ የተባለ
ጌታ የጾመው ስለሆነ፣ /መዝ.47፥1፣ መዝ.146፥5/፡፡ ሁለተኛ ሁዳዴ ጾም
ይባላል፡፡ ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት
ሥራ ሁዳድ ስለሚባል ሲሆን ከአጽዋማት ሁሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ኃያሉ
አምላካችን ስለጾመው ነው፡፡፣ /አሞ.7፥1/፡፡ ሦስተኛ በዓተ ጾም ይባላል፡፡
የጾም መግቢያ፣ መባቻ ወይም ጾሙ የሚሰፍርበት በዓት ማለት ነው፡፡ አራተኛ
ጾመ አርባ ይባላል፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው 40 /ዓርባ/ ቀን
ስለሆነ፣ /ማቴ.4፥1/ አምስተኛ ጾመ ኢየሱስይባላል፡፡ ጾሞ፣ ጹሙ ብሎ
ስላዘዘን፣ ስድስተኛ ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዘወረደ ሰኞ ዕዝል
ከመዝ ይቤ ሙሴ እስመ ለዓለም፣ ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት እያለ በጾመ
ድጓ ስለ ዘመረ ነው፡፡
ዐቢይ ጾምጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው፡፡ ማቴ.4፥1
ምእመናን ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል፡፡ ዐቢይ ጾም
ስምንት ሳምንታት /55 ቀኖች/ አሉት፡፡ ሰባት ቅዳሜ ስምንት እሑድ ይገኛሉ፡፡
አሥራ አምስት ቀን ማለት ነው፡፡ ከጥሉላት እንጂ ከእህል ውኃ ስለማይጦሙ
የጦሙ ወራት አርባ ቀን ብቻ ይሆናል፡፡
3ኛ.
የአቢይ ጾም ሦስቱ ክፍሎች
1. ዘወረደ (ጾመ ሕርቃል)፤ ይህም ጾሙ ከሚገባበት
ሰኞ ጀምሮ እስከ እሑድ ያረስ ያለው 7 ቀን ነው።
2. የጌታ ጾም፤ ይህም ከቅድስት ሰኞ እስከ ሆሣዕና
ዋዜማ ዓርብ ድረስ ያለው 40 ቀን ነው።
3. ሕማማት፤ ይህም ጌታችን በአልዓዛር ቤት ለማዕድ
ከተቀመጠበት የሆሳዕና ቅዳሜ ጀምሮ እስከ ሥዑር
ቅዳሜ ያለው መከራን የተቀበለበት 8 ቀን ሕማማት
ነው።
ይህም 7+40+8 = 55 ቀን ማለት ነው።
4ኛ.
የአብይ ጾም ሳምንታት 8 ናቸው፤
ዘወረደ
ቅድስት
ምኩራብ
መጻጉዕ
ደብረዘይት
ገብርሔር
ኒቆዲሞስ
ሆሣዕ
ሰለ ተትርጉማቸው ከታች ከተለጠፈው ሰንጠረዥ ተመልከት
5ኛ. ለምን አብይ / ታላቅ
ተባለ
አብይ ፆም መባሉ ትልቅና ታላቅ ፆም መሆኑን
ለማሳወቅ ነው። ይህ ፆም ታላቅ
መባሉም ለ55 ቀናት ያህል መፆሙና
ከሌሎቹ አፅዋማት ጋር ሲነፃፀር በቁጥር
መብለጡ ብቻ ሳይሆን ጌታችን አምላካችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ
ቆሮንቶስ መፆም ሳይገባው ለእኛ አርአያና
ትልቅ ምሳሌ ለመሆን የፆመው ፆምም
በመሆኑ ነው
6ኛኛ.
የመጀመሪያ የአቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም
ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ ስያሜውም፤ በ 614 ዓ . ም ኪርዮስ የተባለ
የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ፡፡ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ ቅድሳት ዘርፎ 60 ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3 ሺ የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ 14 ዓመት በኋላ በ 628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው አላቸው እኛ የአንተን እድሜ ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡
@aleroe
#እንኳን ለዐብይ ፆም በሰላም አደረሰን
☞ፆም ማለት ምን ማለት ነው?
☞የአብይ ስያሜዎች ስንት ናቸው?
☞የአብይ ፆም ለምን ታላቁ ጾም ተበለ?
☞የአብይ ጾም ስንት ክፍሎች አሉት?
☞የአብይ ጾም ለስንት ሳምንት ይፆማል
☞ስለ ዘወረደ ምን ያውቃሉ?
1ኛ. ፆም ማለት ምን ማለት ነው?
ፆመ ፦ ተወ " ታቀበ"ታረመ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ነው።
ፍቹም ምግብን መተው ' መከልከል' መጠበቅ ማለት ነው።
ፆም ማለት ሰውነት ከሚያስፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል መወሰን ማለት
ነው። ወይም ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጎመጀውን ነገር መተው ማለት
ነው ።
ፆም ከሃይማኖት ጋር ዝምድና ስላለው ሃይማኖት ባለበት ሁሉ ፆም አለ።
ፆም በብሉይ እና ኪዳን ከፍተኛ ቦታ አለው ።
ነብያት ከእግዚአብሄር ጋር በሚገናኙበት ወራት እህል ውሃ በአፋቸው አይገባም
ነበር።//ዘፀ ፴፬÷፳፰//34*28//
በሐፂያት ብዛት የታዘዘውን የእግዚአብሔርን መዓት የሚመልሰው ሕዝቡ በፆም
ሲለምኑት ሲማልዱት ነበር። //ዮሐ ፪÷፯_፲// 2*7-20//
በሐዲስ ኪዳንም ፆም ሰው ሰራሽ ህግ ሳይሆን እራሱ መድኃኒታችን በመዋዕለ
ስጋዌው የስራ መጀመሪያ አድርጎ የሰራው ህግ ነው።//፬÷፪// 4*2//
ይህ ብቻ ሳይሆን በቁራኝነት አብሮ የሚኖር መንፈስ እርኩስ ሰይጣን እንኳን
በፆም እሚወገድ መሆኑን መድኃኒታችን ተናግሯል።// ማቴ ፲፯÷፳፩//
17*21/ሐ
ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የታዘዙ ሐዋሪያትም ከመንፈስ ቅዱስ በየጊዜው
ትዕዛዝ እሚቀበሉበት በፆም እና በፆለት ላይ እንዳሉ ነበር።// የሐዋ
፲፫÷፪//13*2//
ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናት ቀሳውስት የሚሾሙት በፆምና
በፆለት ነበር።//የሐዋ፲፫÷፫//13*3//
ፆምስ በታወቀው እለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ መከልከል ነው።
ፆም ማለት፦ጥለላት ማባልዕትን ፈፅሞ መተው ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ
ከሌላውም ክፉ ነገር ሁሉ መጠበቅ ፣መገዛት፣ መቆጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ
በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ይቅር በለኝ በማለት ቅድመ
እግዚአብሔር በመንበርከክ ምህረት በአምላክ ለመቀበል መዘጋጀት ነው።
ፆም ቁስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ሀይለ ፍትወትን የምታደክም የበጎ ምግባር
ሁሉ መጀመሪያ ከእግዚአብሔር ፀጋን የምትሰጥ ፣የወንጌል ስራ መጀመሪያ፣
የፅሙዳን ክብራቸው፣ የደናግል እና የንፅህና ጌጣቸው
፣የንፅህና መገለጫ፣ የጸሎት ምክንያት እናት፣ የእንባ መገናኛ መፍለቂያ፣
አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ስራ ሁሉ የምትነቃቃ፣ ሰውነትን
በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትህትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ
መድኃኒት ነፍስ ናት።
ከህገ ልቦና ከነበሩ አበው አንስቶ በዘመነ ኦሪት እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ
በተለያዩ ጊዜያት የነበሩ ቀደምት አበው ነቢያት፣ ነገስታት፣ካህናት በፆምና
በጸሎት ፅሙድ ሁነው እግዚአብሔር አምላካቸው ከክፉ ነገር እንዲሰውራቸው
በይቅርታ እንዲጎበኛቸው ሀይልንም እንዲያጎናፅፋቸው ተማፅነው ሀሳባቸውን
ፈፅሞላቸዋል።
በሀድስ ኪዳን ፆም ስለ ፅድቅ ተብሎ መከናወን ያለበት አብይ ተግባር ነው። //
ማቴ፭÷፮// 5*6//
ስጋዊ ጥቅምን ለማግኘት ተድላ ስጋን በመሻት ሳይሆን ዘላለማዊ መንግስት
ለመውረስ ስለ ፅድቅ ተብሎ የሚፈፀም ነው።
ፆም እንደምን ነው ቢሉ የስጋ ምግባር ነው።
ምፅዋት የገንዘብ ግብር እንደሆነች:አንድም ምፅዋት ስጋን መገበር ነው።
ምፅዋት ገንዘብ መገበር እንደሆነች። ~~~ስለዚህ የሚፆም ሰው በፈቃደ
ስጋው ላይ ድልን ይቀዳጃል።
በእምነት ሁኖ የለመነውን እግዚአብሔር ይሰጠዋል። ሰማያዊ የሆነውን
ምስጢር ለማየት ከአለማዊ ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል።
በአለም እየኖረ ከአለሙ ይለያል። ከአለም አይደለምና//
ዮሐ፲፭÷፲፱//15*19 //
2ኛ.
