ኤልሮኢ:
እሰይ እሰይ
===========
እሰይ እሰይ ተወለደ
እሰይ እሰይ ተጠመቀ
ከሰማየ ሰማያት ወረደ
ከድንግል ማርያም ተወለደ/4/
አዝ--------------//
እሱ ባይወለድ እሰይ እሰይ
ቸሩ አምላካችን እሰይ እሰይ
እርሱ ባይጠመቅ እሰይ እሰይ
መደኃኒታችን እሰይ እሰይ
መች ትገኝ ነበር እሰይ እሰይ
ገነት ርስታችን እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
ብርሃን ወጣላቸው እሰይ እሰይ
በእውነት ወገኖቹ እሰይ እሰይ
በጨለማው ጉዞ እሰይ እሰይ
እንዳይሰላቹ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እንደ ጠል ወረደ እሰይ እሰይ
ከሰማይ ወደኛ እሰይ እሰይ
ወገኖቹን ሊያድን እሰይ እሰይ
ከክፉ ቁራኛ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እግዚአብሔር አብ ላከ እሰይ እሰይ
እንድያ ልጁን እሰይ እሰይ
እርሱ ወዷልና እሰይ እሰይ
እንዲሁ አለሙን እሰይ እሰይ
@aleroe
እሰይ እሰይ
===========
እሰይ እሰይ ተወለደ
እሰይ እሰይ ተጠመቀ
ከሰማየ ሰማያት ወረደ
ከድንግል ማርያም ተወለደ/4/
አዝ--------------//
እሱ ባይወለድ እሰይ እሰይ
ቸሩ አምላካችን እሰይ እሰይ
እርሱ ባይጠመቅ እሰይ እሰይ
መደኃኒታችን እሰይ እሰይ
መች ትገኝ ነበር እሰይ እሰይ
ገነት ርስታችን እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
ብርሃን ወጣላቸው እሰይ እሰይ
በእውነት ወገኖቹ እሰይ እሰይ
በጨለማው ጉዞ እሰይ እሰይ
እንዳይሰላቹ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እንደ ጠል ወረደ እሰይ እሰይ
ከሰማይ ወደኛ እሰይ እሰይ
ወገኖቹን ሊያድን እሰይ እሰይ
ከክፉ ቁራኛ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እግዚአብሔር አብ ላከ እሰይ እሰይ
እንድያ ልጁን እሰይ እሰይ
እርሱ ወዷልና እሰይ እሰይ
እንዲሁ አለሙን እሰይ እሰይ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)
ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።
ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡
✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል
✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ
✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት
✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ
✞ምስጋናን አለመሻት
✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል
✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ
✞ ያለማቋረጥ መጸለይ
✞በምስጢራት መካፈል
✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር
✞በምክረ ንስሀ መጓዝ
✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር
✞ራስን መገምገም መመልከት
✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና
✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም
✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ
✞በጎ አድራጎትን መፈጸም
ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡
ይቆየን!
@aleroe
ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)
ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።
ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡
✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል
✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ
✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት
✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ
✞ምስጋናን አለመሻት
✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል
✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ
✞ ያለማቋረጥ መጸለይ
✞በምስጢራት መካፈል
✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር
✞በምክረ ንስሀ መጓዝ
✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር
✞ራስን መገምገም መመልከት
✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና
✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም
✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ
✞በጎ አድራጎትን መፈጸም
ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡
ይቆየን!
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ምን ይል ይሆን
ዛፍ ቆራጩ የዛፉን ቅርንጫፍ መልምሎ ሲያበቃ ዛፉ እንደቆመ ራሱን ከዛፉ ጋር አስሮ ከግንዱ ጋር ሊታገል ወደ ላይ ተስቦ ከጫፍ ደርሷል። አሳቡ ቅርንጫፉ ተመልምሎ ያለቀለትን ብቻውን የቆመውን ዛፍ ከላይ ጀምሮ እየቆረጠ ወደ ታች ለመውረድ ነው።
መጥረብያውን ወደ ላይ ሲያነሳ ግን ንፋሱ ወደ ኋላ እያስጎነበሰውና በፍጥነት እያቃና ያንገላታዋል። ይሄኔ በሁለት እጁ ግንዱን አፈፍ ያደርግና ዥዋዥዌ ይጫወታል።
ንፋሱ እንኳንስ ስራ ሊያሰራው ቀርቶ ለህይወቱም አስጊ ሆነ። ይሄኔ ሁሉንም ርግፍ አርጎ ዐይኖቹን ወደ ሰማይ በማቅናት "ፈጣሪዬ ሆይ ከዚህ በሰላም ካወረድከኝ በኪሴ ያለውም 50 ብር አምጥቼ አስገባለሁ" ሲል ይሳላል
ወድያው ይህን ተናግሮ ሲጨርስ ነፋሱ ይቆምና በሰላም ይወርዳል። ነገር ግን እግሩ መሬት ሲነካ ፍርሃቱ ሁሉ በኖ ስለጠፋ 50 ብሩን ለማስገባት ሳስቶ ምክንያት ይፈልግ ጀመር
"አዎ በርግጥ ከዚህ ዛፍ ላይ ካወረድከኝ ብዬ ተስያለሁ ነገር ግን የወረድኩት እኔ ራሴ ነኝ። ተሸክሞ ያወረደኝ ሳይኖር ለምንድነው 50ብሬን የማወጣው" ብሎ እራሱን በማሳመን ወደ ቤቱ ጉዞ ቀጠለ።
ዳሩ ግን ትንሽ እየተራመደ ትከሻው ቀለለውና ቢዳብሰው መጥረብያው የለም። መጥረብያው ከዛፉ ጫፍ እንደተሰካ ነው። አሁንስ ምን ይል ይሆን።
የሰው ልጅ ፍጡር ነው ሁሌ ከፈጣሪ እጅ አይወጣም እንድያው ይመስለናል እንጂ ያለ እግዚአብሔር መኖር አንችልም። ያለእኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም ይለናል ዮሐ 15፣5
@aleroe
ምን ይል ይሆን
ዛፍ ቆራጩ የዛፉን ቅርንጫፍ መልምሎ ሲያበቃ ዛፉ እንደቆመ ራሱን ከዛፉ ጋር አስሮ ከግንዱ ጋር ሊታገል ወደ ላይ ተስቦ ከጫፍ ደርሷል። አሳቡ ቅርንጫፉ ተመልምሎ ያለቀለትን ብቻውን የቆመውን ዛፍ ከላይ ጀምሮ እየቆረጠ ወደ ታች ለመውረድ ነው።
መጥረብያውን ወደ ላይ ሲያነሳ ግን ንፋሱ ወደ ኋላ እያስጎነበሰውና በፍጥነት እያቃና ያንገላታዋል። ይሄኔ በሁለት እጁ ግንዱን አፈፍ ያደርግና ዥዋዥዌ ይጫወታል።
ንፋሱ እንኳንስ ስራ ሊያሰራው ቀርቶ ለህይወቱም አስጊ ሆነ። ይሄኔ ሁሉንም ርግፍ አርጎ ዐይኖቹን ወደ ሰማይ በማቅናት "ፈጣሪዬ ሆይ ከዚህ በሰላም ካወረድከኝ በኪሴ ያለውም 50 ብር አምጥቼ አስገባለሁ" ሲል ይሳላል
ወድያው ይህን ተናግሮ ሲጨርስ ነፋሱ ይቆምና በሰላም ይወርዳል። ነገር ግን እግሩ መሬት ሲነካ ፍርሃቱ ሁሉ በኖ ስለጠፋ 50 ብሩን ለማስገባት ሳስቶ ምክንያት ይፈልግ ጀመር
"አዎ በርግጥ ከዚህ ዛፍ ላይ ካወረድከኝ ብዬ ተስያለሁ ነገር ግን የወረድኩት እኔ ራሴ ነኝ። ተሸክሞ ያወረደኝ ሳይኖር ለምንድነው 50ብሬን የማወጣው" ብሎ እራሱን በማሳመን ወደ ቤቱ ጉዞ ቀጠለ።
ዳሩ ግን ትንሽ እየተራመደ ትከሻው ቀለለውና ቢዳብሰው መጥረብያው የለም። መጥረብያው ከዛፉ ጫፍ እንደተሰካ ነው። አሁንስ ምን ይል ይሆን።
የሰው ልጅ ፍጡር ነው ሁሌ ከፈጣሪ እጅ አይወጣም እንድያው ይመስለናል እንጂ ያለ እግዚአብሔር መኖር አንችልም። ያለእኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም ይለናል ዮሐ 15፣5
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
+++ ምን ብዬ ልጸልይ? +++
በግሪክ ሀገር ሁለት ሴት ልጆቹን ያሉት አንድ አባት ነበር። በአንድ ዓመት ብቻ የሚበላለጡትን እነዚህን ሕጻናት እንደ አባትም እንደ እናትም ሆኖ ተንከባክቦ ማሳደግ የዚህ ሰው ዋነኛ ሥራው ነበር።
ስለዚህ ወጥቶ በገባ ቁጥር ልጆቹን የሚያስደስት ነገር እየገዛ ፣ የሚጠይቁትን እያሟላ በድሎት ያኖራቸው ነበር። የራሱን ሕይወት ወደ ጎን ትቶ ለልጆቹ መኖሩ ያለ ዋጋ አልቀረም። ሁለቱም ልጆቹ በጤንነት አድገው ዕድሜያቸው ለጋብቻ ደረሰ።
አባት የለፋባቸው ልጆቹን ከመዳሩ በፊት ብዙ መሰብ ነበረበት። አስተዋይ ነበርና ብዙ ሽማግሌ ቢላክበትም ልጆቹን ለመሥጠት የወሰነው ግን በጥንቃቄ ነበር። ስለዚህ ልጆቹ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እንዳይቸገሩ በማሰብ የተለያየና የማይነጥፍ መተዳደሪያ ላላቸው ወንዶች ባል እንዲሆኑ ለማድረግ ወሰነ።
እንዲህ ሲልም ያወጣና ያወርድ ጀመር :
"ሰዎች ሁልጊዜም ምግብ ያስፈልጋቸዋል ስለዚህ ገበሬ መቼም ቢሆን እህል ገዢ አያጣም። እንዲሁም ሰዎች ውኃ ለመቅዳት ምግብ ለመሥራት ሸክላ ስለሚፈልጉ ሸክላ ሠሪም ገበያ አያጣም።
ስለዚህ ልጆቼን የምሠጠው ለሸክላ ሠሪና ለገበሬ ነው" አለ። እንዳለውም አንዲቷ ልጁ የገበሬ ሚስት ሌላኛዋ ደግሞ የሸክላ ሠሪ ሚስት እንዲሆኑ ሠጣቸው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በአንድ ሰንበት ይህ ሽማግሌ ዛሬስ ልጆቼን ልጠይቅ ብሎ ተነሣ። በመጀመሪያ ወደ ገበሬው ሚስት ሔዶ ሲጫወት አረፈደ።
ተሰናብቶ ሊወጣ ሲል ልጁ እንዲህ አለችው :
"አባዬ እስካሁን ኑሮአችን ሰላም ነበር። አሁን ግን ችግር ላይ ነን። ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም ጨርሶ አልዘነበም። በዚሁ ከቀጠለ የዘራነው አይበቅልም ፣ ተክሎቻችንም ይደርቃሉ።
አባዬ አደራ! በሚመጣው ወር ከባድ ዝናም እንዲጥል ወደ ፈጣሪ ጸልይልን!"