ዐቢይ ጾምም ቤተክርስቲያናችን እንድንጾም ካወጀችልን ጾም አንዱ ነው፡፡
ዐቢይ ጾምየተለያዩ ስሞች አሉት፡፡ አንደኛ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም በመሆኑ እንዲሁም ዐቢይ
እግዚአብሔር ወዓቢይ ኀይሉ ዓቢይ እግዚአብሔር ወብዙኃ አኰቴቱ የተባለ
ጌታ የጾመው ስለሆነ፣ /መዝ.47፥1፣ መዝ.146፥5/፡፡ ሁለተኛ ሁዳዴ ጾም
ይባላል፡፡ ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት
ሥራ ሁዳድ ስለሚባል ሲሆን ከአጽዋማት ሁሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ኃያሉ
አምላካችን ስለጾመው ነው፡፡፣ /አሞ.7፥1/፡፡ ሦስተኛ በዓተ ጾም ይባላል፡፡
የጾም መግቢያ፣ መባቻ ወይም ጾሙ የሚሰፍርበት በዓት ማለት ነው፡፡ አራተኛ
ጾመ አርባ ይባላል፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው 40 /ዓርባ/ ቀን
ስለሆነ፣ /ማቴ.4፥1/ አምስተኛ ጾመ ኢየሱስይባላል፡፡ ጾሞ፣ ጹሙ ብሎ
ስላዘዘን፣ ስድስተኛ ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዘወረደ ሰኞ ዕዝል
ከመዝ ይቤ ሙሴ እስመ ለዓለም፣ ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት እያለ በጾመ
ድጓ ስለ ዘመረ ነው፡፡
ዐቢይ ጾምጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው፡፡ ማቴ.4፥1
ምእመናን ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል፡፡ ዐቢይ ጾም
ስምንት ሳምንታት /55 ቀኖች/ አሉት፡፡ ሰባት ቅዳሜ ስምንት እሑድ ይገኛሉ፡፡
አሥራ አምስት ቀን ማለት ነው፡፡ ከጥሉላት እንጂ ከእህል ውኃ ስለማይጦሙ
የጦሙ ወራት አርባ ቀን ብቻ ይሆናል፡፡
3ኛ.
የአቢይ ጾም ሦስቱ ክፍሎች
1. ዘወረደ (ጾመ ሕርቃል)፤ ይህም ጾሙ ከሚገባበት
ሰኞ ጀምሮ እስከ እሑድ ያረስ ያለው 7 ቀን ነው።
2. የጌታ ጾም፤ ይህም ከቅድስት ሰኞ እስከ ሆሣዕና
ዋዜማ ዓርብ ድረስ ያለው 40 ቀን ነው።
3. ሕማማት፤ ይህም ጌታችን በአልዓዛር ቤት ለማዕድ
ከተቀመጠበት የሆሳዕና ቅዳሜ ጀምሮ እስከ ሥዑር
ቅዳሜ ያለው መከራን የተቀበለበት 8 ቀን ሕማማት
ነው።
ይህም 7+40+8 = 55 ቀን ማለት ነው።
4ኛ.
የአብይ ጾም ሳምንታት 8 ናቸው፤
ዘወረደ
ቅድስት
ምኩራብ
መጻጉዕ
ደብረዘይት
ገብርሔር
ኒቆዲሞስ
ሆሣዕ
ሰለ ተትርጉማቸው ከታች ከተለጠፈው ሰንጠረዥ ተመልከት
5ኛ. ለምን አብይ / ታላቅ
ተባለ
አብይ ፆም መባሉ ትልቅና ታላቅ ፆም መሆኑን
ለማሳወቅ ነው። ይህ ፆም ታላቅ
መባሉም ለ55 ቀናት ያህል መፆሙና
ከሌሎቹ አፅዋማት ጋር ሲነፃፀር በቁጥር
መብለጡ ብቻ ሳይሆን ጌታችን አምላካችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ
ቆሮንቶስ መፆም ሳይገባው ለእኛ አርአያና
ትልቅ ምሳሌ ለመሆን የፆመው ፆምም
በመሆኑ ነው
6ኛኛ.
የመጀመሪያ የአቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም
ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ ስያሜውም፤ በ 614 ዓ . ም ኪርዮስ የተባለ
የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ፡፡ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ ቅድሳት ዘርፎ 60 ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3 ሺ የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ 14 ዓመት በኋላ በ 628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው አላቸው እኛ የአንተን እድሜ ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
የካቲት 15/06/2012
✝ምስባክ
+ ዘነግህ
1 📖መዝ. 101/102፥21
----------------
ከመ ይንግሩ በጽዮን ስመ እግዚአብሔር ወስብሐቲሁኒ በኢየሩሳሌም ሶበ ተጋብኡ አሕዛብ ኅቡረ
+ ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 146/147፥፡1
----------------
ተሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን እስመ አጽንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ
✝ትርጉም
1:- የእግዚአብሔርን ስም በጽዮን ምስጋናውንም በኢየሩሳሌም ይናገሩ ዘንድ
2:- እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና። ለአምላካችን ምስጋና ያማረ ነው ፤ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይሠራል፥ ከእስራኤልም የተበተኑትን ይሰበስባል
@aleroe
የካቲት 15/06/2012
✝ምስባክ
+ ዘነግህ
1 📖መዝ. 101/102፥21
----------------
ከመ ይንግሩ በጽዮን ስመ እግዚአብሔር ወስብሐቲሁኒ በኢየሩሳሌም ሶበ ተጋብኡ አሕዛብ ኅቡረ
+ ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 146/147፥፡1
----------------
ተሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን እስመ አጽንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ
✝ትርጉም
1:- የእግዚአብሔርን ስም በጽዮን ምስጋናውንም በኢየሩሳሌም ይናገሩ ዘንድ
2:- እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና። ለአምላካችን ምስጋና ያማረ ነው ፤ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይሠራል፥ ከእስራኤልም የተበተኑትን ይሰበስባል
@aleroe
ኤልሮኢ:
#እያለፈ_ነው_ዘመኔ
እያለፈ ነው ዘመኔ ትእዛዙን ሳልፈጽም
ወየው ለእኔ/2/
በጠራኝ ጊዜ ምን እላለሁ
ና ብሎ ወደእኔ/2/
በወጣትነቴ ሳልሠራ እያየሁ አለፈኝ
ብዙ አዝመራ/2/
ከእንግዲህ በመሥራት ጌታ ሆይ
ልኑር ከአንተ ጋራ/2/
የማስብበት በየለእቱ ንጹሕ ልብን
ስጠኝ አቤቱ /2/
ከትእዛዝህ ውጪ በመሆን
እዳልቀር በከንቱ /2/
እንደየሥራው ለመስጠት
በግርማ መንግሥቱ ሲመጣ/2/
ማን ይሆን የሚቆም ከፊቱ
ፊተናን የወጣ/2/
እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ
እየተማራችሁ ከቃሉ/2/
ይመጣሉና በእርሱ ስም
አምላክ ነን የሚሉ/2/
ትእግሥትን በመያዝ ሁላችሁ
እስከመጨረሻው ጠንክሩ/2/
ያን ጊዜ ይሆናል በእርሱ ዘንድ
የማዳን ተግባሩ/2/
@aleroe
#እያለፈ_ነው_ዘመኔ
እያለፈ ነው ዘመኔ ትእዛዙን ሳልፈጽም
ወየው ለእኔ/2/
በጠራኝ ጊዜ ምን እላለሁ
ና ብሎ ወደእኔ/2/
በወጣትነቴ ሳልሠራ እያየሁ አለፈኝ
ብዙ አዝመራ/2/
ከእንግዲህ በመሥራት ጌታ ሆይ
ልኑር ከአንተ ጋራ/2/
የማስብበት በየለእቱ ንጹሕ ልብን
ስጠኝ አቤቱ /2/
ከትእዛዝህ ውጪ በመሆን
እዳልቀር በከንቱ /2/
እንደየሥራው ለመስጠት