አባት አደራውን ተቀብሎ ተሰናብቶ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ለመሔድ ጉዞውን ጀመረ።
ከሰዓት በኋላ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ሲደርስ ከሸክላ ሠሪው ባሏ ጋር በአክብሮት ተቀብለው አስተናገዱት። ከጠዋቱ የበለጠ ደስተኛ ሆኖም አሳለፈ። መሰናበቻው ላይ ግን ልጁ ተነሥታ እንዲህ አለችው:
"አባዬ ለአንተ ለጸሎተኛው አባቴና ለጠንካራው ባለቤቴ ምስጋና ይሁንና ኑሮአችን እስካሁን ጥሩ ነው። እንደምታውቀው ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም አልዘነመም። በዚህም ደስተኞች ነን። አሁን የምለምንህ አንድ ነገር ብቻ ነው።
በሜዳ ላይ ተደርድሮ እንደምታየው እጅግ ብዙ ሸክላዎች እየሠራን ነው። በሚመጣው ወር ዝናም ካልዘነመና ደረቅ ከሆነ የሠራናቸው ዕቃዎች ሁሉ ደርቀው ለገበያ ይደርሱልናል። ስለዚህ በሚመጣው ወር ዝናም እንዳይጥል ወደ ፈጣሪህ ጸልይልን"
አባት ተሰናብቶ ሲወጣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ
"ፈጣሪዬ ሆይ አንዲቱ እንዳይዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ሌላዋ እንዲዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ምን ብዬ ልጸልይ?" አለ።
ይህ አረጋዊ የእኛን ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቢያስቀድስ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም ነበር። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ የሚያነበው ምእመናን በግንባራቸው ተደፍተው የሚሰሙት "በእንተ ቅድሳት" የሚባል ጸሎት ላይ የዚህን ሽማግሌ ልብ የሚያረጋጋ ስለ ዝናም የሚጸለይ አንቀጽ አለ። እንዲህ ይላል:
"በሚሻበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ ስለ ዝናም እንማልዳለን"
"በሚሻበት" የሚለው ቃል ላይ "ሻ" ጠብቃ ትነበባለች። "በሚፈለግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ" (ኀበ ዘይትፈቀድ መካን) ማለት ነው። ቀሳውስቱም ስለ ዝናማት በሚጸልዩት መስተብቁዕ ላይ "ወደ ሚሻበት ቦታ ዝናሙን ይልክ ዘንድ" (ከመ ዝናሞ ይፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) "ወደሚሻበት ቦታ ዝናሞችህን ላክ"(ዝናማቲከ ፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) ይላሉ።
ዝናም እንደ ገበሬው ቤት የሚፈለግበት ቦታ እንዳለ ሁሉ እንደ ሸክላ ሠሪው ቤት ደግሞ የማይፈለግበት ቦታ አለና ቤተ ክርስቲያን ከፈጣሪዋ ዝናም ከመለመን አልፋ የሚያዘንምበትን ቦታም እየጠቆመች ትጸልያለች።
"ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ "
@aleroe
+++ ምን ብዬ ልጸልይ? +++
በግሪክ ሀገር ሁለት ሴት ልጆቹን ያሉት አንድ አባት ነበር። በአንድ ዓመት ብቻ የሚበላለጡትን እነዚህን ሕጻናት እንደ አባትም እንደ እናትም ሆኖ ተንከባክቦ ማሳደግ የዚህ ሰው ዋነኛ ሥራው ነበር።
ስለዚህ ወጥቶ በገባ ቁጥር ልጆቹን የሚያስደስት ነገር እየገዛ ፣ የሚጠይቁትን እያሟላ በድሎት ያኖራቸው ነበር። የራሱን ሕይወት ወደ ጎን ትቶ ለልጆቹ መኖሩ ያለ ዋጋ አልቀረም። ሁለቱም ልጆቹ በጤንነት አድገው ዕድሜያቸው ለጋብቻ ደረሰ።
አባት የለፋባቸው ልጆቹን ከመዳሩ በፊት ብዙ መሰብ ነበረበት። አስተዋይ ነበርና ብዙ ሽማግሌ ቢላክበትም ልጆቹን ለመሥጠት የወሰነው ግን በጥንቃቄ ነበር። ስለዚህ ልጆቹ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እንዳይቸገሩ በማሰብ የተለያየና የማይነጥፍ መተዳደሪያ ላላቸው ወንዶች ባል እንዲሆኑ ለማድረግ ወሰነ።
እንዲህ ሲልም ያወጣና ያወርድ ጀመር :
"ሰዎች ሁልጊዜም ምግብ ያስፈልጋቸዋል ስለዚህ ገበሬ መቼም ቢሆን እህል ገዢ አያጣም። እንዲሁም ሰዎች ውኃ ለመቅዳት ምግብ ለመሥራት ሸክላ ስለሚፈልጉ ሸክላ ሠሪም ገበያ አያጣም።
ስለዚህ ልጆቼን የምሠጠው ለሸክላ ሠሪና ለገበሬ ነው" አለ። እንዳለውም አንዲቷ ልጁ የገበሬ ሚስት ሌላኛዋ ደግሞ የሸክላ ሠሪ ሚስት እንዲሆኑ ሠጣቸው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በአንድ ሰንበት ይህ ሽማግሌ ዛሬስ ልጆቼን ልጠይቅ ብሎ ተነሣ። በመጀመሪያ ወደ ገበሬው ሚስት ሔዶ ሲጫወት አረፈደ።
ተሰናብቶ ሊወጣ ሲል ልጁ እንዲህ አለችው :
"አባዬ እስካሁን ኑሮአችን ሰላም ነበር። አሁን ግን ችግር ላይ ነን። ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም ጨርሶ አልዘነበም። በዚሁ ከቀጠለ የዘራነው አይበቅልም ፣ ተክሎቻችንም ይደርቃሉ።
አባዬ አደራ! በሚመጣው ወር ከባድ ዝናም እንዲጥል ወደ ፈጣሪ ጸልይልን!"
አባት አደራውን ተቀብሎ ተሰናብቶ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ለመሔድ ጉዞውን ጀመረ።
ከሰዓት በኋላ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ሲደርስ ከሸክላ ሠሪው ባሏ ጋር በአክብሮት ተቀብለው አስተናገዱት። ከጠዋቱ የበለጠ ደስተኛ ሆኖም አሳለፈ። መሰናበቻው ላይ ግን ልጁ ተነሥታ እንዲህ አለችው:
"አባዬ ለአንተ ለጸሎተኛው አባቴና ለጠንካራው ባለቤቴ ምስጋና ይሁንና ኑሮአችን እስካሁን ጥሩ ነው። እንደምታውቀው ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም አልዘነመም። በዚህም ደስተኞች ነን። አሁን የምለምንህ አንድ ነገር ብቻ ነው።
በሜዳ ላይ ተደርድሮ እንደምታየው እጅግ ብዙ ሸክላዎች እየሠራን ነው። በሚመጣው ወር ዝናም ካልዘነመና ደረቅ ከሆነ የሠራናቸው ዕቃዎች ሁሉ ደርቀው ለገበያ ይደርሱልናል። ስለዚህ በሚመጣው ወር ዝናም እንዳይጥል ወደ ፈጣሪህ ጸልይልን"
አባት ተሰናብቶ ሲወጣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ
"ፈጣሪዬ ሆይ አንዲቱ እንዳይዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ሌላዋ እንዲዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ምን ብዬ ልጸልይ?" አለ።
ይህ አረጋዊ የእኛን ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቢያስቀድስ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም ነበር። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ የሚያነበው ምእመናን በግንባራቸው ተደፍተው የሚሰሙት "በእንተ ቅድሳት" የሚባል ጸሎት ላይ የዚህን ሽማግሌ ልብ የሚያረጋጋ ስለ ዝናም የሚጸለይ አንቀጽ አለ። እንዲህ ይላል:
"በሚሻበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ ስለ ዝናም እንማልዳለን"
"በሚሻበት" የሚለው ቃል ላይ "ሻ" ጠብቃ ትነበባለች። "በሚፈለግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ" (ኀበ ዘይትፈቀድ መካን) ማለት ነው። ቀሳውስቱም ስለ ዝናማት በሚጸልዩት መስተብቁዕ ላይ "ወደ ሚሻበት ቦታ ዝናሙን ይልክ ዘንድ" (ከመ ዝናሞ ይፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) "ወደሚሻበት ቦታ ዝናሞችህን ላክ"(ዝናማቲከ ፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) ይላሉ።
ዝናም እንደ ገበሬው ቤት የሚፈለግበት ቦታ እንዳለ ሁሉ እንደ ሸክላ ሠሪው ቤት ደግሞ የማይፈለግበት ቦታ አለና ቤተ ክርስቲያን ከፈጣሪዋ ዝናም ከመለመን አልፋ የሚያዘንምበትን ቦታም እየጠቆመች ትጸልያለች።
"ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ "
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ይህን ያውቁ ሮሯል!!!
በተለምዶ ‹‹ አርባ አራቱ ታቦት›› እያልን የምንጠራቸው አብያተ ክርስቲያናት ያሉት በጐንደር ከተማ ሲሆን ስማቸውም የሚከተለው ነው፡፡
1. ፊት ሚካኤል
2. ፊት አቦ
3. አደባባይ ኢየሱስ
4. ግምጃ ቤት ማርያም
5. እልፍኝ ጊዮርጊስ
6. መድኃኔዓለም
7. ቅዱስ ገብርኤል
8. ጠዳ እግዚአብሔር አብ
9. አባ እንጦንዮስ
10. ደብረ ብርሃን ሥላሴ
11. አደባባይ ተክለሃይማኖት
12. ሠለስቱ ምእት
13. ልደታ ለማርያም
14. አጣጣሚ ሚካኤል
15. አቡነ ኤውስጣቴዎስ
16. ቅዱስ ሩፋኤል
17. ደፈጫ ኪዳነ ምሕረት
18. ቁስቋም ደብረ ፀሐይ
19. መጥምቁ ዮሐንስ
20. በኣታ ለማርያም
21. ቅዱስ ቂርቆስ
22. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
23. አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
24. ፈንጠር ልደታ
25. ደብረ ምጥማቅ ማርያም
26. አባ ዐቢየ እግዚእ
27. ቅዱስ ፋሲለደስ
28. ሐዋርያት
29. ቀሃ ኢየሱስ
30. አርባዕቱ እንስሳት
31. ጎንደሮች ጊዮርጊስ
32. ጎንደሮች ማርያም
33. አበራ ጊዮርጊስ
34. ብላጅግ ቅዱስ ሚካሌል
35. አባ ሳሙኤል
36. አይራ ሚካኤል
37. ጓራ ዮሐንስ
38. ወረንግቦ ጊዮርጊስ
39. አሮጌ ልደታ
40. አዘዞ ተ/ሃይማኖት
41. ምንዝሮ ተ/ሀይማኖት
42. ሰራራ ማርያም
43. ዳሞት ጊዮርጊስ
44. ጫጭቁና ማርያም
በቃል ያለ ይረሳል በ………………………
@aleroe
ይህን ያውቁ ሮሯል!!!
በተለምዶ ‹‹ አርባ አራቱ ታቦት›› እያልን የምንጠራቸው አብያተ ክርስቲያናት ያሉት በጐንደር ከተማ ሲሆን ስማቸውም የሚከተለው ነው፡፡
1. ፊት ሚካኤል
2. ፊት አቦ
3. አደባባይ ኢየሱስ
4. ግምጃ ቤት ማርያም
5. እልፍኝ ጊዮርጊስ
6. መድኃኔዓለም
7. ቅዱስ ገብርኤል
8. ጠዳ እግዚአብሔር አብ
9. አባ እንጦንዮስ
10. ደብረ ብርሃን ሥላሴ
11. አደባባይ ተክለሃይማኖት
12. ሠለስቱ ምእት
13. ልደታ ለማርያም
14. አጣጣሚ ሚካኤል
15. አቡነ ኤውስጣቴዎስ
16. ቅዱስ ሩፋኤል
17. ደፈጫ ኪዳነ ምሕረት
18. ቁስቋም ደብረ ፀሐይ
19. መጥምቁ ዮሐንስ
20. በኣታ ለማርያም
21. ቅዱስ ቂርቆስ
22. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
23. አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
24. ፈንጠር ልደታ
25. ደብረ ምጥማቅ ማርያም
26. አባ ዐቢየ እግዚእ
27. ቅዱስ ፋሲለደስ
28. ሐዋርያት
29. ቀሃ ኢየሱስ
30. አርባዕቱ እንስሳት
31. ጎንደሮች ጊዮርጊስ
32. ጎንደሮች ማርያም
33. አበራ ጊዮርጊስ
34. ብላጅግ ቅዱስ ሚካሌል
35. አባ ሳሙኤል
36. አይራ ሚካኤል
37. ጓራ ዮሐንስ
38. ወረንግቦ ጊዮርጊስ
39. አሮጌ ልደታ
40. አዘዞ ተ/ሃይማኖት
41. ምንዝሮ ተ/ሀይማኖት
42. ሰራራ ማርያም
43. ዳሞት ጊዮርጊስ
44. ጫጭቁና ማርያም
በቃል ያለ ይረሳል በ………………………
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ቤተ ክርስቲያን መሄድ ጥቅም የለውምን ?
የግብጻዊው መነኩሴ ምክር
…………✍ብዙ ጊዜ በእግረ ስጋው ወደ ቤ/ክ ይመላለስ የነበረ አንድ አማኝ ወደ አንድ አባት ሄዶ ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን መመላለሱ ስሜት አልባ እና ትርጉም የሌለው ነገር እንደሆነበት እየተማረረ እንዲህ አላቸው “ለ 30 አመታት ያህል ቤተ ክርስቲያን ተመላልሻለሁ፣ በእነዚህ አመታት ብዙ ጉባኤያትን ተካፍያለሁ፣ ቅዳሴ አስቀድሻለሁ፣ ንስሀ ገብቻለሁ. . . . . . ግን ትርጉም ያለው ነገር የለኝም፣ ካሳለፍኳቸው አገልግሎቶች ውስጥ ትዝ የሚሉኝ ብዙም የሉም፣ እንደ ትዝታ የሚታወሰኝም የለኝም፣ እንደ ብክነት አየዋለሁ . . . .ካህናቱና ሰባክያኑም ያለ ምንም ትርፍ ጊዜያቸውን እያባከኑ ያለ ይመስለኛል. . . . .”
ካህኑ በጥንቃቄ አዳመጡት፡፡ የብዙ አማኝ ችግርም እንደሆነ አስረዱት፣ ሰይጣን ሆነ ብሎ የቀየሰው ወጥመድ እንደሆነ አስታወሱትና ያለፈውን የህይወት ተሞክሯቸውን እያነሱለት እሱ እንደ ብክነት መስሎት የተመለከተው ነገር ጥቅሙ እንደነበር ነግረውት የእሱ ችግር ሰይጣን ቤተ ክርስቲያን ባሳለፋቸው 30 አመታት የተጠቀመውን እንዳይመለከት አይኑን ዘግቶት ጉድለቱን ብቻ እያሳየው ተስፋ እያስቆረጠው እንደሆነ ነግረውት የራሳቸውን ተሞክሮ በዘይቤ እንዲህ አሉት ፡-
“ትዳር የያዝኩት የዛሬ 30 አመት ነው፣ ካገባሁ 30 አመት ሞልቶኛል፡፡ በእነዚህ 30 አመታት ውስጥ ባለቤቴ ከ 32,000 በላይ የምግብ አይነት ሰርታ መግባኛለች፡፡ ሆኖም ግን አንድም ቀን እነዚህን የምግብ ዝርዝሮች ለአንድ ጊዜም ቢሆን አስታውሻቸው አላውቅም፣ የማውቀው ነገር ቢኖር ግን ይህንን ነው፡- እነዚህ ምግቦች ተንከባክበውኛል፣ በሽታ እንዳያጠቃኝ ተከላክለውልኛል፣ ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ ጥንካሬ ሰጥተውኛል፣ የነቃ አእምሮ እንዲኖረኝ አንቅተውኛል፡፡ ባለቤቴ ዛሬ በዚህ ጤንነት እንድቆም ያደረገኝን ምግብ ባትመግበኝ ኖሮ በህይወት ባልኖርኩና በሞትኩ ነበር ፣ አይነታቸው ትዝ ስላላለኝ ጥቅም የላቸውም ልል ይገባኛልን? ለዛሬ መኖሬ ምክንያት ባለፈው 30 አመታት የተመገብኳቸው ግን አሁን ትዝ የማይሉኝ ምግቦች ናቸው፣ ምግብ ሁሌም አዲስ ነው፣ የምንመገበውም እንደ አዲስ ነውና፡፡ ባልሞት እንኳን ንቁ ሆኜ ሰው የሚጠቀምበትን አገልግሎት ባላገለገልኩ እንደ አንተ አይነት ያሉትን ባልመከርኩ ነበር” ልክ እንዲሁ ላለፉት ብዙ ጊዜያት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄጄ ባይሆን ኖሮ በመንፈሴ ሞቼ በኖርኩ ነበር፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያንን ተጠግቼ ህይወቴን እንድመለከት ባልሆንኩ ነበር፤ ሌላው ቢቀር እንኳን “ያሳለፍኩት አመታት ብክነት ይሆኑ እንዴ” ያስባለኝ ቤተ ክርስቲያን መመላለሴ ነው፡፡ የሰማኋቸው፣ ያነበብኳቸው የቃል ምግቦቹ በዝተው ዛሬ እንድቆም አድርገውኛል፡፡ ጥቅሜን ማየት ተስኖኝ እንጂ ለካ ዛሬ በመንፈሴ ጤናማ ሆኜ የቆምኩት ባለፉት 30 አመታት የተመገብኳቸው አገልግሎቶች ናቸው? የዛሬ 20 እና 25 ዓመታት የተማርናቸውን ትምህርቶች ላናስታውሳቸው እንችል ይሆናል፡፡ ዛሬ መልካም አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት፣ ኃጥያት ስንሰራ የሚገስፅ አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት እዚህ በመመላለሳችን ያገኘናቸው ሀብቶች ናቸው። ለምንም ወደታች ስትወርድ እግዚአብሔር ለአንድ ነገር ወደ ላይ ያወጣሃል፡፡ የወረድክ ቢመስልህም አትመን ጌታ ወደ ላይ ለጥቅም ያወጣሃልና፡፡ በቤቱ ያለ ትርፍ እየተመላለስክ ያለህ አይምሰልህ ሽልማት ላይ ደርሰሃልና፡፡ እምነት የማይታየውን ያያል፣ የማይታመነውን ያምናል፣ የማይቻለውን ይቀበላል፡፡ ሴጣን ከቤ/ክ እንድንቀር፣ ፀሎት እርግፍ አድርገን እንድንተው ሲፈልግ ነው ያንን ማድረጋችን ምንም ጥቅም እንደሌለው ደጋግሞ ያሳስበናል። በቤቱ መመላለሳችን ግን ጥቅም አለው በረከት አለው። ማንም የአንድ ባለፀጋ ቤት ተጋብዞ ሄዶ ሳይበላ ሳይጠጣ ሚመጣ የለም፣ እኛም ከሁሉ የሚበልጠው ባለፀጋው የመድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት(ቤተክርስቲያን) ኑ ብሎ ጠርቶን ሄደን ባዶአችንን ፍፅም አንመለስም። ለእኛ አሁን ጥቅሙ ባይታየንም የመንፈስ ቅዱስ በረከት ግን እያደረብን ይሄዳል።
በቤቱ ፀንተን ለዘለዓለም እንድንኖር ይርዳን።
አሜን!
@aleroe
ቤተ ክርስቲያን መሄድ ጥቅም የለውምን ?