በግርማ መንግሥቱ ሲመጣ/2/
ማን ይሆን የሚቆም ከፊቱ
ፊተናን የወጣ/2/
እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ
እየተማራችሁ ከቃሉ/2/
ይመጣሉና በእርሱ ስም
አምላክ ነን የሚሉ/2/
ትእግሥትን በመያዝ ሁላችሁ
እስከመጨረሻው ጠንክሩ/2/
ያን ጊዜ ይሆናል በእርሱ ዘንድ
የማዳን ተግባሩ/2/
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
፨ጊዜዬን ባርክልኝ፨
በዝናብ አብቅለህ በፀሐይ አብስለህ
የምትመግብ ጌታ ሁሉን አዘጋጅተህ
ነጻነቱን ሰጥተህ ጥበቡን አድለህ
እዚህ ላደረስከኝ ምስጋና ይድረስህ
ሁሌም ጠብቀኸኝ በምሕረት ጥላ
ጊዜን ባርክልኝ ሰርቼ እንድበላ
ከፍጥረታት ሁሉ አልቀህ ፈጥረኸኝ
የጸጋን ገዢነት በፍቅርህ አድለኸኝ
ከቤትህ እንድኖር ርስትአውረሰኸኝ
ለዚህ ያበቃህኝ ከቶ እኔ ማነኝ
ያለኝ ምስጋና ነው አምላክ ክበርልኝ
እኔ ስበድልህ አንተ ስትምረኝ
በምሕረት ታግለህ ፈጥነህ ሳታጠፋኝ
ንስሐ እንድገባ ጊዜን ባርክልኝ።
@aleroe
፨ጊዜዬን ባርክልኝ፨
በዝናብ አብቅለህ በፀሐይ አብስለህ
የምትመግብ ጌታ ሁሉን አዘጋጅተህ
ነጻነቱን ሰጥተህ ጥበቡን አድለህ
እዚህ ላደረስከኝ ምስጋና ይድረስህ
ሁሌም ጠብቀኸኝ በምሕረት ጥላ
ጊዜን ባርክልኝ ሰርቼ እንድበላ
ከፍጥረታት ሁሉ አልቀህ ፈጥረኸኝ
የጸጋን ገዢነት በፍቅርህ አድለኸኝ
ከቤትህ እንድኖር ርስትአውረሰኸኝ
ለዚህ ያበቃህኝ ከቶ እኔ ማነኝ
ያለኝ ምስጋና ነው አምላክ ክበርልኝ
እኔ ስበድልህ አንተ ስትምረኝ
በምሕረት ታግለህ ፈጥነህ ሳታጠፋኝ
ንስሐ እንድገባ ጊዜን ባርክልኝ።
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
……✍ከእለታት አንድ ቀን አንድ አባት ወደ አባታችን አባ መቃርዮስ በኣት ሄደና "አባቴ ሆይ ድኅነትን አገኝ ዘንድ ምን ላድርግ?" ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው። አባታችንም እንዲህ በማለት አሉት።
"ወደ መቃብር ሂድና ሙታንን ሰድበሃቸው ና" አሉት። ይህ አባትም የተባለውን አድርጎ ተመለሰ። አባታችንም "ምን አሉህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየዉም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባ መቃርዮስም "አሁን ደግሞ ሂድና ሙታንን አመስግናቸው" አሉት። ሄዶም አመሰገናቸው። "አሁንስ ምን አሉህ" ሲል በድጋሚ ጠየቁት። ሰውዬም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባታችን አባ መቃርዮስም: "ስትሰድባቸው ፤ስታመሰግናቸው እና ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም፤ አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደሞተ ሰው ሆነህ ኑር። ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም፣ ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አሉት።
======================
@aleroe
……✍ከእለታት አንድ ቀን አንድ አባት ወደ አባታችን አባ መቃርዮስ በኣት ሄደና "አባቴ ሆይ ድኅነትን አገኝ ዘንድ ምን ላድርግ?" ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው። አባታችንም እንዲህ በማለት አሉት።
"ወደ መቃብር ሂድና ሙታንን ሰድበሃቸው ና" አሉት። ይህ አባትም የተባለውን አድርጎ ተመለሰ። አባታችንም "ምን አሉህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየዉም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባ መቃርዮስም "አሁን ደግሞ ሂድና ሙታንን አመስግናቸው" አሉት። ሄዶም አመሰገናቸው። "አሁንስ ምን አሉህ" ሲል በድጋሚ ጠየቁት። ሰውዬም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባታችን አባ መቃርዮስም: "ስትሰድባቸው ፤ስታመሰግናቸው እና ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም፤ አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደሞተ ሰው ሆነህ ኑር። ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም፣ ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አሉት።
======================
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ምክረ አበው
“ #እምነት-አለኝ” ብሎ ምግባር የሌለው ሰውና፥ “ምግባር አለኝ” ብሎ እምነት የሌለው ሰው እኩል ናቸው፤ ኹለቱም መንግሥተ ሰማያት አይገቡም፡፡
ስለዚህ “እምነት አለን” ብለን ልል ዘሊላን አንኹን ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላልና፡- “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም” (ማቴ.7፡21)፡፡
ስለዚህ እምነት እንደሌላቸው ሰዎች ከመንግሥተ ሰማያት ውፁአን እንዳንኾን #የእግዚአብሔርን ፈቃድ ነቅተን እንሥራ፡፡ ምግባር ትሩፋትን ተግተን እንሥራ፡፡ አምነን ልጅነትን ከተቀበልን በኋላ ልጅነታችንን አጽንተን የምንጠብቀው፣ ርስቱንና መንግሥቱንም የምንወርሰው ይህን ያደረግን እንደ ኾነ ነውና ነቅተን እንሥራ፡፡
እኛ ሥራ ሠርተን አንበቃምና ጽዋ ተርታችን ዕድል ፈንታችን ይህ ይኾን ዘንድ ከባሕርይ አባ ከአብ፣ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነቱ፣ ኃይሉና ክብሩ አንድ የሚኾን ጌታችንና መድኃኒታችን በቸርነቱና ሰውን በመውደዱ ይርዳን፤ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ አሜን!!!
@aleroe
ምክረ አበው
“ #እምነት-አለኝ” ብሎ ምግባር የሌለው ሰውና፥ “ምግባር አለኝ” ብሎ እምነት የሌለው ሰው እኩል ናቸው፤ ኹለቱም መንግሥተ ሰማያት አይገቡም፡፡
ስለዚህ “እምነት አለን” ብለን ልል ዘሊላን አንኹን ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላልና፡- “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም” (ማቴ.7፡21)፡፡
ስለዚህ እምነት እንደሌላቸው ሰዎች ከመንግሥተ ሰማያት ውፁአን እንዳንኾን #የእግዚአብሔርን ፈቃድ ነቅተን እንሥራ፡፡ ምግባር ትሩፋትን ተግተን እንሥራ፡፡ አምነን ልጅነትን ከተቀበልን በኋላ ልጅነታችንን አጽንተን የምንጠብቀው፣ ርስቱንና መንግሥቱንም የምንወርሰው ይህን ያደረግን እንደ ኾነ ነውና ነቅተን እንሥራ፡፡
እኛ ሥራ ሠርተን አንበቃምና ጽዋ ተርታችን ዕድል ፈንታችን ይህ ይኾን ዘንድ ከባሕርይ አባ ከአብ፣ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነቱ፣ ኃይሉና ክብሩ አንድ የሚኾን ጌታችንና መድኃኒታችን በቸርነቱና ሰውን በመውደዱ ይርዳን፤ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ አሜን!!!