የግብጻዊው መነኩሴ ምክር
…………✍ብዙ ጊዜ በእግረ ስጋው ወደ ቤ/ክ ይመላለስ የነበረ አንድ አማኝ ወደ አንድ አባት ሄዶ ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን መመላለሱ ስሜት አልባ እና ትርጉም የሌለው ነገር እንደሆነበት እየተማረረ እንዲህ አላቸው “ለ 30 አመታት ያህል ቤተ ክርስቲያን ተመላልሻለሁ፣ በእነዚህ አመታት ብዙ ጉባኤያትን ተካፍያለሁ፣ ቅዳሴ አስቀድሻለሁ፣ ንስሀ ገብቻለሁ. . . . . . ግን ትርጉም ያለው ነገር የለኝም፣ ካሳለፍኳቸው አገልግሎቶች ውስጥ ትዝ የሚሉኝ ብዙም የሉም፣ እንደ ትዝታ የሚታወሰኝም የለኝም፣ እንደ ብክነት አየዋለሁ . . . .ካህናቱና ሰባክያኑም ያለ ምንም ትርፍ ጊዜያቸውን እያባከኑ ያለ ይመስለኛል. . . . .”
ካህኑ በጥንቃቄ አዳመጡት፡፡ የብዙ አማኝ ችግርም እንደሆነ አስረዱት፣ ሰይጣን ሆነ ብሎ የቀየሰው ወጥመድ እንደሆነ አስታወሱትና ያለፈውን የህይወት ተሞክሯቸውን እያነሱለት እሱ እንደ ብክነት መስሎት የተመለከተው ነገር ጥቅሙ እንደነበር ነግረውት የእሱ ችግር ሰይጣን ቤተ ክርስቲያን ባሳለፋቸው 30 አመታት የተጠቀመውን እንዳይመለከት አይኑን ዘግቶት ጉድለቱን ብቻ እያሳየው ተስፋ እያስቆረጠው እንደሆነ ነግረውት የራሳቸውን ተሞክሮ በዘይቤ እንዲህ አሉት ፡-
“ትዳር የያዝኩት የዛሬ 30 አመት ነው፣ ካገባሁ 30 አመት ሞልቶኛል፡፡ በእነዚህ 30 አመታት ውስጥ ባለቤቴ ከ 32,000 በላይ የምግብ አይነት ሰርታ መግባኛለች፡፡ ሆኖም ግን አንድም ቀን እነዚህን የምግብ ዝርዝሮች ለአንድ ጊዜም ቢሆን አስታውሻቸው አላውቅም፣ የማውቀው ነገር ቢኖር ግን ይህንን ነው፡- እነዚህ ምግቦች ተንከባክበውኛል፣ በሽታ እንዳያጠቃኝ ተከላክለውልኛል፣ ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ ጥንካሬ ሰጥተውኛል፣ የነቃ አእምሮ እንዲኖረኝ አንቅተውኛል፡፡ ባለቤቴ ዛሬ በዚህ ጤንነት እንድቆም ያደረገኝን ምግብ ባትመግበኝ ኖሮ በህይወት ባልኖርኩና በሞትኩ ነበር ፣ አይነታቸው ትዝ ስላላለኝ ጥቅም የላቸውም ልል ይገባኛልን? ለዛሬ መኖሬ ምክንያት ባለፈው 30 አመታት የተመገብኳቸው ግን አሁን ትዝ የማይሉኝ ምግቦች ናቸው፣ ምግብ ሁሌም አዲስ ነው፣ የምንመገበውም እንደ አዲስ ነውና፡፡ ባልሞት እንኳን ንቁ ሆኜ ሰው የሚጠቀምበትን አገልግሎት ባላገለገልኩ እንደ አንተ አይነት ያሉትን ባልመከርኩ ነበር” ልክ እንዲሁ ላለፉት ብዙ ጊዜያት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄጄ ባይሆን ኖሮ በመንፈሴ ሞቼ በኖርኩ ነበር፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያንን ተጠግቼ ህይወቴን እንድመለከት ባልሆንኩ ነበር፤ ሌላው ቢቀር እንኳን “ያሳለፍኩት አመታት ብክነት ይሆኑ እንዴ” ያስባለኝ ቤተ ክርስቲያን መመላለሴ ነው፡፡ የሰማኋቸው፣ ያነበብኳቸው የቃል ምግቦቹ በዝተው ዛሬ እንድቆም አድርገውኛል፡፡ ጥቅሜን ማየት ተስኖኝ እንጂ ለካ ዛሬ በመንፈሴ ጤናማ ሆኜ የቆምኩት ባለፉት 30 አመታት የተመገብኳቸው አገልግሎቶች ናቸው? የዛሬ 20 እና 25 ዓመታት የተማርናቸውን ትምህርቶች ላናስታውሳቸው እንችል ይሆናል፡፡ ዛሬ መልካም አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት፣ ኃጥያት ስንሰራ የሚገስፅ አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት እዚህ በመመላለሳችን ያገኘናቸው ሀብቶች ናቸው። ለምንም ወደታች ስትወርድ እግዚአብሔር ለአንድ ነገር ወደ ላይ ያወጣሃል፡፡ የወረድክ ቢመስልህም አትመን ጌታ ወደ ላይ ለጥቅም ያወጣሃልና፡፡ በቤቱ ያለ ትርፍ እየተመላለስክ ያለህ አይምሰልህ ሽልማት ላይ ደርሰሃልና፡፡ እምነት የማይታየውን ያያል፣ የማይታመነውን ያምናል፣ የማይቻለውን ይቀበላል፡፡ ሴጣን ከቤ/ክ እንድንቀር፣ ፀሎት እርግፍ አድርገን እንድንተው ሲፈልግ ነው ያንን ማድረጋችን ምንም ጥቅም እንደሌለው ደጋግሞ ያሳስበናል። በቤቱ መመላለሳችን ግን ጥቅም አለው በረከት አለው። ማንም የአንድ ባለፀጋ ቤት ተጋብዞ ሄዶ ሳይበላ ሳይጠጣ ሚመጣ የለም፣ እኛም ከሁሉ የሚበልጠው ባለፀጋው የመድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት(ቤተክርስቲያን) ኑ ብሎ ጠርቶን ሄደን ባዶአችንን ፍፅም አንመለስም። ለእኛ አሁን ጥቅሙ ባይታየንም የመንፈስ ቅዱስ በረከት ግን እያደረብን ይሄዳል።
በቤቱ ፀንተን ለዘለዓለም እንድንኖር ይርዳን።
አሜን!
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ልሳነ_ግዕዝ ሞክሼ_ፊደላት
ሞክሼ ፊደላት የሚባሉት አንድ አይነት ድምጽ ያላቸው ነገር ግን በቅርጽ እና በስራቸው የተለያዩ ፊደላት የሆኑ ናቸው።
በድሮ ጊዜ ግን አባቶቻችን ሀን ከ ሐ ፣ ጸን ከ ፀ... ፊደሎችን በድምጽ አወጣጥ ይለዮአቸው ነበር።
እኝህ ፊደላት በቁጥር ፱(9) ሰሆኑ
ሀ ፣ ሐ ፣ ኀ ፣ ሠ ፣ ሰ ፣ አ ፣ ዐ ፣ ጸ ፣ ፀ ናቸው።
ሀ ➺ ሃሌታው "ሀ" ይባላል።
◦ሃሌ ሉያ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ስለሆነ ሃሌታው "ሀ" ተብሏል።
ሐ ➺ ሐመሩ "ሐ" ይባላል።
◦ሐመር ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው በዚህ ፊደል ስለሆነ ነው።
ኀ ➺ ብዙኀኑ "ኀ" ይባላል
◦ብዙህ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።
አ ➺ አልፋው "አ" ይባላል።
◦አልፋ ኦሜጋ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
ዐ ➺ ዓይኑ "ዐ" ይባላል።
◦ዓይኑ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
ሠ ➺ ንጉሡ "ሠ" ይባላል።
◦ንጉሥ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለ ሆነ ነው።
ሰ ➺ እሳቱ "ሰ" ይባላል።
◦እሳት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።
ጸ ➺ ጸሎቱ "ጸ" ይባላል።
◦ጸሎት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለሆነ ነው።
ፀ ➺ ፀሐዩ "ፀ" ይባላል።
◦ፀሐይ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ነው።
✅ እነዚህ ሞክሼ ፊደላት አንዱ በአንዱ ቦታ መግባት የለበትም ምክንያቱም የትርጉም ለውጥ ያመጣሉ።
ለምሳሌ ፦
➺ ሠረቀ = ወጣ
ሰረቀ = ሰረቀ
➺ አመት = አገልጋይ
ዓመት = ዘመን
➺ ሰዐለ = ስዕል ሳለ
ሰአለ = ለመነ
➺ መሀረ = አስተማረ
መሐረ = ይቅር አለ
➺ ኀለየ = አመሰገነ
ሐለየ = አሰበ
➺ ፈጸመ = ጨረሰ
ፈፀመ = ነጨ
➺ ማኅሌት = ማመስገን
ማሕሌት = ማሰብ
@aleroe
ልሳነ_ግዕዝ ሞክሼ_ፊደላት
ሞክሼ ፊደላት የሚባሉት አንድ አይነት ድምጽ ያላቸው ነገር ግን በቅርጽ እና በስራቸው የተለያዩ ፊደላት የሆኑ ናቸው።
በድሮ ጊዜ ግን አባቶቻችን ሀን ከ ሐ ፣ ጸን ከ ፀ... ፊደሎችን በድምጽ አወጣጥ ይለዮአቸው ነበር።
እኝህ ፊደላት በቁጥር ፱(9) ሰሆኑ
ሀ ፣ ሐ ፣ ኀ ፣ ሠ ፣ ሰ ፣ አ ፣ ዐ ፣ ጸ ፣ ፀ ናቸው።
ሀ ➺ ሃሌታው "ሀ" ይባላል።
◦ሃሌ ሉያ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ስለሆነ ሃሌታው "ሀ" ተብሏል።
ሐ ➺ ሐመሩ "ሐ" ይባላል።
◦ሐመር ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው በዚህ ፊደል ስለሆነ ነው።
ኀ ➺ ብዙኀኑ "ኀ" ይባላል
◦ብዙህ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።
አ ➺ አልፋው "አ" ይባላል።
◦አልፋ ኦሜጋ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
ዐ ➺ ዓይኑ "ዐ" ይባላል።
◦ዓይኑ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
ሠ ➺ ንጉሡ "ሠ" ይባላል።
◦ንጉሥ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለ ሆነ ነው።
ሰ ➺ እሳቱ "ሰ" ይባላል።
◦እሳት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።
ጸ ➺ ጸሎቱ "ጸ" ይባላል።
◦ጸሎት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለሆነ ነው።
ፀ ➺ ፀሐዩ "ፀ" ይባላል።
◦ፀሐይ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ነው።
✅ እነዚህ ሞክሼ ፊደላት አንዱ በአንዱ ቦታ መግባት የለበትም ምክንያቱም የትርጉም ለውጥ ያመጣሉ።
ለምሳሌ ፦
➺ ሠረቀ = ወጣ
ሰረቀ = ሰረቀ
➺ አመት = አገልጋይ
ዓመት = ዘመን
➺ ሰዐለ = ስዕል ሳለ
ሰአለ = ለመነ
➺ መሀረ = አስተማረ
መሐረ = ይቅር አለ
➺ ኀለየ = አመሰገነ
ሐለየ = አሰበ
➺ ፈጸመ = ጨረሰ
ፈፀመ = ነጨ
➺ ማኅሌት = ማመስገን
ማሕሌት = ማሰብ
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
#ፍቅር_ማለት
ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
ኢ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________
@aleroe
#ፍቅር_ማለት
ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
ኢ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
# ትሕትና + ትእግስት + ተስፋ + ፅናት + ፍቅር + እምነት + አምልኮት + ምግባር=>ስኬት!!
~አንዲት ስጋ የምትጠብስ ሴት ስጋውን መጥበሻው ላይ ትጥደውና ስጋውን ታገላብጠዋለች ።ከዛ መብሰል አለመብሰሉን ለማረጋገጥ በሹካ ወጋ ወጋ አድርጋ ታየዋለች። ከበሰለ ታወርድና ለመዓድ ገበታ ላይ ታቀርበዋለች።ልብ በሉ....
~ፈጣሪም እኛን ይለዉጥናል እውቀት ይሰጡናል ያበስሉናል ብሎ ባሰባቸው በተለያዩ ነገሮች ላይ ይጥደንና ጤና ማጣት፣ስራ ማጣት፣ወዳጅ ማጣት፣ የህይወት አጋር ማጣት፣ገንዘብ ማጣት፣ፍትሕ ማጣት፣ተስፋ ማጣት፣ነገሮችን አለመሳካት፣ሰርቶ መና፣መከዳት፣መናቅ፣ወ ... በተባሉ ሹካዎች ወጋ ወጋ አድርጎ መብሰል አለመብሰላችንን ያረጋግጣል።
~ችግር ውስጥ ሆነን ካመሰገንን በስለናል ካማረርን ግን ይቀረናልና፤አንዳንዴ በተለያዩ ችግር ውስጥ ጥዶ ያገላብጠናል።
~አንድ ካሜራ ማን እኛን ፎቶ ከማንሳቱ በፊት ፈገግ በል ቀና በል ትንሽ ወደ ቀኝ ምናምን እያለ አስቀድሞ ያስተካክለናል ከዛ ያነሳናል። ፈጣሪም እኛን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያስገባ ነው ህይወታችንን ሚያስተካክለው ምክንያትም የደፈረሰ ህይወታችን መጥራት ስላለበትና ጥርት ለማድረግ።
~መከራ ፈጣሪ እኛን ወደሱ የሚጎትትበት ገመድ ነው። ዳይመንድን ውድ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ አቆራረጡ ነው።ዳይመንድን የምናውቀውን ቅርፁን ያስያዘውና ከተለያየ አቅጣጫ እንዲያንፀባርቅ ያደረገው አቆራረጡ ነው ይላሉ። እኛንም ዛሬ እየቆረጡንና እያስጨነቁን ያሉ ሳንቋቋማቸው ቀርተን እያማረርንባቸው ያለን ችግሮቻችንን ነገ እኛን ዉድና የሚያበራ ማንነት ባለቤት የሚያደርጉን ናቸው ።
~ማዕበል ሲነሳና ባህሩን ሲያማስለው ሁሉም እንስሶች ይሸሻሉ።ንስር አሞራው ግን በመሀሉ ገብቶ ዓሳ ይዞ ይወጣል።
~ ወዳጄ ሆይ እንደ ንስር አሞራው በችግር ውስጥ ብትሆንም እራስህን አንፅ። ሸክላ የምትሰራ ሴት እንኳን ሸክላዋን ሰርታ ስትጨርስ እንዲጠነክርላት በእሳት ነው ምትጠብሰው።ዛሬ የሚጠብሱህ ችግሮችና የህይወት መሰናክሎች ከፀናህ ማንነትህን ነው የሚያጠነክሩልህ።
~ ስለዚህ ስለሆነው ስለሚሆነው እየሆነ ስላለው ፣ ስለተደረግልህ ስላልተደረገልህ ፣ ስለ ሰጠህ ስለ ነፈገህ ነገር ሁሉ እሱን አመስግነው።
~ # እንዲ_በለው ፦
"ደስታንም ሆነ መከራን ብትሰጠኝ አመሰግንሀለሁ፤ ከኔ ይልቅ አንተ ነህና ለእኔ ምትቀርበው።ስለዚህም ጌታ ሆይ በመንገዴና በህይወቴ ሁሉ ፈቃድህ እንጂ ፈቃዴ አይሁን።"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
@aleroe
# ትሕትና + ትእግስት + ተስፋ + ፅናት + ፍቅር + እምነት + አምልኮት + ምግባር=>ስኬት!!
~አንዲት ስጋ የምትጠብስ ሴት ስጋውን መጥበሻው ላይ ትጥደውና ስጋውን ታገላብጠዋለች ።ከዛ መብሰል አለመብሰሉን ለማረጋገጥ በሹካ ወጋ ወጋ አድርጋ ታየዋለች። ከበሰለ ታወርድና ለመዓድ ገበታ ላይ ታቀርበዋለች።ልብ በሉ....
~ፈጣሪም እኛን ይለዉጥናል እውቀት ይሰጡናል ያበስሉናል ብሎ ባሰባቸው በተለያዩ ነገሮች ላይ ይጥደንና ጤና ማጣት፣ስራ ማጣት፣ወዳጅ ማጣት፣ የህይወት አጋር ማጣት፣ገንዘብ ማጣት፣ፍትሕ ማጣት፣ተስፋ ማጣት፣ነገሮችን አለመሳካት፣ሰርቶ መና፣መከዳት፣መናቅ፣ወ ... በተባሉ ሹካዎች ወጋ ወጋ አድርጎ መብሰል አለመብሰላችንን ያረጋግጣል።
~ችግር ውስጥ ሆነን ካመሰገንን በስለናል ካማረርን ግን ይቀረናልና፤አንዳንዴ በተለያዩ ችግር ውስጥ ጥዶ ያገላብጠናል።
~አንድ ካሜራ ማን እኛን ፎቶ ከማንሳቱ በፊት ፈገግ በል ቀና በል ትንሽ ወደ ቀኝ ምናምን እያለ አስቀድሞ ያስተካክለናል ከዛ ያነሳናል። ፈጣሪም እኛን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያስገባ ነው ህይወታችንን ሚያስተካክለው ምክንያትም የደፈረሰ ህይወታችን መጥራት ስላለበትና ጥርት ለማድረግ።
~መከራ ፈጣሪ እኛን ወደሱ የሚጎትትበት ገመድ ነው። ዳይመንድን ውድ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ አቆራረጡ ነው።ዳይመንድን የምናውቀውን ቅርፁን ያስያዘውና ከተለያየ አቅጣጫ እንዲያንፀባርቅ ያደረገው አቆራረጡ ነው ይላሉ። እኛንም ዛሬ እየቆረጡንና እያስጨነቁን ያሉ ሳንቋቋማቸው ቀርተን እያማረርንባቸው ያለን ችግሮቻችንን ነገ እኛን ዉድና የሚያበራ ማንነት ባለቤት የሚያደርጉን ናቸው ።
~ማዕበል ሲነሳና ባህሩን ሲያማስለው ሁሉም እንስሶች ይሸሻሉ።ንስር አሞራው ግን በመሀሉ ገብቶ ዓሳ ይዞ ይወጣል።
~ ወዳጄ ሆይ እንደ ንስር አሞራው በችግር ውስጥ ብትሆንም እራስህን አንፅ። ሸክላ የምትሰራ ሴት እንኳን ሸክላዋን ሰርታ ስትጨርስ እንዲጠነክርላት በእሳት ነው ምትጠብሰው።ዛሬ የሚጠብሱህ ችግሮችና የህይወት መሰናክሎች ከፀናህ ማንነትህን ነው የሚያጠነክሩልህ።
~ ስለዚህ ስለሆነው ስለሚሆነው እየሆነ ስላለው ፣ ስለተደረግልህ ስላልተደረገልህ ፣ ስለ ሰጠህ ስለ ነፈገህ ነገር ሁሉ እሱን አመስግነው።
~ # እንዲ_በለው ፦
"ደስታንም ሆነ መከራን ብትሰጠኝ አመሰግንሀለሁ፤ ከኔ ይልቅ አንተ ነህና ለእኔ ምትቀርበው።ስለዚህም ጌታ ሆይ በመንገዴና በህይወቴ ሁሉ ፈቃድህ እንጂ ፈቃዴ አይሁን።"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
#ነበርኩ_መች_ያድናል
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
____________________
@aleroe
#ነበርኩ_መች_ያድናል
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
____________________
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
ኤልሮኢ:
✉ ለራስህ ነው ✉
አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡
ገና ጨቅላ እያለ በጎ በጎ ትእዛዛት በሕሊናው ጓዳ በልቡናው ሰሌዳ ላይ ከተቀረጸ፥ በሰም እንደ ታተመ ጸንቶ ይኖራል እንጂ ሲያድግ እነዚህን ትእዛዛት ሊያጠፋበትና ሊፍቅበት የሚችል ማንም አይኖርምና፡፡ ልጅህ አሁን ያለበት ዕድሜ ደግሞ በሚያየውና በሚነገረው በሌላም ነገር ኹሉ የሚንቀጠቀጥበት፣ የሚፈራበትና የሚደነግጥበት ዕድሜ ነው፡፡ ስለዚህ ልክ እንዳልደረቀ ሰም እንደምትፈልገው አድርገህ ቅረጸው፡፡ እንደዚህ አድርገህ ስታበቃ፥ መልካም ልጅ ቢኖርህ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የምትኾነው አንተው ራስህ ነህ፡፡ እግዚአብሔር የሚጠቀመው ከአንተ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ የምትደክመው ለሌላ አካል ሳይኾን ለራስህ ነው፡፡
✝ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ
@aleroe
✉ ለራስህ ነው ✉
አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡
ገና ጨቅላ እያለ በጎ በጎ ትእዛዛት በሕሊናው ጓዳ በልቡናው ሰሌዳ ላይ ከተቀረጸ፥ በሰም እንደ ታተመ ጸንቶ ይኖራል እንጂ ሲያድግ እነዚህን ትእዛዛት ሊያጠፋበትና ሊፍቅበት የሚችል ማንም አይኖርምና፡፡ ልጅህ አሁን ያለበት ዕድሜ ደግሞ በሚያየውና በሚነገረው በሌላም ነገር ኹሉ የሚንቀጠቀጥበት፣ የሚፈራበትና የሚደነግጥበት ዕድሜ ነው፡፡ ስለዚህ ልክ እንዳልደረቀ ሰም እንደምትፈልገው አድርገህ ቅረጸው፡፡ እንደዚህ አድርገህ ስታበቃ፥ መልካም ልጅ ቢኖርህ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የምትኾነው አንተው ራስህ ነህ፡፡ እግዚአብሔር የሚጠቀመው ከአንተ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ የምትደክመው ለሌላ አካል ሳይኾን ለራስህ ነው፡፡
✝ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ
@aleroe
ጥር 24/05/2012
✝ የቅዳሴ ምንባባት
፪ ቆሮ ም ፩ ቁ ፲፫-ፍ.ም
፩ ዮሐ ም ፪ ቁ ፳፪-ፍ.ም
ግብ.ሐዋ ም ፲፫ ቁ ፳-፳፰
✝ ምስባክ
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርእየ ለነ
ግበሩ በዐለበት ትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ
🙏 ትርጉም
እግዚአብሔር አምላክ ነው ለእኛም በራልን
እሰከ መሠዊያው ቀንዶች ደረሱ
በዓሉ መሥዋዕት በገመድ እስሩት
መዝ ፻፲፮-፳፮
✝ ወንጌል
ሉቃ 2÷42 ፍ.ም
✝ ቅዳሴ
ዘሐዋርያት አው ዘዲዮስቆሮስ
@aleroe
✝ የቅዳሴ ምንባባት
፪ ቆሮ ም ፩ ቁ ፲፫-ፍ.ም
፩ ዮሐ ም ፪ ቁ ፳፪-ፍ.ም
ግብ.ሐዋ ም ፲፫ ቁ ፳-፳፰
✝ ምስባክ
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርእየ ለነ
ግበሩ በዐለበት ትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ
🙏 ትርጉም
እግዚአብሔር አምላክ ነው ለእኛም በራልን
እሰከ መሠዊያው ቀንዶች ደረሱ
በዓሉ መሥዋዕት በገመድ እስሩት
መዝ ፻፲፮-፳፮
✝ ወንጌል
ሉቃ 2÷42 ፍ.ም
✝ ቅዳሴ
ዘሐዋርያት አው ዘዲዮስቆሮስ
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ሩጫ ✞............🏃🏃🏃🏃
ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።
@aleroe
ሩጫ ✞............🏃🏃🏃🏃
ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
#ወይ_ማወቅ_ደጉ !