@aleroe
ኤልሮኢ
ማርያም ማርያም
°ማንኛውም የአለም ሰው 5 የስሜት ሕዋሳት አሉት የኢትዮጵያውያን ግን 6 ነው ስድስተኛውም ቅድስት ድንግል ማርያም ናት
+ እርጉዝ ሴት እቤት ስትመጣ የማርያም እንግዳ መጣች
+ ልትወልድ ስትል ማርያም ማርያም
+ ስትወልድ እንኳን ማርያም ማረችሽ
+ እሷ አልጋላይ ሆና ማርያም ታኑርሽ(ህ)
+ ተጠይቆ ሲወጣ ማርያም በሽልም ታውጣሽ
+ ስንጫወት የማርያም መንገድ ስጠኝ(ስጪኝ)
+ ትንሿ ጣታችንን የማርያም ጣት
+ ሰው የጠራን መስሎን ስንደነግጥ የማርያምን ብቅል እየፈጨው ነው
+ ገላችን ላይ ምልክት ስትወጣ ማርያም የሣመችኝ
ኸረ ስንቱ ይነገር እኛ እና እሷ ያለን ወዳጅነት።
መልካም የፆም ጊዜ
@aleroe
ማርያም ማርያም
°ማንኛውም የአለም ሰው 5 የስሜት ሕዋሳት አሉት የኢትዮጵያውያን ግን 6 ነው ስድስተኛውም ቅድስት ድንግል ማርያም ናት
+ እርጉዝ ሴት እቤት ስትመጣ የማርያም እንግዳ መጣች
+ ልትወልድ ስትል ማርያም ማርያም
+ ስትወልድ እንኳን ማርያም ማረችሽ
+ እሷ አልጋላይ ሆና ማርያም ታኑርሽ(ህ)
+ ተጠይቆ ሲወጣ ማርያም በሽልም ታውጣሽ
+ ስንጫወት የማርያም መንገድ ስጠኝ(ስጪኝ)
+ ትንሿ ጣታችንን የማርያም ጣት
+ ሰው የጠራን መስሎን ስንደነግጥ የማርያምን ብቅል እየፈጨው ነው
+ ገላችን ላይ ምልክት ስትወጣ ማርያም የሣመችኝ
ኸረ ስንቱ ይነገር እኛ እና እሷ ያለን ወዳጅነት።
መልካም የፆም ጊዜ
@aleroe
ኤልሮኢ:
🕐 የካቲት 22/06/2012 ዓ.ም🕖
✨✨በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ✨✨
✨✨መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ✨✨
👉 ዲያቆን
📖 1 ቆሮ. 12፥1 ወበእንተሂ ዘመንፈስ ቅዱስ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 1፥7 ወባሕቱ አዳጠ ይእዜ ሀለወክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 16÷16 ወእንዘ ነሐውር ለፀሎት ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 142/143፥1
----------------
እግዚኦ ስምዓኒ ጸሎትየ ወአፅምአኒ ስእለትየ በጽድቅከ ወስምዐኒ በርትዕከ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 142/143፥8
----------------
ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረትከ በጽባሕ እስመ ኪያከ ተወከልኩ እግዚኦ ምርሀኒ እግዚኦ ፍኖተ እንተ ባቲ አሐውር
ትርጉም
-------------
1:- አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ በእውነትህ ልመናዬን አድምጥ፥ በጽድቅህም መልስልኝ
2:- አንተን ታምኛለሁና በማለዳ ምሕረትህን አሰማኝ፤ አቤቱ፥ ነፍሴን ወደ አንተ አንሥቻለሁና የምሄድበትን መንገድ አስታውቀኝ
📖 ወንጌል
የሉቃስ ወንጌል 13÷ 10 - 17
---------------------
በሰንበትም በአንድ ምኵራብ ያስተምር ነበር ፤ እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም ፤ ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት ፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች ፤ የምኵራብ አለቃ ግን ኢየሱስ በሰንበት ስለ ፈወሰ ተቈጥቶ መለሰና ሕዝቡን። ሊሠራባቸው የሚገባ ስድስት ቀኖች አሉ፤ እንግዲህ በእነርሱ መጥታችሁ ተፈወሱ እንጂ በሰንበት አይደለም አለ ፤ ጌታም መልሶ። እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን? ፤ ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው ፤ ይህንም ሲናገር ሳለ የተቃወሙት ሁሉ አፈሩ፤ ከእርሱም በተደረገው ድንቅ ሁሉ ሕዝቡ ሁሉ ደስ አላቸው።
📖 ቅዳሴ
ግሩም
@aleroe
🕐 የካቲት 22/06/2012 ዓ.ም🕖
✨✨በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ✨✨
✨✨መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ✨✨
👉 ዲያቆን
📖 1 ቆሮ. 12፥1 ወበእንተሂ ዘመንፈስ ቅዱስ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 1፥7 ወባሕቱ አዳጠ ይእዜ ሀለወክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 16÷16 ወእንዘ ነሐውር ለፀሎት ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 142/143፥1
----------------
እግዚኦ ስምዓኒ ጸሎትየ ወአፅምአኒ ስእለትየ በጽድቅከ ወስምዐኒ በርትዕከ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 142/143፥8
----------------
ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረትከ በጽባሕ እስመ ኪያከ ተወከልኩ እግዚኦ ምርሀኒ እግዚኦ ፍኖተ እንተ ባቲ አሐውር
ትርጉም
-------------
1:- አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ በእውነትህ ልመናዬን አድምጥ፥ በጽድቅህም መልስልኝ
2:- አንተን ታምኛለሁና በማለዳ ምሕረትህን አሰማኝ፤ አቤቱ፥ ነፍሴን ወደ አንተ አንሥቻለሁና የምሄድበትን መንገድ አስታውቀኝ
📖 ወንጌል
የሉቃስ ወንጌል 13÷ 10 - 17
---------------------
በሰንበትም በአንድ ምኵራብ ያስተምር ነበር ፤ እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም ፤ ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት ፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች ፤ የምኵራብ አለቃ ግን ኢየሱስ በሰንበት ስለ ፈወሰ ተቈጥቶ መለሰና ሕዝቡን። ሊሠራባቸው የሚገባ ስድስት ቀኖች አሉ፤ እንግዲህ በእነርሱ መጥታችሁ ተፈወሱ እንጂ በሰንበት አይደለም አለ ፤ ጌታም መልሶ። እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን? ፤ ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው ፤ ይህንም ሲናገር ሳለ የተቃወሙት ሁሉ አፈሩ፤ ከእርሱም በተደረገው ድንቅ ሁሉ ሕዝቡ ሁሉ ደስ አላቸው።
📖 ቅዳሴ
ግሩም
@aleroe
ኤልሮኢ:
አንተ ነህ
አንተ ነህ ×(2)
ከቀድሞ ጀምሮ ታምር የሰራህ
ከቀድሞ ጀምሮ የወጣ ዝናህ
ትላንትናም ዛሬም ዘላለም ያለህ
የእግዚአብሄር ስም ግንብ እያፈረሰ
ቃዴስና በርኔን እያረሰረሰ
ባህር ከፍሎ ህዝብ እያሻገረ
ይኖራል ለትውልድ እየተነገረ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበቱ
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
ተናገሩ የተጎበኛችሁ
ነቀፌታችሁን ያስወገደላችሁ
ያለፋችሁ ሳይነካቹ ቀስቱ
ከአንበሳ መንጋጋ ተርፋችሁ ከእሳቱ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበት
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
ከሞት መዳን በእርሱ ነው ማምለጥ
ማንም አይከለክል እግዚአብሄር ሲሰጥ
ከመረጠ ካበቃ ለርስቱ
ሀሌሉያ መዝሙር ይምጣለት ከቤቱ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበቱ
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
#ዘማሪ ገብረ ዮሀንስ
@aleroe
አንተ ነህ
አንተ ነህ ×(2)
ከቀድሞ ጀምሮ ታምር የሰራህ
ከቀድሞ ጀምሮ የወጣ ዝናህ
ትላንትናም ዛሬም ዘላለም ያለህ
የእግዚአብሄር ስም ግንብ እያፈረሰ
ቃዴስና በርኔን እያረሰረሰ
ባህር ከፍሎ ህዝብ እያሻገረ
ይኖራል ለትውልድ እየተነገረ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበቱ
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
ተናገሩ የተጎበኛችሁ
ነቀፌታችሁን ያስወገደላችሁ
ያለፋችሁ ሳይነካቹ ቀስቱ
ከአንበሳ መንጋጋ ተርፋችሁ ከእሳቱ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበት
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
ከሞት መዳን በእርሱ ነው ማምለጥ
ማንም አይከለክል እግዚአብሄር ሲሰጥ
ከመረጠ ካበቃ ለርስቱ
ሀሌሉያ መዝሙር ይምጣለት ከቤቱ
በተዘረጋች እጅ በፀናች ጉልበቱ
በታላቅ ትድግና ይኖራል ፍጥረቱ
እግዚአብሄር ነውና ብርቱና ገናና
ለዘላለም ክብሩ ይነገራል ገና×(2)
#ዘማሪ ገብረ ዮሀንስ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
#ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ማትያስ_ቀዳማዊ_ፓትርያሪክ_ርእሰ_ሊቃነ_ጳጳሳት_ዘኢትዮጵያ_ሊቀ_ጳጳስ_ዘአክሱም_ወፅጨጌ_ዘመንበረ_ተክለ_ሀይማኖትሞ
💚💛❤️
ዛሬ 7ኛ ዓመት በዓለ ሲመት እየተከበረ ነው። ረጅም እድሜና
ጤና ይስጥልንለአባታችን
#አሜን❤️
💚💛❤️
ዛሬ 7ኛ ዓመት በዓለ ሲመት እየተከበረ ነው። ረጅም እድሜና
ጤና ይስጥልንለአባታችን
#አሜን❤️
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)
በዜሮ ይባዛል!