በባህር_በጥልቁ በሰማይ ተማክሮ
ሊወጋው_ምስኪኑን ሃይል አስተባብሮ
ሄደ ከምስኪኑ ሰፈር
ሊያጠፋው መታሰቢያው ሳይቀር
ዉጣ ይለይልህ ኪዳን አለኝ ማለት
ፀሎቱ መዝሙሩ አይደለም ከማጀት
ይህን ሁሉ ፉከራ የሰማው ምስኪን ሰው
ወዬው ጠፋሁ ብሎ ፍርሃት ብርክ ያዘው
የሞት ሞቱን ጨክኖ ብቅ ቢልባቸው
የያዙት_መሳሪያ ወደቀ ከጃቸው
እግሬ_አውጭኝ እግሬ አውጭኝ
እያሉ በሽቅድምድም
ሄዱ ከመጡበት አለም
ይህ ሁሉ የሆነው..ምክንያቱ ምንድነው?
ጋሻ ጦር አልያዝኩኝ....ይሄው ባዶየን ነኝ
ምን አይተው ሮጡ......ሊገሉኝ የመጡ
እያለ ምስኪኑ ግራ እየተጋባ
ግድግዳው ላይ ካለው መስታወት ተጠጋ
ድንገት ቀና ብሎ ፊቱን ቢመለከት
ለካስ_የኢየሱስ ደም በግንባሩ አለበት
አሃ ! ደሙን አይተው ነው የተመለሱት
ወይ ማወቅ ደጉ!
#ለካስ_መፍትሄው ግንባርን ማሳየት
#ያኔ_ይመለሳል ሰይጣን ከመጣበት ።
@aleroe
#ወይ_ማወቅ_ደጉ !
በባህር_በጥልቁ በሰማይ ተማክሮ
ሊወጋው_ምስኪኑን ሃይል አስተባብሮ
ሄደ ከምስኪኑ ሰፈር
ሊያጠፋው መታሰቢያው ሳይቀር
ዉጣ ይለይልህ ኪዳን አለኝ ማለት
ፀሎቱ መዝሙሩ አይደለም ከማጀት
ይህን ሁሉ ፉከራ የሰማው ምስኪን ሰው
ወዬው ጠፋሁ ብሎ ፍርሃት ብርክ ያዘው
የሞት ሞቱን ጨክኖ ብቅ ቢልባቸው
የያዙት_መሳሪያ ወደቀ ከጃቸው
እግሬ_አውጭኝ እግሬ አውጭኝ
እያሉ በሽቅድምድም
ሄዱ ከመጡበት አለም
ይህ ሁሉ የሆነው..ምክንያቱ ምንድነው?
ጋሻ ጦር አልያዝኩኝ....ይሄው ባዶየን ነኝ
ምን አይተው ሮጡ......ሊገሉኝ የመጡ
እያለ ምስኪኑ ግራ እየተጋባ
ግድግዳው ላይ ካለው መስታወት ተጠጋ
ድንገት ቀና ብሎ ፊቱን ቢመለከት
ለካስ_የኢየሱስ ደም በግንባሩ አለበት
አሃ ! ደሙን አይተው ነው የተመለሱት
ወይ ማወቅ ደጉ!
#ለካስ_መፍትሄው ግንባርን ማሳየት
#ያኔ_ይመለሳል ሰይጣን ከመጣበት ።
@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
ኤልሮኢ:(መዝሙር)
#የሚጠብቀኝ አይተኛም
የሚጠብቀኝ አይተኛም(×2) አያንቀላፋም(×2)
ቤት ባይኖረኝም
በደጅ ባድር
ቀንና ሌሊት ከኔ አይርቅም
ድምፀ አራዊት የሌሊት ግርማ
ወደ እኔ አይገቡም ድምፅህ ሲሰማ
መሰናከልን ለእግሮቼ አይሰጥም
ይሰውረኛል በቀኙ ሰላም
ፀሀይም በቀን አይተኩሰኝም
የአጋንንትም ሀይል አያስፈራኝም
ነፍሴን ጠበቃት ከጠላት ወጥመድ
ጌታዬ መራኝ በፅድቅ መንገድ
መውጣት መግባቴን እየጠበቀ
ለዚህ አበቃኝ እርሱ ባወቀ
የሰማዩን ጥል እታገሳለሁ
ሰው ከጨከነ ምን እሆናለሁ
ሌሊት በድብቅ ለሚጎበኙ
ለፃድቃኑ ግን አምላክ ይስጥልኝ
እንቅልፌን ባርኮ የሰጠኝ ጌታ
በዓለም ሀሳብ ሳልንገላታ
የዕለት ምግቤንም ላልነሳኝ ፍፁም
ምስጋና ላቅርብ እስከዘላለም
#ዘማሪ ይልማ
@aleroe
#የሚጠብቀኝ አይተኛም
የሚጠብቀኝ አይተኛም(×2) አያንቀላፋም(×2)
ቤት ባይኖረኝም
በደጅ ባድር
ቀንና ሌሊት ከኔ አይርቅም
ድምፀ አራዊት የሌሊት ግርማ
ወደ እኔ አይገቡም ድምፅህ ሲሰማ
መሰናከልን ለእግሮቼ አይሰጥም
ይሰውረኛል በቀኙ ሰላም
ፀሀይም በቀን አይተኩሰኝም
የአጋንንትም ሀይል አያስፈራኝም
ነፍሴን ጠበቃት ከጠላት ወጥመድ
ጌታዬ መራኝ በፅድቅ መንገድ
መውጣት መግባቴን እየጠበቀ
ለዚህ አበቃኝ እርሱ ባወቀ
የሰማዩን ጥል እታገሳለሁ
ሰው ከጨከነ ምን እሆናለሁ
ሌሊት በድብቅ ለሚጎበኙ
ለፃድቃኑ ግን አምላክ ይስጥልኝ
እንቅልፌን ባርኮ የሰጠኝ ጌታ
በዓለም ሀሳብ ሳልንገላታ
የዕለት ምግቤንም ላልነሳኝ ፍፁም
ምስጋና ላቅርብ እስከዘላለም
#ዘማሪ ይልማ
@aleroe
ኤልሮኢ:
ዘፈን' #ለምን_ተከለከለ?
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለምን ዘፈንን አወገዘች???
#1. ዘፈን የአጋንንት ሥራ ነው:: አጋንንት ይዘፍናሉና:: ለዚህ ምንም ማስተባበያ አያስፈልገውም:: መጽሐፍ ቅዱስ "በዚያም አጋንንት ይዘፍናሉ" በማለት ስለ አጋንንት ዘፋኝነት ይናገራል::(ኢሳ.13:21) አትዝፈኑ ማለት የአጋንንትን ሥራ አትሥሩ ማለት መሆኑን እንረዳ:: ይህን በተመለከተ መጽሐፈ መቃብያን ደግሞ እንዲህ ይላል:- "....እየዘፈኑም ከአጋንንት ጋር ይጫወቱ ነበር:: አጋንንትም ጫወታቸውንና ዘፈናቸውንም ሁሉ ያደንቁላቸው ነበር::" (1ኛ.መቃ.36፥27-28) በዚህ ስፍራ አገላለጥ ደግሞ ለየት የሚለው አጋንንት ዘፋኞች ብቻ ሳይሆኑ ከዘፈን አድናቂዎች ጐራ መሰለፋቸው ነው::
#2. ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ሥራን አስመልክቶ ሲናገር እንዲህ ይላል:- "ስለ ተግባረ ዕድ ግን በዓለም ከሚሠሩ ሥራዎች መንፈሳዊ ሕግን ከሚቃወም ሥራ በቀር ሁሉንም ሊሠሩ ይገባል:: ... እንደ ዘፋኝነት፥ እንደ መጥፎ ጫወታ፥
በእግር እንደ ማሸብሸብ(ዳንስና ጭፈራ) ካልሆነ በቀር ነው::" (ፍት.ነገ.መን.አን. 23:820) ይህ የአበው ቃል ዘፋኝነት በመንፈሳዊ እይታ እንደ ሥራ መቆጠር እንደሌለበት ያስረዳል::
#3. ዘፋኝነት "የሥጋ ሥራ" በመሆኑ ኃጢአት ነው::
(ገላ.5:21):: "በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ፤" ተብሏልና:: (ገላ.5:16)::
#4. ዘፈን በመንፈሳውያን መጻሕፍት ተወግዟል:: ሐዋርያት በዲድስቅልያ "ኢትኩኑ ዘፈንያነ" ፥ "ዘፋኞች አትሁኑ" ብለዋል:: (ዲድስቅልያ፤ አንቀጽ 7) ቅዱስ ጳውሎስ "በቀን እንደምንሆን በአግባብ እንመላለስ:: በዘፈንና በስካር አይሁን" ብሏል:: (ሮሜ.13፥13) ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ "በስካርና በዘፈን የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል::" ይለናል:: (1ኛ.ጴጥ.4:3):: መጽሐፈ ሐዊ ደግሞ "ከሰይጣን የተገኘ ነውና ዘፈንንና ዳንስን ከኛ ማራቅ ይገባናል::" ይለናል:: (መጽ.ሐዊ አን. 50):: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ደግሞ ከማዘዝ አልፎ ዘፈንን እንተው ዘንድ "ዘፈንን ትተዉ ዘንድ እማልዳችሗለሁ፤" በማለት ይማጸናል:: (ተግ.ዘዮሐ.አፈ.28) ዘፈንን አንተውም
ላሉ ደግሞ መጽሐፈ ሐዊ "በዘፈን ጸንተው የሚኖሩ ይፈረድባቸዋል" በማለት ሲያስጠነቅቅ እናገኛለን:: (መጽ.ሐዊ.አን. 12)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@aleroe
ዘፈን' #ለምን_ተከለከለ?