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@aleroe
በዜሮ ይባዛል!
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ከዝሙት የዳነችው ብላቴና
ጫማ በመጠገን የሚተዳደር አንድ ሰው ነበር፡፡ ይህም ሰው ደም ግባቷ ያማረ፣ መልከ መልካም፣ የተወደደች፣ የተባረከች መንፈሳዊ ብላቴና ነበረችው፡፡ ውጫዊ ሰውነቷ ፈጽሞ ያማረ እንደሆነ ውስጣዊ ማንነቷም በትሕትና፣ በጸሎትና በጾም ያጌጠ ነው፡፡ ከታላላቁና ከታናናሹ ሁሉ ኃጢአት ርቃ፣ በፍጹም ሐሳቧ በልቧም እመቤታችንን ትወዳት ነበር፡፡ ስሟም ማርያም ይባል ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በእመቤታችን ስዕል ፊት ተቀምጣ “እመቤቴ ሆይ! ይህ ስም ላንቺ ብቻ ነው እንጂ ለእኔ አይገባኝም፡፡ አንቺ የንጹሐን ንጽሕት ነሽና አለች፡፡ በይቅርታሽ ድንግልናዬን ትጠብቂያት ዘንድ፣ የሰይጣንን ተንኮልን ሁሉ በፍቅርሽና በጸሎትሽ ከኔ ታርቂ ዘንድ የምእመናን አለኝታቸው ሆይ! እማጸንሻለሁ” ብላ እመቤታችንን ለመነቻት፡፡
የበጎ ነገር ጠላትና የአዳም ልጆችም ሁሉ ጠላት የሚሆን ሰይጣን ከዓላማዋ ሊያናውጻት ምክንያት አመጣባት፡፡ አንድ ፈረስ ያለው ሰው በመንገድ ሲሄድ ይህቺን ብላቴና አገኛት፡፡ ይህ ባለፈረስ አጅግ ባለ ጸጋና ገንዘቡም የበዛ ነው፡፡ ይህም ሰው ሴት ወዳጅ ስለሆነ ባያት ጊዜ ፈጽሞ ወደዳት፣ በሷም ፍቅር ተነደፈ፡፡
እርሱም ይህን የዝሙት ሐሳቡን እንድታስፈጽምለት አንዲት በጎ ምግባር የሌላትን ባነጋገሯና በሥራዋ የሰውን ልቡና የምታስት፣ ባንደበቷና በልቧ ውስጥ በሚኖር ሰይጣን ማሳትና በሥራዋ የሰውን ነፍስ ወደ ሲኦል የምታወርድ መሠሪት ሴት ወደ ርሷ ላከ፡፡ ያችን ደግ ብላቴና ክፉ በሚሆን ፊቷ ለማታለል ትነጋገራት ዘንድና ታግባባት ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ደግ ብላቴና ነገሯን በሰማች ጊዜ ሐሳቧንና የውስጧን ተንኮል ዐወቀች፡፡ ፊቷንም ታጠቁር ዘንድ ሥራዋንም ትነቅፍ ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ክፉ ሴት በብላቴናዋ መልስ እያዘነችና እየተከዘች ትታት ሄደች፡፡ ከዚህ በኋላ ለፈረሰኛው ሰው ሄዳ የኾነውን ነገረችው፡፡ እርሱም በዚች ብላቴና ፍቅር ምክንያት ልቡ እንደእሳት ተቃጥሎ ነበርና፣ እርሷን የሚያገኝበትን መንገድ ሁለተኛ እንድትመክረው ጠየቃት፡፡ ያቺም የሰይጣን የግብር ልጅ የኾነች ሴት እንዲህ አለችው፡፡ “ የዚያች ብላቴና አባት ድሃ ነው፣ አንተ ግን ባለጸጋ ነህና አስጠርተህ ከገንዘብህ ከፍለህ ስጠው፣ ያን ጊዜ ልጁን ፈጥኖ ያመጣልሃል” አለችው፡፡ እርሱም በክፉ ምክሯ ተመርቶ ያለችውን አደረገ፡፡ አባቷም ያለፍቃዷ ልጁን ይዞ እያዘነች እያለቀሰች ወደ ባለጸጋው ወሰዳት፡፡ ብላቴናዋም ሊታደጋት የሚችል ረዳትና ኃይል እንደሌለ ባወቀች ጊዜ አምላክን ወደ ወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደጸናች ክብርት እመቤታችን ጮኻ ለመነች፡፡ “ ሰውን የምትወጂ እመቤቴ ከእኔ አትራቂ” አለቻት፡፡ “የድኾች አለኝታቸው የምትሆኝ የተቸገሩትን የምታድኛቸው፣ ከዚያ ሰው ያንቺ ኃይል ይጸናል፣ ይበልጣል አድኚኝ እያለች ለመነቻት፡፡ ያም ባለጸጋ ብዙ ለቅሶዋንና ኀዘንዋን በሰማ ጊዜ “ለምን እንዲህ አድርገሽ ታዝኛለሽ፣ ታለቅሺያለሽ ኣላት” እኔስ ከሕጻነቴ ጀምሮ ድንግልናዬን ነፍሴን ለእመቤታችን ተስያለሁ አለችው፡፡ አንተም የድንግልናዬን ብጽዓት አፍርሰህ ብትወስደኝ በፈታሔ ጽቅ ልጀዋ ፊት በምትቆምበት በዕለተ ትንሳኤ ጊዜ ይችው ትፈርድብሃለች” አለችው፡፡
ፈረሰኛው ከዚያች ብላቴና አንደበት የእመቤታችን ስም ሲሰማ ፍጹም ፈርቶ እጀግ አዘነ ሰውነቱም ተንቀጠቀጠ፣ ደነገጠ፡፡ ያም ባለጸጋ ባመረ ቃልና በፍጹም ፍርሃት ልትመነኩሺ ትወጃለሽን አላት፡፡ ማገልገሏን የወደድኩ፣ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንን አገለግላት ዘንድ “ አዎ እወዳለሁ” አለችው፡፡ እኔ ብዙ ገንዘብ ሰጥቼ ወደ መበለታት ገዳም ወስጄ እሰጥሻለሁ፡፡ ዳግመኛም ልብሳቸውንና ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ መበለታት ገዳም ወስዶ ይህችን ብላቴና እንደናንተ ጠብቁዋት፡፡ እኔንም በጸሎታችሁ አትርሱ ብሎ አደራ አስጠበቃቸው፡፡ ዘወትርም ይጎበኛቸው ነበር፡፡ የሚጠብቃቸውንም ያህል ብዙ ገንዘብና ምግባቸውን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ተአምረ ማርያም ተአምር ፹፮
@aleroe
ከዝሙት የዳነችው ብላቴና
ጫማ በመጠገን የሚተዳደር አንድ ሰው ነበር፡፡ ይህም ሰው ደም ግባቷ ያማረ፣ መልከ መልካም፣ የተወደደች፣ የተባረከች መንፈሳዊ ብላቴና ነበረችው፡፡ ውጫዊ ሰውነቷ ፈጽሞ ያማረ እንደሆነ ውስጣዊ ማንነቷም በትሕትና፣ በጸሎትና በጾም ያጌጠ ነው፡፡ ከታላላቁና ከታናናሹ ሁሉ ኃጢአት ርቃ፣ በፍጹም ሐሳቧ በልቧም እመቤታችንን ትወዳት ነበር፡፡ ስሟም ማርያም ይባል ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በእመቤታችን ስዕል ፊት ተቀምጣ “እመቤቴ ሆይ! ይህ ስም ላንቺ ብቻ ነው እንጂ ለእኔ አይገባኝም፡፡ አንቺ የንጹሐን ንጽሕት ነሽና አለች፡፡ በይቅርታሽ ድንግልናዬን ትጠብቂያት ዘንድ፣ የሰይጣንን ተንኮልን ሁሉ በፍቅርሽና በጸሎትሽ ከኔ ታርቂ ዘንድ የምእመናን አለኝታቸው ሆይ! እማጸንሻለሁ” ብላ እመቤታችንን ለመነቻት፡፡