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለምን ዘፈንን አወገዘች???
#1. ዘፈን የአጋንንት ሥራ ነው:: አጋንንት ይዘፍናሉና:: ለዚህ ምንም ማስተባበያ አያስፈልገውም:: መጽሐፍ ቅዱስ "በዚያም አጋንንት ይዘፍናሉ" በማለት ስለ አጋንንት ዘፋኝነት ይናገራል::(ኢሳ.13:21) አትዝፈኑ ማለት የአጋንንትን ሥራ አትሥሩ ማለት መሆኑን እንረዳ:: ይህን በተመለከተ መጽሐፈ መቃብያን ደግሞ እንዲህ ይላል:- "....እየዘፈኑም ከአጋንንት ጋር ይጫወቱ ነበር:: አጋንንትም ጫወታቸውንና ዘፈናቸውንም ሁሉ ያደንቁላቸው ነበር::" (1ኛ.መቃ.36፥27-28) በዚህ ስፍራ አገላለጥ ደግሞ ለየት የሚለው አጋንንት ዘፋኞች ብቻ ሳይሆኑ ከዘፈን አድናቂዎች ጐራ መሰለፋቸው ነው::
#2. ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ሥራን አስመልክቶ ሲናገር እንዲህ ይላል:- "ስለ ተግባረ ዕድ ግን በዓለም ከሚሠሩ ሥራዎች መንፈሳዊ ሕግን ከሚቃወም ሥራ በቀር ሁሉንም ሊሠሩ ይገባል:: ... እንደ ዘፋኝነት፥ እንደ መጥፎ ጫወታ፥
በእግር እንደ ማሸብሸብ(ዳንስና ጭፈራ) ካልሆነ በቀር ነው::" (ፍት.ነገ.መን.አን. 23:820) ይህ የአበው ቃል ዘፋኝነት በመንፈሳዊ እይታ እንደ ሥራ መቆጠር እንደሌለበት ያስረዳል::
#3. ዘፋኝነት "የሥጋ ሥራ" በመሆኑ ኃጢአት ነው::
(ገላ.5:21):: "በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ፤" ተብሏልና:: (ገላ.5:16)::
#4. ዘፈን በመንፈሳውያን መጻሕፍት ተወግዟል:: ሐዋርያት በዲድስቅልያ "ኢትኩኑ ዘፈንያነ" ፥ "ዘፋኞች አትሁኑ" ብለዋል:: (ዲድስቅልያ፤ አንቀጽ 7) ቅዱስ ጳውሎስ "በቀን እንደምንሆን በአግባብ እንመላለስ:: በዘፈንና በስካር አይሁን" ብሏል:: (ሮሜ.13፥13) ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ "በስካርና በዘፈን የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል::" ይለናል:: (1ኛ.ጴጥ.4:3):: መጽሐፈ ሐዊ ደግሞ "ከሰይጣን የተገኘ ነውና ዘፈንንና ዳንስን ከኛ ማራቅ ይገባናል::" ይለናል:: (መጽ.ሐዊ አን. 50):: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ደግሞ ከማዘዝ አልፎ ዘፈንን እንተው ዘንድ "ዘፈንን ትተዉ ዘንድ እማልዳችሗለሁ፤" በማለት ይማጸናል:: (ተግ.ዘዮሐ.አፈ.28) ዘፈንን አንተውም
ላሉ ደግሞ መጽሐፈ ሐዊ "በዘፈን ጸንተው የሚኖሩ ይፈረድባቸዋል" በማለት ሲያስጠነቅቅ እናገኛለን:: (መጽ.ሐዊ.አን. 12)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
እኅቴን ላኩልኝ
#በዲ/ን ሕሊና በለጠ
√
ምነው ጨላለመች - የሀገሬ ፀሐይ
የሴት ልጅ ደም ፈሶ - ሥርየት አለ ወይ?
√
ዓርቡ የረዘመ - እሑዱ የራቀው
ምን የሚሉት ጾም ነው - ባ'ገሬ የገባው?
√
ምን ክፋት ቢኖርህ - ምንም ያ'ል ብታቄም
ምን ጀብደኛ ብትኾን - ብታደራጅ አቅም
ሴት አሥሮ 'ሚሟገት - ጀግናስ እኔ አላውቅም።
√
መጥቀው እንዲያመጥቁን - ብንሰድ እንዲማሩ
በዕውቀት ተራቀው - ተሠወሩ አሉ።
√
"ከማጀት ላውላት" - ብዬ ነበር ያኔ
"ግድ የሎትም ትማር" - ብለው ወትውተውኝ - ነጥለው ከጎኔ
ትም' ርቱ አልበቃ ቢል - ለጦር ላኳት አሉ - ወዮ ኧረ ወይኔ!
√
እኅትነት ቅኔ - መውደዷም ነው ዕንቁ
ደግሞ ሠወር ስትል - እንኳንስ ሕይወቷ - ድምጿም መናፈቁ።
√
ያገሬ መጋኛ - ጥፊው አያጠፋም
ያገሬ ሰላቢ - ምትሐቱ ዕቃን እንጂ - ሰውን አይሠውርም።
አፍኖ የዋጠሽ - ሲያኝክ ማያሰማ
የየት አገሩ ይኾን - የበላሽ እቴዋ!?
√
ምግቡም ጣዕም የለው - አልበላ አለኝ
አጣፍጣ ታጉርሰኝ - እኅቴን ላኩልኝ።
@aleroe
#በዲ/ን ሕሊና በለጠ
√
ምነው ጨላለመች - የሀገሬ ፀሐይ
የሴት ልጅ ደም ፈሶ - ሥርየት አለ ወይ?
√
ዓርቡ የረዘመ - እሑዱ የራቀው
ምን የሚሉት ጾም ነው - ባ'ገሬ የገባው?
√
ምን ክፋት ቢኖርህ - ምንም ያ'ል ብታቄም
ምን ጀብደኛ ብትኾን - ብታደራጅ አቅም
ሴት አሥሮ 'ሚሟገት - ጀግናስ እኔ አላውቅም።
√
መጥቀው እንዲያመጥቁን - ብንሰድ እንዲማሩ
በዕውቀት ተራቀው - ተሠወሩ አሉ።
√
"ከማጀት ላውላት" - ብዬ ነበር ያኔ
"ግድ የሎትም ትማር" - ብለው ወትውተውኝ - ነጥለው ከጎኔ
ትም' ርቱ አልበቃ ቢል - ለጦር ላኳት አሉ - ወዮ ኧረ ወይኔ!
√
እኅትነት ቅኔ - መውደዷም ነው ዕንቁ
ደግሞ ሠወር ስትል - እንኳንስ ሕይወቷ - ድምጿም መናፈቁ።
√
ያገሬ መጋኛ - ጥፊው አያጠፋም
ያገሬ ሰላቢ - ምትሐቱ ዕቃን እንጂ - ሰውን አይሠውርም።
አፍኖ የዋጠሽ - ሲያኝክ ማያሰማ
የየት አገሩ ይኾን - የበላሽ እቴዋ!?
√
ምግቡም ጣዕም የለው - አልበላ አለኝ
አጣፍጣ ታጉርሰኝ - እኅቴን ላኩልኝ።
@aleroe
ኤልሮኢ:
የቫላንታይን ቀን በዓል - ድብቅ እውነታ
======================
(ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ)
ስንቶቻችን ይሆን የቫለንታይን ቀን(የፍቅረኞች ቀን ብለን የምናከብረው) የሚከበርበት ምክንያትና መነሻው የምናውቀው? ወይስ ሰው ስለ አከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው? ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ክፍለ ዘመናት በፊት አረማዊ ሮማውያንየካቲት 14 ማታና የካቲት 15 "የተኩላ አዳኙ"ለሚሉት ሉፐርኩስ(Lupercus) ክብር በማለት በጣኦት አምልኮ ያከብሩት ነበር።ሮማውያን ይህ በዓል ሉፐርካልያ
(Lupercalia) ይሉታል።ንጉሥ ቆንጠንጢኖስ ክርስትና የሮማውያን ይፋዊ ሃይማኖት መሆኑ በማወጁ ማነኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተወስኑ ሮማውያን
ሰዎች ግን በዓሉን ማክበር አልተዉም።ይህንን አረማዊ በዓል
ማለትም ሉፐርካልያ የሮማው ጳጳስ ገላስዮስ ክርስትያናዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር አደረጉ።ጳጳስ ገላስዮስ ለካቲት 15 ሲከበር የነበረው በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን በሚል አዲስ ስያሜ የካቲት 14 እንዲከበር አደረጉ።
እንዴት ይህ አረማዊ በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የሚል ስያሜ ተሰጠው?
ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው።ቫላንታይን ጥንታዊው ታዋቂው ሉፐርኩስ ነው።ሉፐርኩስ በግሪካውያን ፓን(pan) ተብሎ ይጠራል።በጥንታውያን አይሁድ
ደግሞ ይህ ፓን ባል(Baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።ባል በመጽሓፍ ቅዱስ ዘፍጥረት 10-9 ላይ ታላቁ አዳኝ ተብሎ
ለተገለጸው ኒምሮድ ሌላኛው መጠርያው ነው።ኒምሮድ የሮማውያን የተኩላ አዳኙ ሉፐርኩስ ነበር።በዚህ መሠረትም
የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የአረማውያን ለኒምሮድ ክብር የሚያከብሩት የጣኦት አምልኮ ነው። ቫለንታይን የሚል ቃል ቫለንቲኑስ(valentinus) ቫለንስ ከሚል
የላቲን ቃል የመጣ ነው።ቀጥተኛ ትርጉሙ ጠንካራ፣ሃይለኛ
ታላቅ ማለት ነው።ዘፍጥረት10-9 ላይ እንደምናነበው " እርሱም
በእግዚአብሔር ፊት አዳኝ ነበረ ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር
ፊት ሃያል አዳኝ እንደ ኒምሮድ ተባለ።" ኒምሮድ የሮማውያን
ጀግና ሃይለኛ ሰው ቫለንታይን ነበር።
ሌላኛው የኒምሮድ ስም ሳንክቱስ(Sancutus) ወይ ሳንታ
(santa) ነው ሳይንት(saint) የሚል የእግሊዝኛ ትርጉምአለው
ማለትም ቅዱስ።የሮማውያን ሉፐርካልያ በመጨረሻ ቅዱስ
ቫለንታይን የሚል ስያሜያዘ ማለት ነው።
ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን በቀዱት አረማዊ የልብ
(heart) ምልክት ይጠቀማሉ።በባቢሎናውያን ባል(bal) ልብ የሚል ፍቺ ነው ያለው።በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት
ለቫለንታይን ቀን(የፍቅረኛሞች ቀንየምንለው) መገለጫ እንጠቀምበታለን።ባል የባቢሎናውያን የጣኦት ጌታ ነበር።በሌላ መንገድም ኒምሮድ ወይም ቅዱስ ቫለንታይን ሳተርን ተብሎ ይጠራል።ሳተርን የሮማ-ባቢሎን ከአባራሮዎቹ ለመሸሽ በምስጥራዊ ቦታ የሚደበቅ ጣኦት ነው።ሳተርን የሚል የላቲን ቃል ሴመቲክ(አይሁድ) ቋንቋ ከሚናገሩ ባቢሎናውያን የተገኝ ነው።መደበቅ፣ራስን መደበቅ የሚል ፍቺ አለው። በጥንታዊ እምነትም ኒምሮድ(ሳተርን) ከአባራሮዎቹ በመሸሽ ወደ ጣልያን እንደተጓዘይነገራል።የአፐኒን ተራራ ስያሜው ወደ ኔምብሮድ ወይም ኒምሮድ ተቀየረ።ይህ ተራራ ኒምሮድ በጣልያን የተሸሸገበት ቦታ ነበር።ሮማም በዚ ተራራ ላይ እንደ ተመሰረተች ይታወቃል።ሮም ፈርሳ እንደገና ከመሰራትዋ 753ዓ/ዓ በፊት ሳቹርንያ (ሳተርን፡ኒምሮድ የተደበቀባት ቦታ) የሚል ስያሜ ነበራት።ኒምሮድ በዚህ ቦታ ተይዞበፈጸመው ወንጀል ተገደለ።በንጉሥ ቆስጠንጦኖስ ጊዜም ክርስትያናዊ ሰማዕት የሚል የውሸት ክብር ተሰጥቶት በሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን
መዘከር ጀመረ።ኒምሮድ፣ባል፣ቫለንታይን፣ታላቁ አዳኝ፣ፋውኑስና ሉፐርክስ 31ኛ፣32ኛና 33ኛና ደረጃ (ዲግሪ) ላይ ያሉ ፍሪማሶኖሪዎች ከሚያመልኩትባፎሜት(የሜንደዝ ፍየል) ጋር የሚስተካከል ነው። እንግዲህ በሰላቢ እጆች (ኢሊሙናቲ) ሴራ ዘመናዊነት ተላብሶ ድብቅ ጣኦት የሚመለክበት የቅዱስ ቫለንታይን ቀን እኛ ደግሞ የፍቅረኛሞች ቀን በማለት እያከበርን ማለትም እያመለክን ነው።አንድ በአል የሚከበርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሊኖረው ግድ ነው።ሆኖም የምናከብረውን በአል የምናከብርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሳናውቅ ከሴሮኞች ድብቅ አላማ ማስፈጸምያ ከመሆን መቆጠብ ይበጃል።
@aleroe
የቫላንታይን ቀን በዓል - ድብቅ እውነታ
======================
(ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ)
ስንቶቻችን ይሆን የቫለንታይን ቀን(የፍቅረኞች ቀን ብለን የምናከብረው) የሚከበርበት ምክንያትና መነሻው የምናውቀው? ወይስ ሰው ስለ አከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው? ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ክፍለ ዘመናት በፊት አረማዊ ሮማውያንየካቲት 14 ማታና የካቲት 15 "የተኩላ አዳኙ"ለሚሉት ሉፐርኩስ(Lupercus) ክብር በማለት በጣኦት አምልኮ ያከብሩት ነበር።ሮማውያን ይህ በዓል ሉፐርካልያ
(Lupercalia) ይሉታል።ንጉሥ ቆንጠንጢኖስ ክርስትና የሮማውያን ይፋዊ ሃይማኖት መሆኑ በማወጁ ማነኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተወስኑ ሮማውያን
ሰዎች ግን በዓሉን ማክበር አልተዉም።ይህንን አረማዊ በዓል
ማለትም ሉፐርካልያ የሮማው ጳጳስ ገላስዮስ ክርስትያናዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር አደረጉ።ጳጳስ ገላስዮስ ለካቲት 15 ሲከበር የነበረው በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን በሚል አዲስ ስያሜ የካቲት 14 እንዲከበር አደረጉ።
እንዴት ይህ አረማዊ በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የሚል ስያሜ ተሰጠው?
ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው።ቫላንታይን ጥንታዊው ታዋቂው ሉፐርኩስ ነው።ሉፐርኩስ በግሪካውያን ፓን(pan) ተብሎ ይጠራል።በጥንታውያን አይሁድ
ደግሞ ይህ ፓን ባል(Baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።ባል በመጽሓፍ ቅዱስ ዘፍጥረት 10-9 ላይ ታላቁ አዳኝ ተብሎ
ለተገለጸው ኒምሮድ ሌላኛው መጠርያው ነው።ኒምሮድ የሮማውያን የተኩላ አዳኙ ሉፐርኩስ ነበር።በዚህ መሠረትም
የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የአረማውያን ለኒምሮድ ክብር የሚያከብሩት የጣኦት አምልኮ ነው። ቫለንታይን የሚል ቃል ቫለንቲኑስ(valentinus) ቫለንስ ከሚል
የላቲን ቃል የመጣ ነው።ቀጥተኛ ትርጉሙ ጠንካራ፣ሃይለኛ
ታላቅ ማለት ነው።ዘፍጥረት10-9 ላይ እንደምናነበው " እርሱም
በእግዚአብሔር ፊት አዳኝ ነበረ ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር
ፊት ሃያል አዳኝ እንደ ኒምሮድ ተባለ።" ኒምሮድ የሮማውያን
ጀግና ሃይለኛ ሰው ቫለንታይን ነበር።
ሌላኛው የኒምሮድ ስም ሳንክቱስ(Sancutus) ወይ ሳንታ
(santa) ነው ሳይንት(saint) የሚል የእግሊዝኛ ትርጉምአለው
ማለትም ቅዱስ።የሮማውያን ሉፐርካልያ በመጨረሻ ቅዱስ
ቫለንታይን የሚል ስያሜያዘ ማለት ነው።
ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን በቀዱት አረማዊ የልብ
(heart) ምልክት ይጠቀማሉ።በባቢሎናውያን ባል(bal) ልብ የሚል ፍቺ ነው ያለው።በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት
ለቫለንታይን ቀን(የፍቅረኛሞች ቀንየምንለው) መገለጫ እንጠቀምበታለን።ባል የባቢሎናውያን የጣኦት ጌታ ነበር።በሌላ መንገድም ኒምሮድ ወይም ቅዱስ ቫለንታይን ሳተርን ተብሎ ይጠራል።ሳተርን የሮማ-ባቢሎን ከአባራሮዎቹ ለመሸሽ በምስጥራዊ ቦታ የሚደበቅ ጣኦት ነው።ሳተርን የሚል የላቲን ቃል ሴመቲክ(አይሁድ) ቋንቋ ከሚናገሩ ባቢሎናውያን የተገኝ ነው።መደበቅ፣ራስን መደበቅ የሚል ፍቺ አለው። በጥንታዊ እምነትም ኒምሮድ(ሳተርን) ከአባራሮዎቹ በመሸሽ ወደ ጣልያን እንደተጓዘይነገራል።የአፐኒን ተራራ ስያሜው ወደ ኔምብሮድ ወይም ኒምሮድ ተቀየረ።ይህ ተራራ ኒምሮድ በጣልያን የተሸሸገበት ቦታ ነበር።ሮማም በዚ ተራራ ላይ እንደ ተመሰረተች ይታወቃል።ሮም ፈርሳ እንደገና ከመሰራትዋ 753ዓ/ዓ በፊት ሳቹርንያ (ሳተርን፡ኒምሮድ የተደበቀባት ቦታ) የሚል ስያሜ ነበራት።ኒምሮድ በዚህ ቦታ ተይዞበፈጸመው ወንጀል ተገደለ።በንጉሥ ቆስጠንጦኖስ ጊዜም ክርስትያናዊ ሰማዕት የሚል የውሸት ክብር ተሰጥቶት በሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን
መዘከር ጀመረ።ኒምሮድ፣ባል፣ቫለንታይን፣ታላቁ አዳኝ፣ፋውኑስና ሉፐርክስ 31ኛ፣32ኛና 33ኛና ደረጃ (ዲግሪ) ላይ ያሉ ፍሪማሶኖሪዎች ከሚያመልኩትባፎሜት(የሜንደዝ ፍየል) ጋር የሚስተካከል ነው። እንግዲህ በሰላቢ እጆች (ኢሊሙናቲ) ሴራ ዘመናዊነት ተላብሶ ድብቅ ጣኦት የሚመለክበት የቅዱስ ቫለንታይን ቀን እኛ ደግሞ የፍቅረኛሞች ቀን በማለት እያከበርን ማለትም እያመለክን ነው።አንድ በአል የሚከበርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሊኖረው ግድ ነው።ሆኖም የምናከብረውን በአል የምናከብርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሳናውቅ ከሴሮኞች ድብቅ አላማ ማስፈጸምያ ከመሆን መቆጠብ ይበጃል።
@aleroe