የበጎ ነገር ጠላትና የአዳም ልጆችም ሁሉ ጠላት የሚሆን ሰይጣን ከዓላማዋ ሊያናውጻት ምክንያት አመጣባት፡፡ አንድ ፈረስ ያለው ሰው በመንገድ ሲሄድ ይህቺን ብላቴና አገኛት፡፡ ይህ ባለፈረስ አጅግ ባለ ጸጋና ገንዘቡም የበዛ ነው፡፡ ይህም ሰው ሴት ወዳጅ ስለሆነ ባያት ጊዜ ፈጽሞ ወደዳት፣ በሷም ፍቅር ተነደፈ፡፡
እርሱም ይህን የዝሙት ሐሳቡን እንድታስፈጽምለት አንዲት በጎ ምግባር የሌላትን ባነጋገሯና በሥራዋ የሰውን ልቡና የምታስት፣ ባንደበቷና በልቧ ውስጥ በሚኖር ሰይጣን ማሳትና በሥራዋ የሰውን ነፍስ ወደ ሲኦል የምታወርድ መሠሪት ሴት ወደ ርሷ ላከ፡፡ ያችን ደግ ብላቴና ክፉ በሚሆን ፊቷ ለማታለል ትነጋገራት ዘንድና ታግባባት ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ደግ ብላቴና ነገሯን በሰማች ጊዜ ሐሳቧንና የውስጧን ተንኮል ዐወቀች፡፡ ፊቷንም ታጠቁር ዘንድ ሥራዋንም ትነቅፍ ዘንድ ጀመረች፡፡ ያችም ክፉ ሴት በብላቴናዋ መልስ እያዘነችና እየተከዘች ትታት ሄደች፡፡ ከዚህ በኋላ ለፈረሰኛው ሰው ሄዳ የኾነውን ነገረችው፡፡ እርሱም በዚች ብላቴና ፍቅር ምክንያት ልቡ እንደእሳት ተቃጥሎ ነበርና፣ እርሷን የሚያገኝበትን መንገድ ሁለተኛ እንድትመክረው ጠየቃት፡፡ ያቺም የሰይጣን የግብር ልጅ የኾነች ሴት እንዲህ አለችው፡፡ “ የዚያች ብላቴና አባት ድሃ ነው፣ አንተ ግን ባለጸጋ ነህና አስጠርተህ ከገንዘብህ ከፍለህ ስጠው፣ ያን ጊዜ ልጁን ፈጥኖ ያመጣልሃል” አለችው፡፡ እርሱም በክፉ ምክሯ ተመርቶ ያለችውን አደረገ፡፡ አባቷም ያለፍቃዷ ልጁን ይዞ እያዘነች እያለቀሰች ወደ ባለጸጋው ወሰዳት፡፡ ብላቴናዋም ሊታደጋት የሚችል ረዳትና ኃይል እንደሌለ ባወቀች ጊዜ አምላክን ወደ ወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደጸናች ክብርት እመቤታችን ጮኻ ለመነች፡፡ “ ሰውን የምትወጂ እመቤቴ ከእኔ አትራቂ” አለቻት፡፡ “የድኾች አለኝታቸው የምትሆኝ የተቸገሩትን የምታድኛቸው፣ ከዚያ ሰው ያንቺ ኃይል ይጸናል፣ ይበልጣል አድኚኝ እያለች ለመነቻት፡፡ ያም ባለጸጋ ብዙ ለቅሶዋንና ኀዘንዋን በሰማ ጊዜ “ለምን እንዲህ አድርገሽ ታዝኛለሽ፣ ታለቅሺያለሽ ኣላት” እኔስ ከሕጻነቴ ጀምሮ ድንግልናዬን ነፍሴን ለእመቤታችን ተስያለሁ አለችው፡፡ አንተም የድንግልናዬን ብጽዓት አፍርሰህ ብትወስደኝ በፈታሔ ጽቅ ልጀዋ ፊት በምትቆምበት በዕለተ ትንሳኤ ጊዜ ይችው ትፈርድብሃለች” አለችው፡፡
ፈረሰኛው ከዚያች ብላቴና አንደበት የእመቤታችን ስም ሲሰማ ፍጹም ፈርቶ እጀግ አዘነ ሰውነቱም ተንቀጠቀጠ፣ ደነገጠ፡፡ ያም ባለጸጋ ባመረ ቃልና በፍጹም ፍርሃት ልትመነኩሺ ትወጃለሽን አላት፡፡ ማገልገሏን የወደድኩ፣ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንን አገለግላት ዘንድ “ አዎ እወዳለሁ” አለችው፡፡ እኔ ብዙ ገንዘብ ሰጥቼ ወደ መበለታት ገዳም ወስጄ እሰጥሻለሁ፡፡ ዳግመኛም ልብሳቸውንና ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ መበለታት ገዳም ወስዶ ይህችን ብላቴና እንደናንተ ጠብቁዋት፡፡ እኔንም በጸሎታችሁ አትርሱ ብሎ አደራ አስጠበቃቸው፡፡ ዘወትርም ይጎበኛቸው ነበር፡፡ የሚጠብቃቸውንም ያህል ብዙ ገንዘብና ምግባቸውን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ተአምረ ማርያም ተአምር ፹፮
@aleroe
ኤልሮኢ:
የካቲት 27/06/2012 ዓ.ም
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ
መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ
👉 ዲያቆን
📖 ሮሜ. 6፥5 ወእመሰኬ ተመሰልናሁ በሞቱ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 2፥21 ወበእንተ ዝንቱ ተጸዋዕክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 10÷36 ወፈነወ ቃሎ ለደቂቀ እስራኤል ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 21/22፥16
----------------
ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 55/56፥1
----------------
ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ ወኵሎ አሚረ አሥርሐኒ ቀትል ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ ዓሚረ በኑኀ ዕለት
ትርጉም
-------------
1:- ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ
2:- አቤቱ፥ ሰው ረግጦኛልና ማረኝ፤ ሁልጊዜም በሰልፍ አስጨንቆኛል
📖 ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል 19 ÷ 16 - 30
📖 ቅዳሴ
ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
የካቲት 27/06/2012 ዓ.ም
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ
መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ
👉 ዲያቆን
📖 ሮሜ. 6፥5 ወእመሰኬ ተመሰልናሁ በሞቱ .....
👉 ንፍቅ ዲያቆን
📖 1 ጴጥ. 2፥21 ወበእንተ ዝንቱ ተጸዋዕክሙ ....
👉 ንፍቅ ካህን
📖 ግብረ ሐዋርያት 10÷36 ወፈነወ ቃሎ ለደቂቀ እስራኤል ....
👉 ምስባክ
ዘነግህ
1 📖መዝ. 21/22፥16
----------------
ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ
ዘቅዳሴ
2 📖መዝ. 55/56፥1
----------------
ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ ወኵሎ አሚረ አሥርሐኒ ቀትል ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ ዓሚረ በኑኀ ዕለት
ትርጉም
-------------
1:- ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ
2:- አቤቱ፥ ሰው ረግጦኛልና ማረኝ፤ ሁልጊዜም በሰልፍ አስጨንቆኛል
📖 ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል 19 ÷ 16 - 30
📖 ቅዳሴ
ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ምኩራብ
ምኩራብ የአብይ ጾም ሶስተኛው ሳምንት ነው።
ምኩራብ የአይሁዳውያን ቤተ መቅደስ ሲሆን
ይሄ ሳምንት ምኩራብ የተባለው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ
የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡
ማቴ ፳፩፥፲፪―፲፬ እንዲህ ይላል«ኢየሱስ ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ የሚሸጡትና የሚገዙትንም ኹሉ አወጣ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጪዎችን ወንበሮች ገለበጠና ቤቴ የፀሎት ቤት ትባላለች
ተብሎ ተፅፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችውት አላቸው።በመቅደስም እውሮችና አንካሳዎች ወደ ርሱ ቀረቡና ፈወሳቸው።»
@aleroe
ምኩራብ
ምኩራብ የአብይ ጾም ሶስተኛው ሳምንት ነው።
ምኩራብ የአይሁዳውያን ቤተ መቅደስ ሲሆን
ይሄ ሳምንት ምኩራብ የተባለው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ
የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡
ማቴ ፳፩፥፲፪―፲፬ እንዲህ ይላል«ኢየሱስ ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ የሚሸጡትና የሚገዙትንም ኹሉ አወጣ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጪዎችን ወንበሮች ገለበጠና ቤቴ የፀሎት ቤት ትባላለች
ተብሎ ተፅፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችውት አላቸው።በመቅደስም እውሮችና አንካሳዎች ወደ ርሱ ቀረቡና ፈወሳቸው።»
@aleroe
ኤልሮኢ:
ጌታችን አንጽሖተ ቤተ መቅደስን ኹለት ጊዜ መፈጸሙ በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ አንደኛው በማቴዎስ 21 ላይ የሚገኝ ታሪክ ሲኾን፡ በሆሣዕና ጊዜ በስፋት የሚነሣ ነው፡፡ ሌላኛው በዮሐንስ 2 ላይ የሚገኘው ነው፡፡ በዚህኛው ክፍል ላይ ጌታችን የፈጸመውን የአንጽሖት ግብር በ3 ዋና ዋና ንዑስ ድርጊቶች ከፍለን መማር እንችላለን፡፡
1ኛ. ጌታችን ‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ››፡፡(ዮሐ.2፡13-14)፡፡ በመቅደስ የሚነግዱትንም አየ፡፡
2ኛ. ‹‹የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።›› (ዮሐ.2፡15-16)፡፡
3ኛ. ይህንን ያዩት አይሁድም በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ›› አላቸው፡፡
ልብ በሉ! ማንጻትን የሚያስብ ሰው ኹሉ እነዚህን ሦስት ነገሮች መፈጸም አለበት፡፡ ለአንጽሖት እጅግ አስፈላጊ ነጥቦች ናቸው፡፡
1ኛ. ማየት
የመጀመሪያው፡ ልናነጻው ያሰብነውን ነገር ኼዶ ማየት ነው፡፡ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት ማንጻት አይቻልም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊያነጻ የሚፈልግ ኹሉ፡ ቤተ ክርስቲያንን በደንብ ሊያያት፣ ወደ እርሷ ኼዶ ሊያገኛት፡ ሊያውቃትና ሊረዳት ይገባል፡፡ የዚያን ጊዜ በሬ ሻጮቹ፣ በግ ነጋዴዎቹና ርግብ ሻጮቹ ቁልጭ ብለው ይታዩታል፡፡ ኢትዮጵያንም ሊያነጻ የሚወድ በቅድሚያ ይቅረባት፣ በደንብ ይያት፣ ነጋዴዎቹ የቱጋ እንደ መሸጉ ይለይ፡፡ ራሱንም ሊያነጻ የሚወድ ቢኾን እንኳ፡ ‹‹ካህን›› ወይም ‹‹የንስሐ አባት›› በተባሉ መስታወቶች ራሱን በቅድሚያ በደንብ ማየት አለበት፡፡ ‹‹ራስህን ለካህን አሳይ፥ … ስለ መንጻትህ … መሥዋዕት አቅርብ›› እንዲል፡፡ (ሉቃ.5፡14)፡፡ ካህናት ‹‹አዕይንተ እግዚአብሔር / የእግዚአብሔር ዐይኖች›› ይባላሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ፣ ሀገርም ፣ እኛም በዚህ ዐይን ካልታየን ዕድፋችን አይለይምና መንጻት ከባድ ይኾናል፡፡
2ኛ. ማጽዳት
ጌታችን በመቅደስ ውስጥ የሚሠራውን ካየ በኋላ፡ በቅድሚያ ማጽጃውን ጅራፍ አዘጋጀ፡፡ ከዚያም በሬና በጎችን በጅራፍ አባረረ፤ ጅራፍ የማይችሉትን ርግቦችን ግን ባለቤቶቻቸው እንዲያስወጧቸው አዘዘ፡፡
ለቆሻሻ ኹሉ ማጽጃው አንድ አይደለም፡፡ መጥረጊያ ኹሉን አያጸዳም፡፡ መወልወያም እንዲሁ፡፡ ልብስ በሚታጠብበት የምግብ ዕቃ፣ ዕቃ በሚታጠብበትም ቤት አይታጠብም፡፡ ስለዚህ ለየትኛው ቆሻሻ ምን ዓይነት ማጽጃ እንደሚያስፈልግ በደንብ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የበሬውን ማጽጃ ለርግብ የሚጠቀም አጽጂ፡ በርግጥም አጽጂ ሊባል አይችልም፡፡ በባሕርይዋ ንጽሕት በኾነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሰዎች ምክንያት ጉድለት ቢገኝ፡ ‹‹ይህ የእነ እገሌ ሥራ ነው፡፡ ጳጳሱ እያሉ፣ መምህሩ እያሉ፣ ቄሱ እያሉ… እኔ ምን ቤት ነኝ›› አይባልም፡፡ ጉድለቱን ሥርዐት በሚፈቅደው መልኩ ለማስወገድ መጣር እንጂ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ‹‹የአባታችን ቤት›› ናት፡፡ የአባት ቤት ውስጥ ደግሞ ቆሻሻ ታይቶ አይታለፍም፡፡ ስለዚህ የምንወስደው ኹለተኛ ትምህርት አይቶ እንዳላየ ዝም ማለት ሳይኾን ለተግባር መንቀሳቀስን ነው፡፡
ጠያቂዎች ፣ ጌታችን ነጋዴዎቹን ሲያባርር፡ አይሁድ በጠያቂነት ተቃውመው ተነሥተው ነበር፡፡ በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ሲጠይቁት ነበር፡፡ እርሱም የጠየቁትን ምልክት ነገራቸው፡፡ እነርሱ ግን በሌላ ተረዱት፡፡ ‹‹ቤተ መቅደስ›› ሲል እነርሱ ሲሠራ ዓመታትን ስለ ፈጀው ቤተ መቅደስ ያስቡ ነበር፤ ‹‹እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር››፡፡ (ዮሐ.2፡21)፡፡
ማንጻት ስትጀምሩ፣ መልካም ሥራን ‹ሀ› ብላችሁ ስትወጥኑ ጠያቂና አድካሚ ተቃዋሚ አታጡም፡፡ ጠያቂውን ዝም የሚያሰኝ፣ ተቃዋሚውንም የሚቋቋም ዝግጅት ከሌላችሁ የጸዳው ቤት ተመልሶ መቆሸሹ አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሥራው እያቆሸሹ መልሶ ማጽዳት እንዳይኾን እንዲህ ዓይነት ዝግጅትም ማድረግ ይገባል፡፡ ለሚጠይቁና ለሚቃወሙ ተገቢውን ምላሽ መስጠት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ኹኑ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (1ጴጥ.3፡15)፡፡ ይህ ደግሞ ካለ በቂ ትምህርትና ጸሎት አይኾንም፡፡
የሚገርመው ግን ተቃዋሚዎች ሥራቸው መቃወም ብቻ ስለ ኾነ እንኳን ሳትመልሱ ይቅርና በቂ ምላሽን ብትሰጡም ሊያጣምሙት ይችላሉ፡፡ ስለ ሰውነታችሁ እያወራችሁላቸው ስለ ሕንጻ አወራ ብለው ተቃውሟቸውን ይገፉበታል፡፡ የዚህን ጊዜ ‹‹ውሾች ይጮኻሉ፡ ግመሎቹ ግን ይጓዛሉ›› ብሎ መቀጠል ተገቢ ነው፡፡
@aleroe
ጌታችን አንጽሖተ ቤተ መቅደስን ኹለት ጊዜ መፈጸሙ በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ አንደኛው በማቴዎስ 21 ላይ የሚገኝ ታሪክ ሲኾን፡ በሆሣዕና ጊዜ በስፋት የሚነሣ ነው፡፡ ሌላኛው በዮሐንስ 2 ላይ የሚገኘው ነው፡፡ በዚህኛው ክፍል ላይ ጌታችን የፈጸመውን የአንጽሖት ግብር በ3 ዋና ዋና ንዑስ ድርጊቶች ከፍለን መማር እንችላለን፡፡
1ኛ. ጌታችን ‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ››፡፡(ዮሐ.2፡13-14)፡፡ በመቅደስ የሚነግዱትንም አየ፡፡
2ኛ. ‹‹የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።›› (ዮሐ.2፡15-16)፡፡
3ኛ. ይህንን ያዩት አይሁድም በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ›› አላቸው፡፡
ልብ በሉ! ማንጻትን የሚያስብ ሰው ኹሉ እነዚህን ሦስት ነገሮች መፈጸም አለበት፡፡ ለአንጽሖት እጅግ አስፈላጊ ነጥቦች ናቸው፡፡
1ኛ. ማየት
የመጀመሪያው፡ ልናነጻው ያሰብነውን ነገር ኼዶ ማየት ነው፡፡ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት ማንጻት አይቻልም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊያነጻ የሚፈልግ ኹሉ፡ ቤተ ክርስቲያንን በደንብ ሊያያት፣ ወደ እርሷ ኼዶ ሊያገኛት፡ ሊያውቃትና ሊረዳት ይገባል፡፡ የዚያን ጊዜ በሬ ሻጮቹ፣ በግ ነጋዴዎቹና ርግብ ሻጮቹ ቁልጭ ብለው ይታዩታል፡፡ ኢትዮጵያንም ሊያነጻ የሚወድ በቅድሚያ ይቅረባት፣ በደንብ ይያት፣ ነጋዴዎቹ የቱጋ እንደ መሸጉ ይለይ፡፡ ራሱንም ሊያነጻ የሚወድ ቢኾን እንኳ፡ ‹‹ካህን›› ወይም ‹‹የንስሐ አባት›› በተባሉ መስታወቶች ራሱን በቅድሚያ በደንብ ማየት አለበት፡፡ ‹‹ራስህን ለካህን አሳይ፥ … ስለ መንጻትህ … መሥዋዕት አቅርብ›› እንዲል፡፡ (ሉቃ.5፡14)፡፡ ካህናት ‹‹አዕይንተ እግዚአብሔር / የእግዚአብሔር ዐይኖች›› ይባላሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ፣ ሀገርም ፣ እኛም በዚህ ዐይን ካልታየን ዕድፋችን አይለይምና መንጻት ከባድ ይኾናል፡፡
2ኛ. ማጽዳት
ጌታችን በመቅደስ ውስጥ የሚሠራውን ካየ በኋላ፡ በቅድሚያ ማጽጃውን ጅራፍ አዘጋጀ፡፡ ከዚያም በሬና በጎችን በጅራፍ አባረረ፤ ጅራፍ የማይችሉትን ርግቦችን ግን ባለቤቶቻቸው እንዲያስወጧቸው አዘዘ፡፡
ለቆሻሻ ኹሉ ማጽጃው አንድ አይደለም፡፡ መጥረጊያ ኹሉን አያጸዳም፡፡ መወልወያም እንዲሁ፡፡ ልብስ በሚታጠብበት የምግብ ዕቃ፣ ዕቃ በሚታጠብበትም ቤት አይታጠብም፡፡ ስለዚህ ለየትኛው ቆሻሻ ምን ዓይነት ማጽጃ እንደሚያስፈልግ በደንብ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የበሬውን ማጽጃ ለርግብ የሚጠቀም አጽጂ፡ በርግጥም አጽጂ ሊባል አይችልም፡፡ በባሕርይዋ ንጽሕት በኾነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሰዎች ምክንያት ጉድለት ቢገኝ፡ ‹‹ይህ የእነ እገሌ ሥራ ነው፡፡ ጳጳሱ እያሉ፣ መምህሩ እያሉ፣ ቄሱ እያሉ… እኔ ምን ቤት ነኝ›› አይባልም፡፡ ጉድለቱን ሥርዐት በሚፈቅደው መልኩ ለማስወገድ መጣር እንጂ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ‹‹የአባታችን ቤት›› ናት፡፡ የአባት ቤት ውስጥ ደግሞ ቆሻሻ ታይቶ አይታለፍም፡፡ ስለዚህ የምንወስደው ኹለተኛ ትምህርት አይቶ እንዳላየ ዝም ማለት ሳይኾን ለተግባር መንቀሳቀስን ነው፡፡
ጠያቂዎች ፣ ጌታችን ነጋዴዎቹን ሲያባርር፡ አይሁድ በጠያቂነት ተቃውመው ተነሥተው ነበር፡፡ በምን ሥልጣኑ ይህን እንደሚያደርግ ሲጠይቁት ነበር፡፡ እርሱም የጠየቁትን ምልክት ነገራቸው፡፡ እነርሱ ግን በሌላ ተረዱት፡፡ ‹‹ቤተ መቅደስ›› ሲል እነርሱ ሲሠራ ዓመታትን ስለ ፈጀው ቤተ መቅደስ ያስቡ ነበር፤ ‹‹እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር››፡፡ (ዮሐ.2፡21)፡፡
ማንጻት ስትጀምሩ፣ መልካም ሥራን ‹ሀ› ብላችሁ ስትወጥኑ ጠያቂና አድካሚ ተቃዋሚ አታጡም፡፡ ጠያቂውን ዝም የሚያሰኝ፣ ተቃዋሚውንም የሚቋቋም ዝግጅት ከሌላችሁ የጸዳው ቤት ተመልሶ መቆሸሹ አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሥራው እያቆሸሹ መልሶ ማጽዳት እንዳይኾን እንዲህ ዓይነት ዝግጅትም ማድረግ ይገባል፡፡ ለሚጠይቁና ለሚቃወሙ ተገቢውን ምላሽ መስጠት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ኹኑ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (1ጴጥ.3፡15)፡፡ ይህ ደግሞ ካለ በቂ ትምህርትና ጸሎት አይኾንም፡፡
የሚገርመው ግን ተቃዋሚዎች ሥራቸው መቃወም ብቻ ስለ ኾነ እንኳን ሳትመልሱ ይቅርና በቂ ምላሽን ብትሰጡም ሊያጣምሙት ይችላሉ፡፡ ስለ ሰውነታችሁ እያወራችሁላቸው ስለ ሕንጻ አወራ ብለው ተቃውሟቸውን ይገፉበታል፡፡ የዚህን ጊዜ ‹‹ውሾች ይጮኻሉ፡ ግመሎቹ ግን ይጓዛሉ›› ብሎ መቀጠል ተገቢ ነው፡፡
@aleroe
ቀኑ መጋቢት 5 ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤
“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው
መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ
ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን
አልተቻላቸውም አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ
የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን
ጽሕሙ አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ
ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ
ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር
ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።“ወዳጄ
ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል #ቃል_ኪዳን_እገባልሃለው_ስምህን_የጠራ_መታሰቢያህን_ያደረገውን_እጣን_ቋጥሮ_ግብር
ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት
መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም “#አቤቱ_ጌታ_ሆይ_የኢትዮጰያን
ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም
ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም
ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ
ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤
ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ
የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ
ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን
ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን መጋቢት 5
ሩጫውን ጨረሰ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
(መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት)
@aleroe
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤
“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው
መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ
ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን
አልተቻላቸውም አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ
የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን
ጽሕሙ አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ
ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ
ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር
ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።“ወዳጄ
ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል #ቃል_ኪዳን_እገባልሃለው_ስምህን_የጠራ_መታሰቢያህን_ያደረገውን_እጣን_ቋጥሮ_ግብር
ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት
መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም “#አቤቱ_ጌታ_ሆይ_የኢትዮጰያን
ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም
ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም
ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ
ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤
ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ
የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ
ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን
ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን መጋቢት 5
ሩጫውን ጨረሰ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
(መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት)
@aleroe